ኢንዱስትሪ ፓርኮች❓
ለዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር አልመው የተቋቋሙት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከፍተኛ #የሰራተኛ_ፍልሰት እየፈተናቸው ነው ተባለ፡፡ ከቀጠሯቸው ሰራተኞች በሩብ አመት ውስጥ እስከ 98 በመቶ መልሰው የለቀቁባቸው ፓርኮች መኖራቸውን ተሰምቷል፡፡
ለዚህ ዋናው ምክንያት ፓርኮቹ ተመርቀው ስራ ከጀመሩ በኋላ በአካባቢው የቤት ኪራይ በከፍተኛ መጠን #መጨመር ነው ተብሏል፡፡
የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለ3 ተከታታይ አመታት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ያደረገው የክዋኔ ኦዲት ግኝት እንደሚያሳየው በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሰራተኞች ፍልሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው፡፡
እንደ ምሳሌም በቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ ብቻ በ2008 ሩብ አመት ከተቀጠሩ ሰራተኞች 42 ነጥብ 5 በመቶ ለቅቀዋል፡፡
በ2009 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እድል ካገኙት 72 ነጥብ 3 በመቶዎቹ ስራውን ትተው ሄደዋል፡፡
በሶስተኛ አመት 2010 ዓ/ም ከቀደሙት ጊዜ በባሰ ሁኔታ የለቀቁት ሰራተኞች ቁጥር 98 ነጥብ 9 በመቶ መድረሱን የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት ግኝት ያሳያል፡፡
እንዲህ ያለው የሰራተኞች ፍልሰት የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተቋቋሙበት ዋና ዓላማ የሆነውን ለዜጎች የስራ እድል መፍጠርን ሳይሳካ እንዲቀር ያደርገዋል ተብሏል፡፡ የፓርኮቹ ምርታማነትና የወጪ ንግዱ ላይም ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርስ ተነግሯል፡፡
ወሬውን የሰማነው በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የተደረገውን የክዋኔ ኦዲት ግኝትና የተወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎችን በተመለከተ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ጋር ሲመክር ተገኝተን ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ #ሌሊሴ_ነሜ እንዳሉት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ስራ #የሚለቁ ሰራተኞች ቁጥራቸው ከፍተኛ እንዲሆን ያደረገው ዋና ምክንያት የቤት ኪራይ መጨመርና የኑሮ ውድነት ነው ብለዋል፡፡
#የሐዋሳ_ኢንዱስትሪ_ፓርክ ስራ በጀመረ ጊዜ 300 ብር የነበረው የቤት ኪራይ ከ1 ሺህ 100 ብር በላይ ሆኗል ብለዋል፡፡
የኑሮ ውድነቱ ሰራተኛው ፓርኩን ለቆ በተለያዩ የግንባታ ስራዎች ላይ በቀን ሰራተኝነት ለማስራት እንዲመርጥ አድርጎታል ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፡፡ በመሆኑም መንግስት ለጉዳዩ እልባት በመስጠት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስራ በጀመሩ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 45 ሺ ሰራተኞች ተቀጥረው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር አልመው የተቋቋሙት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከፍተኛ #የሰራተኛ_ፍልሰት እየፈተናቸው ነው ተባለ፡፡ ከቀጠሯቸው ሰራተኞች በሩብ አመት ውስጥ እስከ 98 በመቶ መልሰው የለቀቁባቸው ፓርኮች መኖራቸውን ተሰምቷል፡፡
ለዚህ ዋናው ምክንያት ፓርኮቹ ተመርቀው ስራ ከጀመሩ በኋላ በአካባቢው የቤት ኪራይ በከፍተኛ መጠን #መጨመር ነው ተብሏል፡፡
የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለ3 ተከታታይ አመታት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ያደረገው የክዋኔ ኦዲት ግኝት እንደሚያሳየው በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሰራተኞች ፍልሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው፡፡
እንደ ምሳሌም በቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ ብቻ በ2008 ሩብ አመት ከተቀጠሩ ሰራተኞች 42 ነጥብ 5 በመቶ ለቅቀዋል፡፡
በ2009 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እድል ካገኙት 72 ነጥብ 3 በመቶዎቹ ስራውን ትተው ሄደዋል፡፡
በሶስተኛ አመት 2010 ዓ/ም ከቀደሙት ጊዜ በባሰ ሁኔታ የለቀቁት ሰራተኞች ቁጥር 98 ነጥብ 9 በመቶ መድረሱን የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት ግኝት ያሳያል፡፡
እንዲህ ያለው የሰራተኞች ፍልሰት የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተቋቋሙበት ዋና ዓላማ የሆነውን ለዜጎች የስራ እድል መፍጠርን ሳይሳካ እንዲቀር ያደርገዋል ተብሏል፡፡ የፓርኮቹ ምርታማነትና የወጪ ንግዱ ላይም ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርስ ተነግሯል፡፡
ወሬውን የሰማነው በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የተደረገውን የክዋኔ ኦዲት ግኝትና የተወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎችን በተመለከተ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ጋር ሲመክር ተገኝተን ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ #ሌሊሴ_ነሜ እንዳሉት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ስራ #የሚለቁ ሰራተኞች ቁጥራቸው ከፍተኛ እንዲሆን ያደረገው ዋና ምክንያት የቤት ኪራይ መጨመርና የኑሮ ውድነት ነው ብለዋል፡፡
#የሐዋሳ_ኢንዱስትሪ_ፓርክ ስራ በጀመረ ጊዜ 300 ብር የነበረው የቤት ኪራይ ከ1 ሺህ 100 ብር በላይ ሆኗል ብለዋል፡፡
የኑሮ ውድነቱ ሰራተኛው ፓርኩን ለቆ በተለያዩ የግንባታ ስራዎች ላይ በቀን ሰራተኝነት ለማስራት እንዲመርጥ አድርጎታል ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፡፡ በመሆኑም መንግስት ለጉዳዩ እልባት በመስጠት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስራ በጀመሩ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 45 ሺ ሰራተኞች ተቀጥረው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የምርቶች ዋጋ ...
መንግስት በፍራንኮ ቫሉታ ከውጪ እንዲገቡ የፈቀዳቸው ምርቶች ዋጋ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው #መጨመር አሣሣቢ ሆኗል ተባለ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ምርቶቹን በፍራንኮ ቫሉታ እንዲያስገቡ ከተፈቀደላቸው ነጋዴዎች ጋር ውይይት ማድረጉን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።
ዘይት ፣ ስኳር ፤ ሩዝና የህፃናት ወተት በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ የተፈቀዱ ምርቶች መሆናቸው ይታወሳል።
ምርቶቹ በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ በመፈቀዱ ባለፉት አስር ወራት ብቻ መንግስት በታክስ መልክ ማግኘት የነበረበትን ከ10 ቢሊየን ብር በላይ አጥቷል ተብሏል።
ነገር ግን የምርቶቹ ዋጋ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው ሲጨምር እንደሚታይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ድኤታ አቶ ተሻለ በልሁ ተናግረዋል።
ጭማሪው እየታየ ያለዉ በአለም ላይ ዋጋቸው #ቀንሶ ባለበት ወቅት ጭምር ነው ብለዋል።
ምርቶቹ ወደ ሀገር ውስጥ ከገቡ በኋላ ስርጭታቸውም ላይ ብዙ ግልፅነት እንደሌለ ተነግሯል።
እንደ ማሣያም ዘንድሮ በአስር ወራት ወደ ሀገር ውስጥ የገባው የምግብ ዘይት 97 ሚሊየን ሊትር እንደሆነ ተጠቅሷል። አምና በተመሣሣይ ጊዜ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው ግን ከአንድ መቶ ሚሊየን ነበር ተብሏል።
እንዲያም ሆኖ በገበያው ላይ የምርት አቅርቦት ችግር የለም ተብሏል። ሁኔታው በስርጭቱ ላይ ችግር መኖሩን አመላካች እንደሆነ ተጠቅሷል።
አስመጪዎች በበኩላቸው በብርና ዶላር መካከል ያለው ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ መስፋት የምርቶቹ ዋጋ እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል ማለታቸውን ከሬድዮ ጣቢያው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
መንግስት በፍራንኮ ቫሉታ ከውጪ እንዲገቡ የፈቀዳቸው ምርቶች ዋጋ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው #መጨመር አሣሣቢ ሆኗል ተባለ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ምርቶቹን በፍራንኮ ቫሉታ እንዲያስገቡ ከተፈቀደላቸው ነጋዴዎች ጋር ውይይት ማድረጉን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።
ዘይት ፣ ስኳር ፤ ሩዝና የህፃናት ወተት በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ የተፈቀዱ ምርቶች መሆናቸው ይታወሳል።
ምርቶቹ በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ በመፈቀዱ ባለፉት አስር ወራት ብቻ መንግስት በታክስ መልክ ማግኘት የነበረበትን ከ10 ቢሊየን ብር በላይ አጥቷል ተብሏል።
ነገር ግን የምርቶቹ ዋጋ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው ሲጨምር እንደሚታይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ድኤታ አቶ ተሻለ በልሁ ተናግረዋል።
ጭማሪው እየታየ ያለዉ በአለም ላይ ዋጋቸው #ቀንሶ ባለበት ወቅት ጭምር ነው ብለዋል።
ምርቶቹ ወደ ሀገር ውስጥ ከገቡ በኋላ ስርጭታቸውም ላይ ብዙ ግልፅነት እንደሌለ ተነግሯል።
እንደ ማሣያም ዘንድሮ በአስር ወራት ወደ ሀገር ውስጥ የገባው የምግብ ዘይት 97 ሚሊየን ሊትር እንደሆነ ተጠቅሷል። አምና በተመሣሣይ ጊዜ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው ግን ከአንድ መቶ ሚሊየን ነበር ተብሏል።
እንዲያም ሆኖ በገበያው ላይ የምርት አቅርቦት ችግር የለም ተብሏል። ሁኔታው በስርጭቱ ላይ ችግር መኖሩን አመላካች እንደሆነ ተጠቅሷል።
አስመጪዎች በበኩላቸው በብርና ዶላር መካከል ያለው ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ መስፋት የምርቶቹ ዋጋ እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል ማለታቸውን ከሬድዮ ጣቢያው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia