TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢንተርን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተር ሀኪሞች ከስራ ሰዓትና ክፍያ ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ኢንተርን ሀኪሞቹ ምን አሉ ? “ ከጥቂት ዓመታት በፊት የሆስፒታሉ የኢንተርን ሀኪሞች የሥራ ሰዓት ወደ 24 ሰዓታት ዝቅ እንዲል ተደርጎ ነበር። ነገር ግን የኮሌጁ ግለሰብ / #ዳይሬክተር ሲቀየር በራሱ ውሳኔ የራሱን መላምት በመፍጠር መልሶ ወደ 36 ሰዓታት ከፍ አድርጎታል።…
#ኢንተርን #UoG
“ በኢንተርን ምዘና የተጻፈ መስፈርት የለም ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተርን ሀኪሞች
“ ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” - ዩኒቨርሲቲው
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2016/17 ዓ/ም ኢንተርን ሀኪሞች ፦
- በኢንተርንሽፕ ምን ያህል መስራትና መማር እንዳለብን፣
- ምን መስራትና ምን እውቀት ማምጣት እንዳለብን፣
- በኢንተርን ምዘና የተፃፈ ሰዓትና መስፈርት ባለመኖሩ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎቲው ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ለህክምና መስጫ ተረኛ አዳሪ እረፍት (Day off) እንዲሰጣቸው ኢንተርን ከመጀመራቸው ከሳምነት በፊት በደብዳቤ በመጠየቃቸው የ3 ወራት ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
“ ሥራ ከመጀመራችን ከ3 ቀናት በፊት በሥራና ትምህርት ገበታችን ላይ እንደማንገኝ በደብዳቤ አሳውቀን ከትምህርት ገበታችን ሳንገኝ ቀርተናል ” ብለው ፣ በዚህም የ3 ወራት ደመወዛቸው እንደተቆረጠና ሥራ ቢጀምሩም እንዳልተከፈላቸው አስረድተዋል።
ለተከታታይ 34 ሰዓታት ያለ እረፍት መስራት፣ በሳምንት ከ90 - 94 ሰዓታት መስራት፣ አለፍ ሲልም እስከ 118 ሰዓታት በመስራት አስቸጋሪና ከአቅም በላይ የሆነው አሰራር ካልተቀየረ፦
📌 የአእምሮ መዛል፣ የመንፈስ መቃወስ የሚስከትል
📌 የህክምና ስህተት የሚፈጥር
📌 ከሥራ በቂ እውቀት የማያስገኝ
📌 የእኩልነት መብት የሚጥስ መሆኑን በማስረዳት ሥራና ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት ጠይቀው በሥራ ጫናና በሌሎች ምክንያቶቾ ጥያቄውን ክትትል ሳያደርጉበት እንደቆዩ አስረድተዋል።
“ ሆኖም ግን በጥያቄው ዙሪያ ተወያይተን መፍትሄ እናገኛለን ብለን ስንጠብቅ ቅጣት ተጣለብን ” ብለው፣ ለ4 ቀናት ከቆዩ በኋላ ወደ ሥራ ገበታ ቢመለሱም የ3 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።
የኢንተርን ምዘና መስፈርቱን፣ የሥራና መማሪያ ሰዓት ገደብ አለመቀመጡን በተመለከተ ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ የጠየቅናቸው የጤና ሳይንሱ አካል ዶክተር ሙሉጌታ፣ “ ይህን ጥያቄ ካላቸው ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” ብለዋል።
“ ተገቢ ዶክሜንት አለ። ስርዓተ ትምህርቱ አለ። ይህን የሚያስፈጽሙ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች አሉ። በእነርሱ በኩል መልስ እንሰጣለን ” ሲሉ አክለዋል።
የደመወዝ መቆረጡን በተመለከተ በሰጡት ቃልም፣ “ ነገሩን ለማሳጠር ያህል ባለፈው ዶክተር አይንሸት የሰጠው መልስ ተገቢ ነው። የተለዬ መልስ ተጨማሪ መረጃ የለኝም ” ነው ያሉት።
ዶ/ር አይንሸት የደመወዝ ቅሬታውን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ የኢንተርን ሀኪሞቹ ጥያቄ አቀራረብ ልክ ባለመሆኑ የ3 ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ገልጸው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በኢንተርን ምዘና የተጻፈ መስፈርት የለም ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተርን ሀኪሞች
“ ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” - ዩኒቨርሲቲው
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2016/17 ዓ/ም ኢንተርን ሀኪሞች ፦
- በኢንተርንሽፕ ምን ያህል መስራትና መማር እንዳለብን፣
- ምን መስራትና ምን እውቀት ማምጣት እንዳለብን፣
- በኢንተርን ምዘና የተፃፈ ሰዓትና መስፈርት ባለመኖሩ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎቲው ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ለህክምና መስጫ ተረኛ አዳሪ እረፍት (Day off) እንዲሰጣቸው ኢንተርን ከመጀመራቸው ከሳምነት በፊት በደብዳቤ በመጠየቃቸው የ3 ወራት ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
“ ሥራ ከመጀመራችን ከ3 ቀናት በፊት በሥራና ትምህርት ገበታችን ላይ እንደማንገኝ በደብዳቤ አሳውቀን ከትምህርት ገበታችን ሳንገኝ ቀርተናል ” ብለው ፣ በዚህም የ3 ወራት ደመወዛቸው እንደተቆረጠና ሥራ ቢጀምሩም እንዳልተከፈላቸው አስረድተዋል።
ለተከታታይ 34 ሰዓታት ያለ እረፍት መስራት፣ በሳምንት ከ90 - 94 ሰዓታት መስራት፣ አለፍ ሲልም እስከ 118 ሰዓታት በመስራት አስቸጋሪና ከአቅም በላይ የሆነው አሰራር ካልተቀየረ፦
📌 የአእምሮ መዛል፣ የመንፈስ መቃወስ የሚስከትል
📌 የህክምና ስህተት የሚፈጥር
📌 ከሥራ በቂ እውቀት የማያስገኝ
📌 የእኩልነት መብት የሚጥስ መሆኑን በማስረዳት ሥራና ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት ጠይቀው በሥራ ጫናና በሌሎች ምክንያቶቾ ጥያቄውን ክትትል ሳያደርጉበት እንደቆዩ አስረድተዋል።
“ ሆኖም ግን በጥያቄው ዙሪያ ተወያይተን መፍትሄ እናገኛለን ብለን ስንጠብቅ ቅጣት ተጣለብን ” ብለው፣ ለ4 ቀናት ከቆዩ በኋላ ወደ ሥራ ገበታ ቢመለሱም የ3 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።
የኢንተርን ምዘና መስፈርቱን፣ የሥራና መማሪያ ሰዓት ገደብ አለመቀመጡን በተመለከተ ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ የጠየቅናቸው የጤና ሳይንሱ አካል ዶክተር ሙሉጌታ፣ “ ይህን ጥያቄ ካላቸው ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” ብለዋል።
“ ተገቢ ዶክሜንት አለ። ስርዓተ ትምህርቱ አለ። ይህን የሚያስፈጽሙ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች አሉ። በእነርሱ በኩል መልስ እንሰጣለን ” ሲሉ አክለዋል።
የደመወዝ መቆረጡን በተመለከተ በሰጡት ቃልም፣ “ ነገሩን ለማሳጠር ያህል ባለፈው ዶክተር አይንሸት የሰጠው መልስ ተገቢ ነው። የተለዬ መልስ ተጨማሪ መረጃ የለኝም ” ነው ያሉት።
ዶ/ር አይንሸት የደመወዝ ቅሬታውን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ የኢንተርን ሀኪሞቹ ጥያቄ አቀራረብ ልክ ባለመሆኑ የ3 ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ገልጸው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😡420❤106😭36🙏28😢15👏11😱11🕊10🤔8🥰4
#UoG
🚨 " አሁንም በርካታ የታመሙ ተማሪዎች ወደ ህክምና ተቋሙ እየሄዱ ነው "- ተማሪዎች
➡️ " በሽታው የተከሰተው ከምግብ ወይም ከውሃ ጋር የተያያዘ መሆኑን ገና እየተጣራ ነው " - አብርሃም ዘገየ የተማሪዎች ዲን
በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክሊቲ ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች መታመማቸውን ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከባለፈው እሮብ ጀምሮ በግቢው " በውሃና በምግብ ብክለት ነው " ብለው በጠረጠሩት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች መታመማቸውን ህክምና ላይ ያሉ ተማሪዎች አመልክተዋል።
ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁን በግቢው ተማሪ መሆናቸውን እና አሁን በህክምና ላይ መሆናቸውን የገለፁልን ተማሪዎች ግቢው ውስጥ ባለው የህክምና ተቋም በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች እየታከሙ መሆኑን ገልፀዋል።
