#AddisAbeba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ምክር ቤቱ የ2012 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያካሂዳል ተብሏል፡፡ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አዳራሽ ከዛሬ ጀምሮ በሚካሄደው መደበኛ ጉባኤ ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄዎች የሚነሱባቸውን አራት ተቋማት ማለትም ትምህርት ቢሮ፣ የቤቶችና ኮንስራክሽን ቢሮ፤ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እንዲሁም የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
(አዲስ ሚድያ ኔትወርክ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ምክር ቤቱ የ2012 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያካሂዳል ተብሏል፡፡ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አዳራሽ ከዛሬ ጀምሮ በሚካሄደው መደበኛ ጉባኤ ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄዎች የሚነሱባቸውን አራት ተቋማት ማለትም ትምህርት ቢሮ፣ የቤቶችና ኮንስራክሽን ቢሮ፤ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እንዲሁም የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
(አዲስ ሚድያ ኔትወርክ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ኢጋድ
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) 13ኛው የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) 13ኛው የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia
የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብሰባ ተበተነ!
ፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት ከምርጫ ቦርድ ጋር ሊያደርጉት የነበረው ውይይት በተፈጠረ አለመግባባት ተበተነ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የስነምግባር አዋጅ መፅደቁ ይታወሳል። የፀደቀው አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብ ላይ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ለማድረግ በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ቢሰባሰቡም መግባባት ላይ ባለመድረሳቸው ውይይቱ ተበትኗል።
(AhaduTV)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት ከምርጫ ቦርድ ጋር ሊያደርጉት የነበረው ውይይት በተፈጠረ አለመግባባት ተበተነ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የስነምግባር አዋጅ መፅደቁ ይታወሳል። የፀደቀው አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብ ላይ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ለማድረግ በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ቢሰባሰቡም መግባባት ላይ ባለመድረሳቸው ውይይቱ ተበትኗል።
(AhaduTV)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳይጠበቅ አፍጋኒስታን ሄዱ!
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አፍጋኒስታን የሚገኙ የአሜሪካ ወታደሮችን ጎበኙ። ትራምፕ ጉብኝት እንደሚያካሂዱ ሳያሳውቁ፤ 'ቴንክስጊቪንግ' የተባለውን በዓል አስታከው ወደ አፍጋኒስታን በማቅናት ከወታደሮች ጋር ተገናኝተዋል።
በ 'ባግሪም ኤርፊልድ' የተገኙት ፕሬዘዳንቱ፤ አሜሪካ ከታሊባን ጋር እየተወያየች መሆኑን፣ ታሊባኖች "ስምምነት እንደሚፈልጉም" ለወታደሮቹ ተናገረዋል። ትራምፕ ወደ አፍጋኒስታን ሲሄዱ ይህ የመጀመሪያቸው ሲሆን፤ ከአፍጋኒስታን ፕሬዘዳንት አሽራፍ ጋኒ ጋርም ተገናኛተዋል።
ከታሊባን ጋር ወደ ሰላማዊ ስምምነት ለመመለስ ሲባል፤ የእስረኞች ልውውጥ መካሄዱን ተከትሎ ነው ትራምፕ ወደ አፍጋኒስታን የሄዱት። አሜሪካ ወታደሮቿን "በእጅጉ እየቀነሰች ነው" ሲሉም ተደምጠዋል። አሜሪካ እአአ የደረሰውን የመስከረም 11 ጥቃት ተከትሎ፤ በአፍጋኒስታን ጣልቃ ከገባች 18 ዓመት የሞላ ሲሆን፤ አሁን በአፍጋኒስታን 13,000 ወታደሮች ይቀሯታል።
ትራምፕ ጉብኝታቸውን ያካሄዱት፤ ታሊባን ለአራት ዓመታት ታግተው የነበሩ ሁለት ምዕራባውያን ምሁራንን ነፃ ከለቀቁ በኋላ ነው። በምላሹም ሦስት ታጣቂዎች ነፃ ተደርገዋል። "ከታሊባን ጋር ስንነጋገር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ፈልገን ነበር። እነሱ ግን አልፈለጉም፤ አሁን ግን የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረግ ፈልገዋል" ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል። ውይይቱ ምን ያህል መስመር እንደያዘ የታወቀ ነገር የለም።
(BBC)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አፍጋኒስታን የሚገኙ የአሜሪካ ወታደሮችን ጎበኙ። ትራምፕ ጉብኝት እንደሚያካሂዱ ሳያሳውቁ፤ 'ቴንክስጊቪንግ' የተባለውን በዓል አስታከው ወደ አፍጋኒስታን በማቅናት ከወታደሮች ጋር ተገናኝተዋል።
በ 'ባግሪም ኤርፊልድ' የተገኙት ፕሬዘዳንቱ፤ አሜሪካ ከታሊባን ጋር እየተወያየች መሆኑን፣ ታሊባኖች "ስምምነት እንደሚፈልጉም" ለወታደሮቹ ተናገረዋል። ትራምፕ ወደ አፍጋኒስታን ሲሄዱ ይህ የመጀመሪያቸው ሲሆን፤ ከአፍጋኒስታን ፕሬዘዳንት አሽራፍ ጋኒ ጋርም ተገናኛተዋል።
ከታሊባን ጋር ወደ ሰላማዊ ስምምነት ለመመለስ ሲባል፤ የእስረኞች ልውውጥ መካሄዱን ተከትሎ ነው ትራምፕ ወደ አፍጋኒስታን የሄዱት። አሜሪካ ወታደሮቿን "በእጅጉ እየቀነሰች ነው" ሲሉም ተደምጠዋል። አሜሪካ እአአ የደረሰውን የመስከረም 11 ጥቃት ተከትሎ፤ በአፍጋኒስታን ጣልቃ ከገባች 18 ዓመት የሞላ ሲሆን፤ አሁን በአፍጋኒስታን 13,000 ወታደሮች ይቀሯታል።
ትራምፕ ጉብኝታቸውን ያካሄዱት፤ ታሊባን ለአራት ዓመታት ታግተው የነበሩ ሁለት ምዕራባውያን ምሁራንን ነፃ ከለቀቁ በኋላ ነው። በምላሹም ሦስት ታጣቂዎች ነፃ ተደርገዋል። "ከታሊባን ጋር ስንነጋገር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ፈልገን ነበር። እነሱ ግን አልፈለጉም፤ አሁን ግን የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረግ ፈልገዋል" ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል። ውይይቱ ምን ያህል መስመር እንደያዘ የታወቀ ነገር የለም።
(BBC)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#GamoZone #EmbassyOfItaly
የጋሞ ዞን ከጣሊያን ኢምባሲ ጋር በመተባበር Italian Trade Agency (ICE) ከተባለ ድርጅት ጋር በአትክልትና ፍራፍሬ ምርት አቅርቦትና ማቀነባበር ዙሪያ ውይይት እየተካደ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ በአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበር የሚታወቁ ሶስት የጣሊያን ኩባንያዎች (Tropical Food Machinery, CERMAC,MACFIRUT) የተባሉ ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን የአከባቢውን ምርት ማቀነባበር እና በቀላሉ ለአለም ገበያ ማድረስi በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከዞኑ አመራር፣ ከኢንቨስተሮች እና ህብረት ሥራ ማህበራትና ዩኒየኖች ጋር ተወያይተዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጋሞ ዞን ከጣሊያን ኢምባሲ ጋር በመተባበር Italian Trade Agency (ICE) ከተባለ ድርጅት ጋር በአትክልትና ፍራፍሬ ምርት አቅርቦትና ማቀነባበር ዙሪያ ውይይት እየተካደ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ በአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበር የሚታወቁ ሶስት የጣሊያን ኩባንያዎች (Tropical Food Machinery, CERMAC,MACFIRUT) የተባሉ ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን የአከባቢውን ምርት ማቀነባበር እና በቀላሉ ለአለም ገበያ ማድረስi በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከዞኑ አመራር፣ ከኢንቨስተሮች እና ህብረት ሥራ ማህበራትና ዩኒየኖች ጋር ተወያይተዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብሰባ ተበተነ! ፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት ከምርጫ ቦርድ ጋር ሊያደርጉት የነበረው ውይይት በተፈጠረ አለመግባባት ተበተነ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የስነምግባር አዋጅ መፅደቁ ይታወሳል። የፀደቀው አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብ ላይ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ለማድረግ በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ቢሰባሰቡም መግባባት ላይ ባለመድረሳቸው ውይይቱ ተበትኗል። (AhaduTV) …
የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብሰባ መበተን...
ውይይቱ ሊቋረጥ የቻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ህግ አዋጅ ሆኖ ከመውጣቱ በፊት ረቂቁ ላይ የሰጡት አስተያየት ግብዓት ሆኖ አላገለገለም የሚል ሃሳብ ስላላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
”በመሆኑም የኢትዮጵያ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ህግ አዋጅ ለማስፈጸም በወጣ ረቂቅ ደንብ ላይ ከመወያየታችን በፊት በአዋጁ ላይ ያነሳነው ጥያቄ ሊመለስልን ይገባል” ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱኳን ሚደቅሳ አዋጁ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀ በመሆኑ ከዚህ በኋላ ቦርዱን የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።
በመሆኑም እንደተቋም የአዋጁን ማስፈጸሚያ ደንብ ማውጣትና መተግበር ስለሚያስፈልግ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደባለድርሻ አካላት በረቂቁ ላይ ሃሳብ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲዎቹ አባላት ”ከዚህ በፊት በአዋጁ ረቂቅ ላይ የሰጠነው ሃሳብ ግብዓት ሆኖ ባለማገልገሉ አሁን በዚህ ደንብ ላይ የምንሰጠው አስተያየት ግብዓት ይሆናል የሚል እምነት የለንም” ብለዋል።
በዚህ የተነሳም ለግማሽ ቀን ተጠርቶ የነበረው መድረክ ካለስምምነት ተበትኗል። የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱኳን ሚደቅሳና ሌሎች የቦርዱ አባላት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በሌላ ጊዜ ለውይይት ተዘጋጅተው እንዲመጡ አሳስበው፤ ያላቸውን ጥያቄ በጽሁፍ ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል።
ረቂቅ ደንቡ ፓርቲዎቹ ተወያዩበትም አልተወያዩበትም መጽደቁ ስለማይቀር ለፖለቲካ ሂደቱ ስኬት ሲባል ቢወያዩበት የሚመረጥ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ውይይቱ ሊቋረጥ የቻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ህግ አዋጅ ሆኖ ከመውጣቱ በፊት ረቂቁ ላይ የሰጡት አስተያየት ግብዓት ሆኖ አላገለገለም የሚል ሃሳብ ስላላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
”በመሆኑም የኢትዮጵያ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ህግ አዋጅ ለማስፈጸም በወጣ ረቂቅ ደንብ ላይ ከመወያየታችን በፊት በአዋጁ ላይ ያነሳነው ጥያቄ ሊመለስልን ይገባል” ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱኳን ሚደቅሳ አዋጁ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀ በመሆኑ ከዚህ በኋላ ቦርዱን የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።
በመሆኑም እንደተቋም የአዋጁን ማስፈጸሚያ ደንብ ማውጣትና መተግበር ስለሚያስፈልግ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደባለድርሻ አካላት በረቂቁ ላይ ሃሳብ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲዎቹ አባላት ”ከዚህ በፊት በአዋጁ ረቂቅ ላይ የሰጠነው ሃሳብ ግብዓት ሆኖ ባለማገልገሉ አሁን በዚህ ደንብ ላይ የምንሰጠው አስተያየት ግብዓት ይሆናል የሚል እምነት የለንም” ብለዋል።
በዚህ የተነሳም ለግማሽ ቀን ተጠርቶ የነበረው መድረክ ካለስምምነት ተበትኗል። የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱኳን ሚደቅሳና ሌሎች የቦርዱ አባላት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በሌላ ጊዜ ለውይይት ተዘጋጅተው እንዲመጡ አሳስበው፤ ያላቸውን ጥያቄ በጽሁፍ ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል።
ረቂቅ ደንቡ ፓርቲዎቹ ተወያዩበትም አልተወያዩበትም መጽደቁ ስለማይቀር ለፖለቲካ ሂደቱ ስኬት ሲባል ቢወያዩበት የሚመረጥ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከላይ የምትመለከቱት በድሬ ትዩብ (DireTube) የፌስቡክ ገፅ ላይ ከቀረበው ዜና ጋር የተያያዘው ፎቶ ሀሰተኛ ነው። መረጃው እና ፎቶው ምንም አይነት ግንኙነት የላቸውም።
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በትላንትናው እለት ሁለት ሰዎች ውሀ ውስጥ ገብተው መሞታቸው ተገለጸ!
የአዲስ አበባ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 እንዳስታወቀው በትላንትናው እለት ሁለት ሰዎች ውሃ ውስጥ ገብተው ህይወታቸው አልፏል ብላል፡፡ የመጀመርያው የሞት አደጋ የደረሰው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ እድሜው 40 አመት የሆነ ጎልማስ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ህይወቱ አልፏል ተብሏል፡፡
ሁለተኛው የሞት አደጋ የደረሰው ደግሞ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዮሴፍ ቄስ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ እድሜው 50 አመት የሆነ ጎልማሳ ህይወቱ እንዳለፈ ነው ኮሚሽኑ ያስታወቀው፡፡
በአዲስ አበባ ከቀርብ ጊዜ ወዲህ ጉድጓድ እና ወንዝ ውስጥ ገብተው የሚሞቱ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን በያዝነው ዓመት ብቻ 25 ሰዎች ውሃ ውስጥ ገብተው ሞተዋል፡፡ በከተማዋ ለተለያዩ አገልግሎት ተብለው የሚቀፈሩ ጉድጓዶች በተለይም ለግንባታ እና ለቆሻሻ ማጠራቀምያ እና ለውሀ ማጠራቀሚያ ተብለው የሚቆፈሩ ጉድጓዶች ከፍተኛ አደጋ እያደረሱ እንደሆነ የአዲስ አበባ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያው አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ተናግረዋል፡፡
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የአዲስ አበባ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 እንዳስታወቀው በትላንትናው እለት ሁለት ሰዎች ውሃ ውስጥ ገብተው ህይወታቸው አልፏል ብላል፡፡ የመጀመርያው የሞት አደጋ የደረሰው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ እድሜው 40 አመት የሆነ ጎልማስ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ህይወቱ አልፏል ተብሏል፡፡
ሁለተኛው የሞት አደጋ የደረሰው ደግሞ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዮሴፍ ቄስ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ እድሜው 50 አመት የሆነ ጎልማሳ ህይወቱ እንዳለፈ ነው ኮሚሽኑ ያስታወቀው፡፡
በአዲስ አበባ ከቀርብ ጊዜ ወዲህ ጉድጓድ እና ወንዝ ውስጥ ገብተው የሚሞቱ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን በያዝነው ዓመት ብቻ 25 ሰዎች ውሃ ውስጥ ገብተው ሞተዋል፡፡ በከተማዋ ለተለያዩ አገልግሎት ተብለው የሚቀፈሩ ጉድጓዶች በተለይም ለግንባታ እና ለቆሻሻ ማጠራቀምያ እና ለውሀ ማጠራቀሚያ ተብለው የሚቆፈሩ ጉድጓዶች ከፍተኛ አደጋ እያደረሱ እንደሆነ የአዲስ አበባ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያው አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ተናግረዋል፡፡
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የእንጦጦ የሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና ግንባታ ተጠናቀቀ!
በእንጦጦ ኦብዘረቫቶሪና ምርምር ማዕከል የሚካሄደው የሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና ግንባታ ተጠናቀቀ፡፡ በማዕከሉ የተገነባው የመረጃ መቀበያ አንቴና ኢትዮጵያ በቅርቡ የምታመጥቃትን ሳተላይት ጨምሮ ለሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ አገልግሎት የሚውል መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
(የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በእንጦጦ ኦብዘረቫቶሪና ምርምር ማዕከል የሚካሄደው የሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና ግንባታ ተጠናቀቀ፡፡ በማዕከሉ የተገነባው የመረጃ መቀበያ አንቴና ኢትዮጵያ በቅርቡ የምታመጥቃትን ሳተላይት ጨምሮ ለሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ አገልግሎት የሚውል መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
(የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከሰምንታት በፊት በአዳማ ከተማ ተከስቶ የነበረውን አለመረጋጋት ወደ ሰላማዊ መንገድ ለመመለስ የከተማው አስተዳደርና ህብረተሰቡ በጋራ በመሆን በአዳማ ከተማ የእርቅ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡
የከተማዋ ከንቲባ አቶ አሰግድ ጌታቸው እንደተናገሩት ከባህላችን ውጪ በሆነ መንገድ የተፈጠረው ነገር ማንም የተጠቀመ የለም ያሉ ሲሆን የከተማዋን ፀጥታ ለማደፍረስ የሚሰሩትን ከዚህ በኀላ ዝም ብለን አንመለከትም ብለዋል፡፡ አቶ አሰግድ አክለውም ከሁሉም ብሔሮች ጋር ተከባብረን ተደጋግፈን ለሀገራችን ለውጥ በአንድነት መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የሃይማኖት አባቶችም የአዳማ ህዝብና የኦሮሞ ህዝብ አቃፊና የሰላም ምሳሌ እንደሆነ ገልጸው በሰላም መኖር ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የከተማዋ ከንቲባ አቶ አሰግድ ጌታቸው እንደተናገሩት ከባህላችን ውጪ በሆነ መንገድ የተፈጠረው ነገር ማንም የተጠቀመ የለም ያሉ ሲሆን የከተማዋን ፀጥታ ለማደፍረስ የሚሰሩትን ከዚህ በኀላ ዝም ብለን አንመለከትም ብለዋል፡፡ አቶ አሰግድ አክለውም ከሁሉም ብሔሮች ጋር ተከባብረን ተደጋግፈን ለሀገራችን ለውጥ በአንድነት መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የሃይማኖት አባቶችም የአዳማ ህዝብና የኦሮሞ ህዝብ አቃፊና የሰላም ምሳሌ እንደሆነ ገልጸው በሰላም መኖር ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ብልፅግና ፓርቲና የ‹ባለ አደራ መንግሥት›...
ሕወሓት፤ ብልፅግና ፓርቲ በ2012 ዓ/ም እንደሚደረግ ከሚጠበቀው አገር ዐቀፍ ምርጫ በፊት ከተመሰረተ ኢትዮጵያ በባለ አደራ መንግሥት መመራት አለባት አለ፡፡ ከቀናት በፊት ሊቀመንበሩ ደብረፂዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ብልፅግና ፓርቲን መመስረቱም ሆነ ኢሕአዴግን የማፍረሱ ሒደት ሕጋዊ መንገዱን አልተከተለም በሚል ኢትዮጵያ ከምርጫ በፊት በባለ አደራ ልትመራ ትገደዳለች ማለታቸው ይታወሳል፡፡
በተመሳሳይ ኅዳር 18 ምሽት በትግራይ ቴሌቪዥን ቆይታ የነበራቸው የሕወሓት እና ኢሕአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ጌታቸው ረዳ ይህንኑ ሀሳብ ደግመውታል፡፡
ኢሕአዴግ አራቱን ብሔራዊ ድርጅቶች የማፍረስ ስልጣን አልተሰጠውም የሚሉት ጌታቸው፤ በሐዋሳው ጉባኤ ሀላፊነቱ ተሰጥቶታል የሚባለው #ውሸት ነው ሲሉ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡
‹‹ብልፅግና ፓርቲ ውኅድ ሳይሆን አዲስ ፓርቲ ነው በማለትም›› ብልፅግናን መስርተው አሁን ባለው የመንግሥትነት ቦታ እንቀጥላለን ካሉ፤ ያን ጊዜ ሕግ የሚፈታው ጉዳይ ይሆናልም ብለዋል፡፡ በመሆኑም ብልፅግና ፓርቲ ኢህአዴግን መውረስ አይችልም፤ የብልፅግና ፓርቲ እየሄደበት ያለው ሂደትም ጨፍላቂ ነው ሲሉ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡ በአንጻሩ ብልፅግና ፓርቲ ሕጋዊ ሂደቶችን ተከትሎና ኢሕአዴግን አዋኅዶ እየተፈጠረ መሆኑን በተደጋጋሚ የሚናገሩት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ዐቢይ አሕመድ፤ አዲሱ ውህድ ፓርቲ እውነተኛ ፌደራሊዝምን የሚተገብር እንጂ ጨፍላቂ አይደለም ሲሉ ይደመጣሉ፡፡
(አሃዱ ቴሌቪዥን)
@tikvahethiopia @tikvahethipiaBpt
ሕወሓት፤ ብልፅግና ፓርቲ በ2012 ዓ/ም እንደሚደረግ ከሚጠበቀው አገር ዐቀፍ ምርጫ በፊት ከተመሰረተ ኢትዮጵያ በባለ አደራ መንግሥት መመራት አለባት አለ፡፡ ከቀናት በፊት ሊቀመንበሩ ደብረፂዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ብልፅግና ፓርቲን መመስረቱም ሆነ ኢሕአዴግን የማፍረሱ ሒደት ሕጋዊ መንገዱን አልተከተለም በሚል ኢትዮጵያ ከምርጫ በፊት በባለ አደራ ልትመራ ትገደዳለች ማለታቸው ይታወሳል፡፡
በተመሳሳይ ኅዳር 18 ምሽት በትግራይ ቴሌቪዥን ቆይታ የነበራቸው የሕወሓት እና ኢሕአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ጌታቸው ረዳ ይህንኑ ሀሳብ ደግመውታል፡፡
ኢሕአዴግ አራቱን ብሔራዊ ድርጅቶች የማፍረስ ስልጣን አልተሰጠውም የሚሉት ጌታቸው፤ በሐዋሳው ጉባኤ ሀላፊነቱ ተሰጥቶታል የሚባለው #ውሸት ነው ሲሉ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡
‹‹ብልፅግና ፓርቲ ውኅድ ሳይሆን አዲስ ፓርቲ ነው በማለትም›› ብልፅግናን መስርተው አሁን ባለው የመንግሥትነት ቦታ እንቀጥላለን ካሉ፤ ያን ጊዜ ሕግ የሚፈታው ጉዳይ ይሆናልም ብለዋል፡፡ በመሆኑም ብልፅግና ፓርቲ ኢህአዴግን መውረስ አይችልም፤ የብልፅግና ፓርቲ እየሄደበት ያለው ሂደትም ጨፍላቂ ነው ሲሉ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡ በአንጻሩ ብልፅግና ፓርቲ ሕጋዊ ሂደቶችን ተከትሎና ኢሕአዴግን አዋኅዶ እየተፈጠረ መሆኑን በተደጋጋሚ የሚናገሩት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ዐቢይ አሕመድ፤ አዲሱ ውህድ ፓርቲ እውነተኛ ፌደራሊዝምን የሚተገብር እንጂ ጨፍላቂ አይደለም ሲሉ ይደመጣሉ፡፡
(አሃዱ ቴሌቪዥን)
@tikvahethiopia @tikvahethipiaBpt
"የሀዋሳ ጉባኤ ውህደቱን እንዲያስፈፅም ለኢህአዴግ ምክር ቤት ውክልና ሰጥቶታል የሚባለው፣ ንፁህ ውሸት ነው!"- አቶ ጌታቸው ረዳ
"ኢህአዴግን ለማፍረስ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ቢንስ ሶስቱ የግምባሩ ድርጅቶች ሌላ ነገር ነው የምንፈልገው ብለው ቢያንስ አቋማቸው ስለገለፁ ፣ ቢያንስ በአመራር ደረጃ ማለት ነው፤ ስለዚህ ኢህአዴግን ለማፍረስ የሚያስችሉ መስፈርቶች ይነስም ይብዛም የተሟሉ ነው የሚመስለው፡፡ ፖለቲካሊ ማለቴ ነው፡፡ በፖለቲካ ደረጃ የኢአዴግ አባል ድርጅቶች ፍላጎት ሲኖራቸው ነው ኢህአዴግ ሊኖር የሚችለው፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ እንደ ግምባር ሊቀጥል የሚችልበት እድል አባል ድርጅቶቹ እንዲቀጥል ሲፈልጉ ነው፡፡ ስለዚህ እንዲቀጥል አንፈልግም የሚል እምነት የሚያረጋግጥ የሚመስል ውሳኔዎች ቢያንስ በአመራሮቹ ደረጃ ወስነዋል። ቢሆንም ኢህአዴግን የማፍረስ ሂደት በህግ ማለቅ የሚኖሩባቸውን ጉዳዮች እስኪማሉ ድረስ ቴክኒካሊ ፈርሰዋል ለማለት ግን አይቻልም፡፡ ያው ፍቺ ሲፈርስ የጋራ ሀብት፣ ንብረት የመከፈል ጉዳይ ስለሚኖር።
More👇
https://telegra.ph/TPLF-11-29
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ኢህአዴግን ለማፍረስ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ቢንስ ሶስቱ የግምባሩ ድርጅቶች ሌላ ነገር ነው የምንፈልገው ብለው ቢያንስ አቋማቸው ስለገለፁ ፣ ቢያንስ በአመራር ደረጃ ማለት ነው፤ ስለዚህ ኢህአዴግን ለማፍረስ የሚያስችሉ መስፈርቶች ይነስም ይብዛም የተሟሉ ነው የሚመስለው፡፡ ፖለቲካሊ ማለቴ ነው፡፡ በፖለቲካ ደረጃ የኢአዴግ አባል ድርጅቶች ፍላጎት ሲኖራቸው ነው ኢህአዴግ ሊኖር የሚችለው፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ እንደ ግምባር ሊቀጥል የሚችልበት እድል አባል ድርጅቶቹ እንዲቀጥል ሲፈልጉ ነው፡፡ ስለዚህ እንዲቀጥል አንፈልግም የሚል እምነት የሚያረጋግጥ የሚመስል ውሳኔዎች ቢያንስ በአመራሮቹ ደረጃ ወስነዋል። ቢሆንም ኢህአዴግን የማፍረስ ሂደት በህግ ማለቅ የሚኖሩባቸውን ጉዳዮች እስኪማሉ ድረስ ቴክኒካሊ ፈርሰዋል ለማለት ግን አይቻልም፡፡ ያው ፍቺ ሲፈርስ የጋራ ሀብት፣ ንብረት የመከፈል ጉዳይ ስለሚኖር።
More👇
https://telegra.ph/TPLF-11-29
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Ethiopian Airlines 🛫 ደምቢ ዶሎ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከታህሳስ 7 ጀምሮ በሳምንት ሁለት ቀን ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ ደምቢ ዶሎ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታውቋል።
(የኢትዮጵያ አየር መንገድ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከታህሳስ 7 ጀምሮ በሳምንት ሁለት ቀን ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ ደምቢ ዶሎ የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታውቋል።
(የኢትዮጵያ አየር መንገድ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለሦስት የመንግስት የስራ ኃላፊነት ቦታዎች ሹመት ሰጡ!
ጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት ለኢቲቪ በላከው ደብዳቤ እንዳስታወቀው፦
1. አቶ አህመድ ቱሣ የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣
2. ዶ/ር አለሙ ስሜ በሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል ዘርፍ አስተባባሪ፣
3. አቶ አወሉ አብዲ በሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ላይ ተመድበዋል፡፡
ተሿሚዎቹ ከህዳር 18 ቀን 2012 ጀምሮ በተጠቀሱት የስራ ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተመድበዋል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት ለኢቲቪ በላከው ደብዳቤ እንዳስታወቀው፦
1. አቶ አህመድ ቱሣ የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣
2. ዶ/ር አለሙ ስሜ በሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል ዘርፍ አስተባባሪ፣
3. አቶ አወሉ አብዲ በሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ላይ ተመድበዋል፡፡
ተሿሚዎቹ ከህዳር 18 ቀን 2012 ጀምሮ በተጠቀሱት የስራ ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተመድበዋል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኢራቁ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣናቸውን ሊለቁ ነው!
ጸረ-መንግሥት ተቃውሞ በናጣት ኢራቅ ጠቅላይ ሚንሥትር አደል አብደል ማኅዲ ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ ዛሬ ዐስታወቁ። ጠቅላይ ሚንሥትሩ በጽሑፍ ባሰራጩት መግለጫ ለሀገሪቱ ምክር ቤት የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን በይፋ እንደሚያስገቡ ገልጠዋል። የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄው ኢራቅ ውስጥ የጸጥታ ኃይላት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ ተኩሰው ቢያንስ ዐርባ ሰዎችን በገደሉ ማግስት ነው። የሀገሪቱ የሺዓ እምነት ከፍተኛ ባለሥልጣን ዓሊ ኧል ሲስታኒ ለመንግሥት የሚያደርጉት ድጋፍን «እንደሚያጤኑበት» ለምክር ቤቱ ዛሬ ቀደም ብለው ዐስታውቀው ነበር። ጠቅላይ ሚንሥትር አደል አብደል ማኅዲ ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ በመግለጣቸው በርካታ ተቃዋሚዎች መዲናዪቱ ባግዳድ ወደ ሚገኘው ታኅሪር አደባባይ በብዛት በመሰባሰብ ደስታቸውን ገልጠዋል።
(የጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopia @tsegabwolde
ጸረ-መንግሥት ተቃውሞ በናጣት ኢራቅ ጠቅላይ ሚንሥትር አደል አብደል ማኅዲ ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ ዛሬ ዐስታወቁ። ጠቅላይ ሚንሥትሩ በጽሑፍ ባሰራጩት መግለጫ ለሀገሪቱ ምክር ቤት የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን በይፋ እንደሚያስገቡ ገልጠዋል። የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄው ኢራቅ ውስጥ የጸጥታ ኃይላት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ ተኩሰው ቢያንስ ዐርባ ሰዎችን በገደሉ ማግስት ነው። የሀገሪቱ የሺዓ እምነት ከፍተኛ ባለሥልጣን ዓሊ ኧል ሲስታኒ ለመንግሥት የሚያደርጉት ድጋፍን «እንደሚያጤኑበት» ለምክር ቤቱ ዛሬ ቀደም ብለው ዐስታውቀው ነበር። ጠቅላይ ሚንሥትር አደል አብደል ማኅዲ ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ በመግለጣቸው በርካታ ተቃዋሚዎች መዲናዪቱ ባግዳድ ወደ ሚገኘው ታኅሪር አደባባይ በብዛት በመሰባሰብ ደስታቸውን ገልጠዋል።
(የጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopia @tsegabwolde
አቶ ለማ መገርሳ በመደመር ፍልስፍና እንደማይስማሙ ገለፁ!
የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር እና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ በመደመር ፍልስፍና ወይም በፓርቲዎች መዋሃድ እንደማይስማሙ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ራድዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልፀዋል፡፡
አቶ ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ምክር ቤት የፓርቲዎችን ውህደት ባፀደቀ ጊዜ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተገኝተው እንደነበር ገለፀው ስለሂደቱ ግን አሁን ማብራራት አልፈልግም ብለዋል፡፡
(VOA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር እና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ በመደመር ፍልስፍና ወይም በፓርቲዎች መዋሃድ እንደማይስማሙ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ራድዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልፀዋል፡፡
አቶ ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ምክር ቤት የፓርቲዎችን ውህደት ባፀደቀ ጊዜ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተገኝተው እንደነበር ገለፀው ስለሂደቱ ግን አሁን ማብራራት አልፈልግም ብለዋል፡፡
(VOA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ለማ መደመርን የተቃወሙበት ምክንያት...
"በአጠቃላይ ከመጀመሪያ ጀምሮ እስከ መጨረሻ የፓርቲዎች መዋሃድን በተመለከተ የተለየ ሃሳብ ነው ያለኝ። ከመጀመሪያው ጀምሮ #የማላምንበት መሆኑን ለስራ አስፈፃሚውና ለሁሉም በስፋት ገልጫለሁ። መዋሃዱ ትክክል አይደለም፤ ከሆነም በችኮላ መሆን የለበትም፤ ወቅቱም አይደለም።"
@tikvahethiopia @tsegabwolde
"በአጠቃላይ ከመጀመሪያ ጀምሮ እስከ መጨረሻ የፓርቲዎች መዋሃድን በተመለከተ የተለየ ሃሳብ ነው ያለኝ። ከመጀመሪያው ጀምሮ #የማላምንበት መሆኑን ለስራ አስፈፃሚውና ለሁሉም በስፋት ገልጫለሁ። መዋሃዱ ትክክል አይደለም፤ ከሆነም በችኮላ መሆን የለበትም፤ ወቅቱም አይደለም።"
@tikvahethiopia @tsegabwolde
የኦሮሞ እና አማራ የምሁራን መድረክ እየተካሄደ ነው!
የኦሮሞ እና አማራ የምሁራን መድረክ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የህዝቦችን ትስስርና የሃገርን አንድነት ለማጠናከር ይመከራል።
ከዚህ በተጨማሪም የሁለቱ ክልል ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ተመሳሳይ የህዝብ ለህዝብና የምሁራን መድረኮች ከዚህ ቀደም መካሄዳቸው ይታወሳል።
ከዚህ ባለፈም በቅርቡ የሁለቱ ክልል ባለሃብቶች እና የወጣቶች የውይይት መድረክ መካሄዱም የሚታወስ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሞ እና አማራ የምሁራን መድረክ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የህዝቦችን ትስስርና የሃገርን አንድነት ለማጠናከር ይመከራል።
ከዚህ በተጨማሪም የሁለቱ ክልል ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ተመሳሳይ የህዝብ ለህዝብና የምሁራን መድረኮች ከዚህ ቀደም መካሄዳቸው ይታወሳል።
ከዚህ ባለፈም በቅርቡ የሁለቱ ክልል ባለሃብቶች እና የወጣቶች የውይይት መድረክ መካሄዱም የሚታወስ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከሀሰተኛ ገፆች ተጠንቀቁ!!
29,000 like ያለው ይህ በEritrean Press ስም መረጃዎችን የሚያሰራጭ ገፅ ሃሰተኛ ነው!!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
29,000 like ያለው ይህ በEritrean Press ስም መረጃዎችን የሚያሰራጭ ገፅ ሃሰተኛ ነው!!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"እንዲህ አዝኜ አላውቅም" - አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ
ሱሌይማን ደደፎ በተባብሩት ዓረብ ኢሚሬቶች ባለ ሙሉ ሥልጣን አምባሳደር፤ የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ "በመደመር ፍልስፍና አልስማማም፤ የኢሕአዴግንም ውሕደት አላምንበትም" ማለታቸውን አሳዝኝ እንደሆነ አስታወቁ።
አቶ ለማ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ቋንቋ ዝግጅት ክፍል በሰጡት ቃለ ምልልስ "ከመጀመሪያው ጀምሮ የፓርቲዎችን መዋሃድ በተመለከተ የማላምንበት መሆኑን ለሥራ አስፈጻሚውና ለሁሉም በስፋት ገልጫለሁ። መዋሃዱ ትክክል አይደለም፤ ከሆነም በችኮላ መሆን የለበትም። ወቅቱ አይደለም" ብለዋል።
አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎም በበኩላቸው አቶ ለማ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ጋር ያላቸውን ልዩነቶች እንደሰሙበት ወቅት አዝነው አንደማያውቁ በቲዊተርና ፌስቡክ ገጾቻቸው ላይ አኑረዋል።
#SBS
@tikvahethiopia @tsegabwolde
ሱሌይማን ደደፎ በተባብሩት ዓረብ ኢሚሬቶች ባለ ሙሉ ሥልጣን አምባሳደር፤ የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ "በመደመር ፍልስፍና አልስማማም፤ የኢሕአዴግንም ውሕደት አላምንበትም" ማለታቸውን አሳዝኝ እንደሆነ አስታወቁ።
አቶ ለማ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ቋንቋ ዝግጅት ክፍል በሰጡት ቃለ ምልልስ "ከመጀመሪያው ጀምሮ የፓርቲዎችን መዋሃድ በተመለከተ የማላምንበት መሆኑን ለሥራ አስፈጻሚውና ለሁሉም በስፋት ገልጫለሁ። መዋሃዱ ትክክል አይደለም፤ ከሆነም በችኮላ መሆን የለበትም። ወቅቱ አይደለም" ብለዋል።
አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎም በበኩላቸው አቶ ለማ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ጋር ያላቸውን ልዩነቶች እንደሰሙበት ወቅት አዝነው አንደማያውቁ በቲዊተርና ፌስቡክ ገጾቻቸው ላይ አኑረዋል።
#SBS
@tikvahethiopia @tsegabwolde