TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት

አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መገኘት አስገዳጅ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ከዛሬ ታህሳስ 23 , 2017 ዓ.ም (Jan 1st 2025) ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሆኗል።

በሌላ ተያያዥ መረጃ ...

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ " ፋይዳን ለባንክ አገልግሎት አስገዳጅነት " ትዕዛዝ ወደ ትግበራ መግባት ተከትሎ የተለያዩ ባንኮች የማርኬቲንግ እና ኮርፖሬት ህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ሀላፊዎች ያሳተፈ በጥምረት ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቆናል።

ከኃላፊዎች ጋር በነበረ ውይይት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ ፤ " የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ባንኮች በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን ልክ እንደ አንድ የባንክ አገልግሎት አጽንዖት ተሰጥቶት እንዲሰሩ " ሲሉ አሳስበዋል።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች #DigitalID

@tikvahethiopia
😡1.1K🙏169108👏91🤔39😭38🕊20😢19🥰17😱17
#National_ID_Program

ተጨማሪ የመረጃ ማስተካከያ ጣቢያዎች

የመረጃ ስህተት ሲገጥም እንዲሁም መረጃ መቀየር ቢያስፈልግዎ በአቅራቢያዎ የሚገኝ የመረጃ እድሳት አገልግሎት ሰጪ ጣቢያ መሄድ እንደሚችሉ ያውቃሉ?

እነዚህን እና ተጨማሪ የምዝገባ ጣቢያዎች ለማግኘት id.gov.et/updatecenters ይመልከቱ። ነገር ግን በምዝገባ ቅጽ ላይ የሞሉት መረጃ በመዝጋቢ ባለሙያ በስህተት ከተመዘገበ መረጃዎን ለማስተካከል በአካል መሔድ ሳይጠበቅብዎ id.gov.et/update ላይ ወይም "Fayda ID" የሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በቤትዎ ሆነው የተሳሳተ መረጃዎን እንዲስተካከል መጠየቅ ይችላሉ።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች
272🙏28😡6🥰5👏3🤔2