ለተሻለ ህክምናም ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የተላኩ እንዳሉም ተማሪዎች ተናግረዋል።
በግቢው የአምስተኛ ዓመት ተማሪ እንደሆነ የነገረን ተማሪ ባለፈው እሮብ ምሳ ላይ የተመገቡት ፓስታ እርሱን ጨምሮ በርካቶችን ለህመም እንደዳረጋቸው ይጠረጥራል።
የትኩሳት፣ የተቅማጥ እና እጅና እግር የመቆረጣጠም ምልክት እንዳለው የሚናገሩት ታማሚዎች ወደ ህክምና ተቋም የሄዱ ተማሪዎች በሙሉ " ታይፎድ " ነው እንደተባሉ ተማሪው ተናግሯል።
ሌላው የሶስተኛ አመት የኤሌክትሪካል እንጂነሪንግ ተማሪ መሆኑን የነገረንና ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን ተማሪ ደግሞ ምግቡ፤ የሚጠጣው ውኃም ተበርዟል ይላል። ህክምና ተደርጎለት መድሃኒት እየወሰደ እንደሆነ የሚናገረው ይህ ተማሪ የውሃ እጥረት በግቢው ስር የሰደደ ችግር ነው ብሏል።
ከየት እንደሚመጣ የማይታውቅ ውኃ በቦቴ ተጭኖ ይመጣል በጥራቱ ሁሌ እንጠራጠር ነበር። በተለይ ሰሞኑን ከተማሪዎች መታመም ጋር በተያያዘ አብዛኛው ተማሪ የታሸገ ውሃ ገዝቶ እየጠጣ ይገኛል ብሏል።
ተማሪዎቹ ለተማሪዎች ህብረት ተወካይ ችግሩን ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።
የኢንጅነሪግ ተማሪዎች ብቻ በሚማሩበት በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳት የሆነውን ተማሪ ተመስገን ችግሩ መከሰቱንና እርሱን ጨምሮ በርከት ያሉ ተማሪዎች መታመማቸውን ገልጾ፥ ችግሩ ከውሃው ነው በመባሉ ትላንት በታንከሩ ያለው ውሃ ተቀይሮ በኬሚካል በታከመ ውሃ መቀየሩን ተናግሯል።
በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ዲን አብርሃም ዘገየ በግቢው ከመቶ በላይ ተማሪዎች ወደ ክሊኒክ ታመው መሄዳቸውን ጠቅሰው ከመጡት ውስጥ 84 ተማሪዎች ብቻ " ባክቴሪያ " ተገኝቶባቸው መድሃኒት ተሰጥቶቸው እያገገሙ ነው ብለዋል።
ከዚህ ህመም ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የሄዱት ከ5 እንደማይበልጡና ከእነዚህ ውስጥ ተጏዳኝ የጨጏራና ሌሎች ችግሮች ያለባቸው ናቸው ተብለው ታክመው የተመለሱ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።
ቀለል ያለ ስሜት ላላቸው ተማሪዎችም ኦ አር ኤስ እየተሰጣቸው ነው፤ ከዩንቨርስቲው አመራር ጋር በመሆን የመድሃኒት ችግር እንዳያጋጥምም ወደ ክሊንኩ አስገብተናል ያሉት አብርሃም የውሃና የምግብ ችግር ነው የሚለውን ምክንያት #እየተጣራ ነው ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar
@tikvahethiopia
🚨 " አሁንም በርካታ የታመሙ ተማሪዎች ወደ ህክምና ተቋሙ እየሄዱ ነው "- ተማሪዎች
➡️ " በሽታው የተከሰተው ከምግብ ወይም ከውሃ ጋር የተያያዘ መሆኑን ገና እየተጣራ ነው " - አብርሃም ዘገየ የተማሪዎች ዲን
በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክሊቲ ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች መታመማቸውን ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከባለፈው እሮብ ጀምሮ በግቢው " በውሃና በምግብ ብክለት ነው " ብለው በጠረጠሩት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች መታመማቸውን ህክምና ላይ ያሉ ተማሪዎች አመልክተዋል።
ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁን በግቢው ተማሪ መሆናቸውን እና አሁን በህክምና ላይ መሆናቸውን የገለፁልን ተማሪዎች ግቢው ውስጥ ባለው የህክምና ተቋም በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች እየታከሙ መሆኑን ገልፀዋል።
ለተሻለ ህክምናም ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የተላኩ እንዳሉም ተማሪዎች ተናግረዋል።
በግቢው የአምስተኛ ዓመት ተማሪ እንደሆነ የነገረን ተማሪ ባለፈው እሮብ ምሳ ላይ የተመገቡት ፓስታ እርሱን ጨምሮ በርካቶችን ለህመም እንደዳረጋቸው ይጠረጥራል።
የትኩሳት፣ የተቅማጥ እና እጅና እግር የመቆረጣጠም ምልክት እንዳለው የሚናገሩት ታማሚዎች ወደ ህክምና ተቋም የሄዱ ተማሪዎች በሙሉ " ታይፎድ " ነው እንደተባሉ ተማሪው ተናግሯል።
ሌላው የሶስተኛ አመት የኤሌክትሪካል እንጂነሪንግ ተማሪ መሆኑን የነገረንና ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን ተማሪ ደግሞ ምግቡ፤ የሚጠጣው ውኃም ተበርዟል ይላል። ህክምና ተደርጎለት መድሃኒት እየወሰደ እንደሆነ የሚናገረው ይህ ተማሪ የውሃ እጥረት በግቢው ስር የሰደደ ችግር ነው ብሏል።
ከየት እንደሚመጣ የማይታውቅ ውኃ በቦቴ ተጭኖ ይመጣል በጥራቱ ሁሌ እንጠራጠር ነበር። በተለይ ሰሞኑን ከተማሪዎች መታመም ጋር በተያያዘ አብዛኛው ተማሪ የታሸገ ውሃ ገዝቶ እየጠጣ ይገኛል ብሏል።
ተማሪዎቹ ለተማሪዎች ህብረት ተወካይ ችግሩን ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።
የኢንጅነሪግ ተማሪዎች ብቻ በሚማሩበት በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳት የሆነውን ተማሪ ተመስገን ችግሩ መከሰቱንና እርሱን ጨምሮ በርከት ያሉ ተማሪዎች መታመማቸውን ገልጾ፥ ችግሩ ከውሃው ነው በመባሉ ትላንት በታንከሩ ያለው ውሃ ተቀይሮ በኬሚካል በታከመ ውሃ መቀየሩን ተናግሯል።
በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ዲን አብርሃም ዘገየ በግቢው ከመቶ በላይ ተማሪዎች ወደ ክሊኒክ ታመው መሄዳቸውን ጠቅሰው ከመጡት ውስጥ 84 ተማሪዎች ብቻ " ባክቴሪያ " ተገኝቶባቸው መድሃኒት ተሰጥቶቸው እያገገሙ ነው ብለዋል።
ከዚህ ህመም ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የሄዱት ከ5 እንደማይበልጡና ከእነዚህ ውስጥ ተጏዳኝ የጨጏራና ሌሎች ችግሮች ያለባቸው ናቸው ተብለው ታክመው የተመለሱ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።
ቀለል ያለ ስሜት ላላቸው ተማሪዎችም ኦ አር ኤስ እየተሰጣቸው ነው፤ ከዩንቨርስቲው አመራር ጋር በመሆን የመድሃኒት ችግር እንዳያጋጥምም ወደ ክሊንኩ አስገብተናል ያሉት አብርሃም የውሃና የምግብ ችግር ነው የሚለውን ምክንያት #እየተጣራ ነው ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar
@tikvahethiopia
😭506❤95💔39🙏33🤔25😡21👏17😢15🕊11😱10🥰1
#UoG አንጋፋው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ 4 ቢሊዮን ብር ወጥቶባቸው የተሰሩ 22 ፕሮጀክቶችን እንዳስመረቀ አሳውቋል።
ከነዚህም አንዱ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኘው 510 ሚሊዮን ብር የወጣበት የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከል ሲሆን ማዕከሉ በይፋ ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለካንሰር ታማሚዎች የኬሞ ቴራፒ የሚሰጥ ቢሆንም የጨረር ህክምና አገልግሎት ባለመኖሩ ታካሚዎች ወደ ሌሎች ቦታዎች እየሄዱ እየተቸገሩ ሲታከሙ ነበር።
የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከሉ ፦
- ለክልሉ
- ከቤኒሻንጉል ጉምዝ፣
- ከትግራይ እና ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ታካሚዎች እንዲሁም ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ለሚመጡ ታካሚዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ማዕከሉ ከጅማ፣ ሀረር፣ አዲስ አበባ እና ሀዋሳ በመቀጠል በሀገሪቱ 5ኛው ማዕከል ነው።
ከዚህ ባለፈ የህክምና ኦክስጂን ማምረቻ ፕላትም መመረቁ ተገልጿል።
አንጋፋው ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክቶቹን ያስቅመረቀው ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ፣ ምክትል ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው።
#UoG #AmharaCommu.
@tikvahethiopia
ከነዚህም አንዱ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኘው 510 ሚሊዮን ብር የወጣበት የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከል ሲሆን ማዕከሉ በይፋ ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለካንሰር ታማሚዎች የኬሞ ቴራፒ የሚሰጥ ቢሆንም የጨረር ህክምና አገልግሎት ባለመኖሩ ታካሚዎች ወደ ሌሎች ቦታዎች እየሄዱ እየተቸገሩ ሲታከሙ ነበር።
የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከሉ ፦
- ለክልሉ
- ከቤኒሻንጉል ጉምዝ፣
- ከትግራይ እና ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ታካሚዎች እንዲሁም ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ለሚመጡ ታካሚዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ማዕከሉ ከጅማ፣ ሀረር፣ አዲስ አበባ እና ሀዋሳ በመቀጠል በሀገሪቱ 5ኛው ማዕከል ነው።
ከዚህ ባለፈ የህክምና ኦክስጂን ማምረቻ ፕላትም መመረቁ ተገልጿል።
አንጋፋው ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክቶቹን ያስቅመረቀው ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ፣ ምክትል ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው።
#UoG #AmharaCommu.
@tikvahethiopia
👏907❤709🙏51😡49🤔25🕊15😱9😭6💔5🥰3😢2
#UoG
ጎንደር ዩኒቨርስቲ ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 14 የቀድሞ ምሩቃን ልዩ ዕውቅና ሰጠ !
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለትም በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን 2500 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ምስረታን በትላንትናው ዕለት የፋ ሲያደርግ በዛሬው ዕለት ደግሞ በ13 ዘርፎች ለ14 የቀድሞ ምሩቃን ልዩ ዕውቅና ሰጥቷል።
የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያውን ምረቃ ያካሄደው ሰኔ 30 ቀን 1949 ዓ.ም እንደነበር እና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 66 ዓመታት 107 ሺ 860 ሙህራንን ማፍራቱን አስታውሰዋል።
ከእነዚህ ሙህራን መካከል በ13 ዘርፎች በሙያቸው በጎ ትፅዕኖ የፈጠሩ 14 ሙህራንን ዩንቨርስቲው ዕውቅና ለመስጠት መወሰኑን አስረድተዋል።
ጎንደር ዩኒቨርስቲ በምን ዘርፍ ለየትኞቹ የቀድሞ ተመራቂዎች ልዩ ዕውቅና ሰጠ ?
1. የፕሬዚዳንታዊ ሌጋሲ ከፍተኛ ሽልማት ዘርፍ
- ፕ/ር መንገሻ አድማሱ (የቀድሞው የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት)
- ፕ/ር ያሬድ ወንድምኩን (የመጀመሪያው የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት)
2. የማኅበረሰብ ተጽዕኖ የላቀ ሽልማት (Community Award)
- ፕ/ር ብሩክ ላጲሶ
3. ዓለም አቀፋዊ የመሪነት ዘርፍ (Global Leadership Award)
- ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ (የቀድሞ የኢፌዴሪ ጤና ጥበቃ (ጤና) ሚኒስትር
4. ወጣት ሥራ ፈጣሪና ተጽዕኖ ፈጣሪ ዘርፍ
- አቶ ጃለታ ሙላቱ
5. በጎንደር ዩኒቨርስቲ ድጋፍ እና አጋርነት ዘርፍ
- ዶ/ር ካሱ ከተማ
6. በትምህርት እና ምርምር ልኅቀት ዘርፍ
- ዶ/ር ኤርሚያስ ዲኖ
7. በህዝባዊ አገልግሎት ዘርፍ (Public Service Award)
- ዶ/ር ተዋበች ቢሻው (የመጀመሪያዋ ሴት ጤና መኮንን)
8. በህይወት ዘመን አበርክቶ ዘርፍ
- ፕ/ር ጉታ ዘነበ
9. በጤናና ሰብዓዊ አገልግሎት ዘርፍ
- ዶ/ር ፈቀደ አጉዋር
10. በባህል፤ በመገናኛ ብዙኀን እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ
- አቶ ስለሺ ግርማ ( በአሁኑ ወቅት የቱሪዝም ሚኒስትር ሚ/ዴኤታ)
11. በሥራ ፈጠራና ኢንቨስትመንት ዘርፍ
- ዶ/ር ግርማ አባቢ
12. በዲያስፖራ አምባሳደርነት ከፍተኛ ተሸላሚ
- ዶ/ር ኑሩ አብሲኖ
13. ልዩ የሰብዓዊ አገልግሎት ሽልማት (Social Humanitarian Impact Award)
- ወጣት ዳዊት አየነው
እጩዎችን የማሰባሰብ እና ድምጽ የማሰባሰብ ሥራ ተሰርቶ ተሸላሚዎቹ መለየታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamliyBahirdar
@tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርስቲ ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 14 የቀድሞ ምሩቃን ልዩ ዕውቅና ሰጠ !
