TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SecurityAlert

www.tikvahethiopia.net

በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጅ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የፀጥታ እና የደህንነት ችግር መኖሩን እያሳወቁን ይገኛሉ።

ታጣቂዎች በሰውና በንብረት ላይ ጥቃት እያደረሱ እንደሆነም ገልፀውልናል።

ጉዳዩ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈልግም አባላቶቻችን ጥሪ አቅርበዋል።

በየአካባቢው ያሉ የፀጥታ እንዲሁም የደህንነት ስጋቶችን በ www.tikvahethiopia.net በኩል ማሳወቅ ትችላላችሁ።

@tikvahethmagazine @tikvahmagBot
#SecurityAlert

በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤማንጂ፣በኖሽ፣ ዶቢ ቀበሌዎች አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንዳለባቸውን የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ እንደነበረ ጠቁመዋል። ስለደረሰው ጉዳት አጣርተው እንደሚያሳውቁን ገልፀዋል።

በተጠቀሱት አካባቢዎች ነዋሪው ቤት ንብረቱን ጥሎ እየሸሸ መሆኑንም አባላቶቻችን መልዕክት አድርሰዋል።

www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢው ያለውን የፀጥታ እንዲሁም ደህንነት ስጋት ልታሳውቁን ትችላላችሁ።

#TikvahFamilyBulenWoreda

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia