TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ⬇️

በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ላይ የሰፈረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ወደ #ጦር ሰፈሩ መሰብሰብ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ።

በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ ያለው ውጥረት የተሞላበት የጦርነት ስሜት ከአሁን በኋላ “በከፍተኛ ሁኔታ” #እንደሚቀንስም ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን የተናገሩት የኢትዮጵያን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በቡሬ እና በዛላምበሳ ግንባሮች ያሉ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ በቦሌ አየር ማረፊያ በሰጡት መግለጫ ነው።

“የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ድንበር አካባቢ ላይ #ውጥረት የነበረውን #የጦርነት ስሜት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሶ ወደ ካምፕ በመሰብሰብ የሚያገግምበት፣ የሚሰለጥንበት፣ ራሱን የሚያበቃበት ሁኔታ ይፈጠራል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ።

ምንጭ፦ Dw Amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia