TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SafaricomEthiopia

💪🏾 በአዲስ አመት በአዲስ ሀይል TikTok ላይ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮ ፖስት እያደረግን እስከ 400,000 ብር እንሸለም!
እስከ መስከረም 18 ብቻ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ  እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!
#1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
" የመንግሥት ንብረትና ሐብት ለፓርቲ ሥራ ስለመዋሉ እንዲጣራልኝ ብጠይቀም ምላሽ አላገኘሁም " - ኢዜማ

" የመንግሥት ንብረትና ሐብት ለፓርቲ ሥራ እየዋለ ስለመሆኑ እንዲጣራልኝ ብጠይቀም ምላሽ አላገኘሁም ሲል " የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አስታወቀ።

ኢዜማ " ብልጽግና ፓርቲ መንግሥትን እና ፓርቲን ባለመለየቱ እሳየ ያለው ቸልተኝነት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት እንቅፋት ይሆናል " ብሏል፡፡

በተጨማሪ ፓርቲው ለፌደራል ዋና ኦዲተር የመንግሥት ንብረትና ሀብት ለፓርቲ ሥራ መዋሉ በኦዲት እንዲጣራ ቢጠይቅም አጥጋቢ ምላሽ አለማግኘቱን አስታውቋል፡፡

ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ " ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ለፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመንግሥት ንብረት እና ሀብት ለፓርቲ ሥራ መዋሉን ጠቅሰን በኦዲት እንዲጣራልን በደብዳቤ የጠየቅን ቢሆንም እስከ አሁን አጥጋቢ ምላሽ አላገኘንም " ሲል ገልጿል።

በተመሳሳይ ጥቅምት 07/2016 ዓ.ም. ለብልፅግና ፓርቲ አባላት ሥልጠና ከመንግሥት ካዝና ገንዘብ ወጥቶ መከፈል ስህተት መሆኑንና ሊታረም እንደሚገባ መግለጹን አስታውሷል።

" ይኼው ተግባር ከተጠናቀቀ ጥቂት ቀናት ባስቆጠረው ያለፈው ዓመት ብልፅግና ፓርቲ ከመንግሥት ንብረት የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ ነው " ሲል ፓርቲው ገልጿል።

" ብልፅግና ፓርቲ የመንግሥት ሥልጣንን እንደያዘ ፓርቲ እያሳየ ያለው ዳተኝነትም በሀገራችን እውን ሆኖ ማየት ለምንፈልገው የመድብለ ፓርቲ እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት መሆኑን በተደጋጋሚ በሚፈፅማቸው ስህተቶች እየተመለከትን ነው " ሲልም ተችቷል፡፡

ይህ ተግባር በአስቸኳይ የእርምት እርምጃ ካልተወሰደ ለሀገር ዴሞከራሲ ግንባታ ወደሚበጅ ትክክለኛ አሠራር እና ልምምድ ካልተመለሰ በስተቀር የሚያመጣው ቀውስ እና ይዞ የሚመጣው መዘዝ ቀላል አይደለም ብሏል።

" የሚመለከታቸው ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ሰሞኑን ብልፅግና ፓርቲ ለሥልጠና የተጠቀመበትን ሀብትና ንብረት በትክክል ወደ መንግሥት ካዝና መመለሱን እንዲያረጋግጡ " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

መንግሥትንና የሥራ ኃላፊዎቹን ተጠያቂ ለማድረግ፣ የተቋቋሙ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትም በሀገር እና በሕዝብ የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና መንግሥትን ተጠያቂ እንዲያደርጉ እንዲሁም የሀገርን ሀብት ከሙስና እና ከምዝበራ እንዲታደጉ ሲል ፓርቲው ጠይቋል። #ኢዜማ #አሀዱ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 ትምህርት ዘመን መደበኛ ትምህርት ነገ ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚጀምር የከተማው ትምህርት ቢሮ ገልጿል። @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ2017

ዛሬ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የ2017 የትምህርት ዘመን ተጀምሯል።

በመዲናችን አዲስ አበባ በሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ትምህርት ተጀምሯል።

በተለያዩ የክልል ከተሞችም የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተጀምሯል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

'' በዚህ ጦርነት ውስጥ ማን እየተጠቀመ እንዳለ ማወቅ አልቻልኩም '' - የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

" በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ግጭት ዓላማው ሊገባኝ አልቻለም " ሲል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ገለጸ።

ም/ቤቱ ይህን ያለው ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

የም/ቤቱ ዋና ሰብሳቢ ደስታ ዲንቃ ፥ " በሁለቱ ክልሎች ያለ መፍትሄ የቀጠለው ግጭት የጋራ ምክር ቤቱን በእጅጉ አሳስቦታል " ብለዋል።

" ንጹሃንን እየገደለ፣ እያሰቃየ እና የሀገርን ሀብት እያወደመ ያለውን ግጭት ሁለቱም አካላት ቆም ብለው አስበው ምን እንዳመጣ እራሳቸውን ሊጠይቁ " ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

" ንጹሃን፣ ባለስልጣናት እና የባለስልጣናት ልጆች እየተገደሉ እየታፈኑ ነው " ያሉት ዋና ሰብሳቢው " በዚህ ጦርነት ውስጥ ማን እየተጠቀመ እንዳለ ማወቅ አልቻልኩም " ሲሉ አስረድተዋል፡፡

" በጦርነቱ እንደ ሀገር ሀገር እየተጎዳ ነው፣ እንደ ህዝብ ህዝብ እየተጎዳ ነው ፣እንደ ዜጋ ዜጎች እየተጎዱ ነው ፣እንደ ታሪክ ታሪክን እያበላሽን ነው ምን ዓይነት ስሌት አስልተን እንደምንረጋጋ አላውቅም " ብለዋል፡፡

በሀገሪቱ በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ግጭት ውድመት እያስከተለ ቀጥሏል ያሉት አቶ ደስታ ችግሩን በንግግር ለመፍታት በሁለቱም ወገን ፍላጎት አይታይም ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

" አንዱ በአንዱ ላይ የበላይ ለመሆን ከሚደረግ ሩጫ የዘለለ ግጭቱን በንግግር የመፍታት ፍላጎት እየተመለከትን አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ታጣቂዎች ሆኑ መንግስት ችግሩን በንግግር ከመፍታ ይልቅ ግጭቱን ስም ለማጠልሸት አንዱ ሌላውን ለመወንጀል እና የህዝብ ድጋፍ ለማግኝት እየተጠቀሙበት ነው " ብለዋል።

ምክር ቤቱ በመንግስት እና በታጣዊዎች መካከል እየተካሄደ ያለው ግጭት ሁለቱም አካላት እቆምለታለሁ ፣ እቆረቆርለታለሁ የሚሉትን ህዝብ እና ሀገርን እያወደመ መሆኑን አውቀው በንግግር ችግራቸውን እንዲፈቱ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጠው ቃል ጠይቋል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :- 

1. አቶ ጌታቸው ረዳ 
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር 
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ 
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ 

ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገውና የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳና በርካታ የማእከለዊ ኮሚቴ አባላት " ህገወጥ " ያሉትን 14ኛ ጉባኤ በማካሄድ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መልሶ የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle  

@tikvahethiopia 
#AASTU #ASTU

በ2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ ጥሪ ቀርቧል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በቀጥታ (online) በመስጠት ነው የሚቀበሉት።

የትምህርት መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?

/ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሮ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፣ ማይኒንግ ኢንጂነሪንግ ፣ ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፉድ ሳይንስ፣ አፕላይድ ኒውትሪሽን ፣ ጂኦሎጂ፣ ባዮቴክኖሎጂ

/ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣  ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ኢንጂነሪንግ፣ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ አፕላይድ ቦዮሎጂ፣ አፕላይድ ኬሚስትሪ፣ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፋርማሲ፣ አፕላይድ ፊዚክስ ፣ አፕላይስ ጂኦሎጂ፣ አፕላይድ ማቲማቲክስ

የምዝገባ ጊዜ፡- ከመስከረም 06 እስከ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሆነ ተገልጿል።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ ነው።

የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et ድረገጽን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በድህረ ገጽ የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ ይደረጋል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ፤ በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡

NB. ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቅ ሲሆን የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ፍላጎቱ ያላቸው አመልካቾች ይህን አውቀው ቅድሚያ እንዲመዘገቡ ተብሏል።

@tikvahethiopia
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮፌሰር በየነ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር በየነ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንም ጠቁመዋል።

" በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ " ሲሉም ገልጸዋል። 

@tikvahethiopia
🌼 ፍካት ከመስከረም፣ በረከት ከቴሌብር ሐዋላ!
17% ተጨማሪ ስጦታ ከበርካታ የዕድል ሽልማቶች ጋር!!


ከባሕር ማዶ በቴሌብር ሬሚትና በአጋሮቻችን በኩል ዓለም አቀፍ ሐዋላ የተላከልዎን ገንዘብ በቴሌብር ሲቀበሉ 17% የገንዘብ ስጦታ እንዲሁም:-

💁‍♂️ 5 ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!

✈️ የውጭ ሀገር ደርሶ መልስ የበረራ ትኬት - እያንዳንዳቸው 480,000 ብር
🏞 ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ ቤተሰብ ፓኬጅ - እያንዳንዳቸው 44,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 20,000 ብር...

የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!

🗓 እስከ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲዎች በእኩል የሚያሳትፍ በምክር ቤት የሚመራ ሲቪል ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም አራት የትግራይ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ።

የጋራ መግለጫውን ያወጡት ፦
- ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ፣
- ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፣
- ውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት)
- ዓረና ንሉኣላውነትን ዴሞክራስን  (ዓረና)  ናቸው።

ፓርቲዎቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ ፤ " በትግራይ ያጋጠመው ችግር መነሻው ፓለቲካዊ ውድቀት ስለሆነ ከውድቀቱ ለመውጣት አካታች ፓለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ችግሩ የሚፈታው አንድ የፓለቲካ ፓርቲ በሚያራምደው የበላይነት አመራር ሳይሆን ሁሉም አቀፍ በሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ለዚህም ሁሉም የፓለቲካ ሃይሎች በእኩል የሚሳተፉበት በምክር ቤት የሚመራ ስቪል ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋም እንደ አንድ የችግር መፍቻ አስቀምጠዋል።

ፓርቲዎቹ በአሁኑ ወቅት በሁለት የህወሓት ሃይሎች የተፈጠረው ፓለቲካዊ መሳሳብ ወደ ጎን በመተው ወጣቶች ፣ ሴቶች ፣ የዳያስፓራ ማህበረሰብ መላው የትግራይ ህዝብ ዓላማቸው ደግፎ ከጎናቸው ሆኖ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። 

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ከማንኛውም የፓለቲካ ሃይል ውግንና ነፃ በመሆን የሲቪል መንግስትና ህግ በመመራት ለህዝብና አገር ጥቅም መቆም አለባቸው " ሲሉ አሳስበዋል። 

በቅርቡ የሚፈፀሙት ተጨማሪ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ፣ ግዛታዊ አንድነት የማስመለስ ፣ ታጣቃዎች ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀልና ሌሎች በትግራይ በኩል የሚፈፀሙ ስምምነቶችና ውሎች ለህዝብና ጉዳዩ  ለሚመለከታቸው አካላት ግልፅና ይፋ እንዲደረግም ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ክስ ተመሰረተባቸው። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ? - አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ - የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል…
#Update

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ግለሰቦቹ ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦
➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣
➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል።

በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል።

ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)