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለትም በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን 2500 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ምስረታን በትላንትናው ዕለት የፋ ሲያደርግ በዛሬው ዕለት ደግሞ በ13 ዘርፎች ለ14 የቀድሞ ምሩቃን ልዩ ዕውቅና ሰጥቷል።
የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያውን ምረቃ ያካሄደው ሰኔ 30 ቀን 1949 ዓ.ም እንደነበር እና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 66 ዓመታት 107 ሺ 860 ሙህራንን ማፍራቱን አስታውሰዋል።
ከእነዚህ ሙህራን መካከል በ13 ዘርፎች በሙያቸው በጎ ትፅዕኖ የፈጠሩ 14 ሙህራንን ዩንቨርስቲው ዕውቅና ለመስጠት መወሰኑን አስረድተዋል።
ጎንደር ዩኒቨርስቲ በምን ዘርፍ ለየትኞቹ የቀድሞ ተመራቂዎች ልዩ ዕውቅና ሰጠ ?
1. የፕሬዚዳንታዊ ሌጋሲ ከፍተኛ ሽልማት ዘርፍ
- ፕ/ር መንገሻ አድማሱ (የቀድሞው የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት)
- ፕ/ር ያሬድ ወንድምኩን (የመጀመሪያው የዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት)
2. የማኅበረሰብ ተጽዕኖ የላቀ ሽልማት (Community Award)
- ፕ/ር ብሩክ ላጲሶ
3. ዓለም አቀፋዊ የመሪነት ዘርፍ (Global Leadership Award)
- ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ (የቀድሞ የኢፌዴሪ ጤና ጥበቃ (ጤና) ሚኒስትር
4. ወጣት ሥራ ፈጣሪና ተጽዕኖ ፈጣሪ ዘርፍ
- አቶ ጃለታ ሙላቱ
5. በጎንደር ዩኒቨርስቲ ድጋፍ እና አጋርነት ዘርፍ
- ዶ/ር ካሱ ከተማ
6. በትምህርት እና ምርምር ልኅቀት ዘርፍ
- ዶ/ር ኤርሚያስ ዲኖ
7. በህዝባዊ አገልግሎት ዘርፍ (Public Service Award)
- ዶ/ር ተዋበች ቢሻው (የመጀመሪያዋ ሴት ጤና መኮንን)
8. በህይወት ዘመን አበርክቶ ዘርፍ
- ፕ/ር ጉታ ዘነበ
9. በጤናና ሰብዓዊ አገልግሎት ዘርፍ
- ዶ/ር ፈቀደ አጉዋር
10. በባህል፤ በመገናኛ ብዙኀን እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ
- አቶ ስለሺ ግርማ ( በአሁኑ ወቅት የቱሪዝም ሚኒስትር ሚ/ዴኤታ)
11. በሥራ ፈጠራና ኢንቨስትመንት ዘርፍ
- ዶ/ር ግርማ አባቢ
12. በዲያስፖራ አምባሳደርነት ከፍተኛ ተሸላሚ
- ዶ/ር ኑሩ አብሲኖ
13. ልዩ የሰብዓዊ አገልግሎት ሽልማት (Social Humanitarian Impact Award)
- ወጣት ዳዊት አየነው
እጩዎችን የማሰባሰብ እና ድምጽ የማሰባሰብ ሥራ ተሰርቶ ተሸላሚዎቹ መለየታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamliyBahirdar
@tikvahethiopia
❤1.45K🙏108👏61😡42🤔33🕊15😢13💔12🥰11😭5