#update ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ⬇️
በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ላይ የሰፈረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ወደ #ጦር ሰፈሩ መሰብሰብ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ።
በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ ያለው ውጥረት የተሞላበት የጦርነት ስሜት ከአሁን በኋላ “በከፍተኛ ሁኔታ” #እንደሚቀንስም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን የተናገሩት የኢትዮጵያን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በቡሬ እና በዛላምበሳ ግንባሮች ያሉ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ በቦሌ አየር ማረፊያ በሰጡት መግለጫ ነው።
“የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ድንበር አካባቢ ላይ #ውጥረት የነበረውን #የጦርነት ስሜት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሶ ወደ ካምፕ በመሰብሰብ የሚያገግምበት፣ የሚሰለጥንበት፣ ራሱን የሚያበቃበት ሁኔታ ይፈጠራል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ።
ምንጭ፦ Dw Amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ላይ የሰፈረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ወደ #ጦር ሰፈሩ መሰብሰብ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ።
በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ ያለው ውጥረት የተሞላበት የጦርነት ስሜት ከአሁን በኋላ “በከፍተኛ ሁኔታ” #እንደሚቀንስም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን የተናገሩት የኢትዮጵያን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በቡሬ እና በዛላምበሳ ግንባሮች ያሉ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ በቦሌ አየር ማረፊያ በሰጡት መግለጫ ነው።
“የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ድንበር አካባቢ ላይ #ውጥረት የነበረውን #የጦርነት ስሜት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሶ ወደ ካምፕ በመሰብሰብ የሚያገግምበት፣ የሚሰለጥንበት፣ ራሱን የሚያበቃበት ሁኔታ ይፈጠራል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ።
ምንጭ፦ Dw Amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት በሲዳማ ዞን ለሚገኙ ከተሞችና ወረዳዎች!
📣ትኩረት #ይርጋለም #አለታ_ወንዶ #ጩኮ #ለኩ #ሀገረ_ሰላም በሚባሉ ከተሞች የሚገኙ ዜጎች አሁንም ያለው ሁኔታና አለመረጋጋት እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። በአንዳንድ ከተሞች ክቡር የሆነው የሰው ህይወት ጠፍቷል። ዝርፊያ ተፈፅሟል፤ ሰዎች ህይወታቸውን ሙሉ ለፍተው ያፈሩት ንብረት ወድሞባቸዋል። መልዕክታቸውን ለTIKVAH-ETH በስልክ #ደውለው የተናገሩት የየከተሞቹ ነዋሪዎች የሚመለከተው አካል በሙሉ ከዚህ የከፋ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ሁኔታዎችን ተቆጣጥሮ #እንዲያረጋጋ ተማፅነዋል። ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አስፈሪ ነው፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀገር ሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን...ሌሎችም ለሀገር እና ወገን ተቆርቋሪዎች ወጣቱን በመምከር፣ በማረጋጋት ከጥፋት በመመለስ በኩል ሀገራዊ #ሃላፊነታቸው ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል...
ሀዋሳ ከተማ #የጦርነት_አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። በዚህ ፈታኝ ወቅት ሀገሪቱን ወደማያባራ ግጭት ውስጥ እድትገባ ፅኑ ፍላጎት ያላቸው የፌስቡክ አርበኞች በመኖራቸው የምንሰማቸውን መረጃዎች #በደንብ ልናጣራ እና ልንመረምራቸው ይገባል።
🚫📱💻በሲዳማ ዞን እና ዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት እንደተቋረጠ ነው። ከየከተሞቹ ነዋሪዎች በስልክ የሚደርሱኝን የተጣሩ መረጃዎች ወደናተ የማደርስ ይሆናል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
📣ትኩረት #ይርጋለም #አለታ_ወንዶ #ጩኮ #ለኩ #ሀገረ_ሰላም በሚባሉ ከተሞች የሚገኙ ዜጎች አሁንም ያለው ሁኔታና አለመረጋጋት እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። በአንዳንድ ከተሞች ክቡር የሆነው የሰው ህይወት ጠፍቷል። ዝርፊያ ተፈፅሟል፤ ሰዎች ህይወታቸውን ሙሉ ለፍተው ያፈሩት ንብረት ወድሞባቸዋል። መልዕክታቸውን ለTIKVAH-ETH በስልክ #ደውለው የተናገሩት የየከተሞቹ ነዋሪዎች የሚመለከተው አካል በሙሉ ከዚህ የከፋ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ሁኔታዎችን ተቆጣጥሮ #እንዲያረጋጋ ተማፅነዋል። ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አስፈሪ ነው፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀገር ሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን...ሌሎችም ለሀገር እና ወገን ተቆርቋሪዎች ወጣቱን በመምከር፣ በማረጋጋት ከጥፋት በመመለስ በኩል ሀገራዊ #ሃላፊነታቸው ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል...
ሀዋሳ ከተማ #የጦርነት_አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። በዚህ ፈታኝ ወቅት ሀገሪቱን ወደማያባራ ግጭት ውስጥ እድትገባ ፅኑ ፍላጎት ያላቸው የፌስቡክ አርበኞች በመኖራቸው የምንሰማቸውን መረጃዎች #በደንብ ልናጣራ እና ልንመረምራቸው ይገባል።
🚫📱💻በሲዳማ ዞን እና ዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት እንደተቋረጠ ነው። ከየከተሞቹ ነዋሪዎች በስልክ የሚደርሱኝን የተጣሩ መረጃዎች ወደናተ የማደርስ ይሆናል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia