TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ብርሃን_ባንክ

የብርሃን ሞባይል ባንኪንግን ተጠቅመው :-

የዋይፋይ እና የሌሎችም የኢትዮ ቴሌኮም ክፍያዎችን በቀላሉ ያከናውኑ ፤ የአየር ትኬትዎን ይቁረጡ ፤ቀሪ የብድር መጠንዎን ይወቁ ፤ (*881#) በመጠቀም ያለ ኢንተርኔት ገንዘብ ያስተላለፍ በሞባይልዎ የቼክ ደብተር ይዘዙ ፤ የት/ቤት ክፍያዎን በቀላሉ ይክፈሉ ፤ ከራስዎ የባንክ ሂሳብ ወደ ሌሎች ባንኮች ሂሳብ ገንዘብ ያስተላልፉ።
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
#OLF

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራሮች ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በቡራዩ እስር ላይ ካሉ 7 የኦነግ አመራሮች 4ቱ ከእስር እንዲለቀቁ የቡራዩ ወረዳ ፍ/ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ጠበቃ አቶ ደምሴ ፍቃዱ ጉዳዩን በተመለከተ ለ #ቪኦኤ_ሬድዮ በሰጡት ቃል አራቱ የኦነግ አመራሮች አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቅርበው እንደነበር፤ አቤቱታ የቀረበለት የቡራዩ ከተማ ፍ/ ቤት ግለሰቦቹ በማን እና ለምን እንደታሰሩ ለመረዳት ለሶስት ተከታታይ ችሎት ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

ነገር ግን ፖሊስ ሆነ እስረኞች አልቀረቡም። አርብ ሀምሌ 8 የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ማብራሪያ ሠጥቷል።

ጠበቃ ደምሴ ፍቃዱ ፦

" 1ኛ አመልካች የሆነው ሚካኤል በቀለ ከዚህ ቀደም የወንጀል መዝገብ ተጣርቶበት በወንጀል አንቀፅ 42 መሰረት የተጠረጠረበት ጉዳይ ወንጀል ነው ተብሎ የሚያስከስስ ባለመሆኑ መዝገቡ ተዘግቶ ፖሊስ ከእስር ቤት እንዲለቀው ትዕዛዝ ፅፈንለት ፖሊስ ግን አለቅም ማለቱን አቃቤ ህግ ገልጿል።

2ኛ እና 3ኛ አመልካቾች ለሚ ቤኛ እና ዳዊት አብደታን በተመለከተ በተጠረጠሩበት ወንጀል ተከሰው የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከተሰሙ በኃላ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ የሚያስቀጣ አይደለም በማለት በነፃ ካሰናበታቸው በኃላ ፖሊስ በራሱ ስልጣን ነው ያሰረው ሲል አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት አመልክቷል።

4ኛ አመልካች ገዳ ገቢሳ የተጠረጠረበት ወንጀል አቃቤ ህግ ከመረመረ በኃላ አያስከስስም ብሎ መዝገቡን ዘግቶ ከእስር እንዲለቀቅ ለፖሊስ ትዕዛዝ መስጠቱን አብራርቷል።

ከአቃቤ ህግም ምንም መዝገብ የላቸውም ሲል ነው የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት ያስረዳው። "

ፍ/ቤት ሀምሌ 11 ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነ ቢሆንን ታሳሪዎቹ እስካሁን አልተለቀቁም።

@TIKVAHETHIOPIA
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማስታወሻ በ18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ4ኛ ቀን ውድድር ዛሬ ይካሄዳል። የሀገራችን ልጆች የሚካፈሉበት ውድድር የሚከተሉት ናቸው። 🏟️ በማራቶን የሴቶች ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ጎይቶቶም ገ/ስላሴ 🇪🇹 አባበል የሻነህ 🇪🇹 አሸቴ በክሬ (ሰዓት - ቀን 10:15) 🏟️ 3,000 ሜትር መሰናክል የወንዶች ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ለሜቻ ግርማ 🇪🇹 ሀይለማርያም አማረ 🇪🇹 ጌትነት ዋለ (ሰዓት - ለሊት 11:20)…
#ማስታወሻ🇪🇹

የአለም ሻምፒዮናው 6ኛ ቀኑ ይዟል። በዛሬው ዕለት ሀገራችን አንድ የፍፃሜ ውድድርን ጨምሮ ሁለት ማጣርያዎችን የምታደርግ ይሆናል።

🏟️ የሴቶች 5,000 ሜትር ማጣርያ ፦

🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ
🇪🇹 ለተሰንበት ግደይ
🇪🇹 ዳዊት ስዩም

(ሰዓት - ለሊት 8:25)

🏟️ የወንዶች 800 ሜትር ማጣርያ ፦

🇪🇹 ኤርሚያስ ግርማ
🇪🇹 ቶሎሳ ቦደና

(ሰዓት-ሌሊት 9:20)

🏟️ የሴቶች 3,000 ሜትር መሰናክል #ፍፃሜ

🇪🇹 መቅደስ አበበ
🇪🇹 ወርቅውሃ ጌታቸው

(ሰዓት - ሌሊት 11:45)

ድል ሀገራችን 🇪🇹 !

ተጨማሪ ስፖርታዊ ጉዳዮች https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#DrTazebachew

የዶ/ር ታዘባቸው ውዴ ጉዳይ ዛሬም ድረስ መፍትሄ ሳያገኝ፤ ዩኒቨርሲቲውም አንዳች ነገር ሳይል ቀጥሏል።

ዶ/ር ታዘባቸው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በህክምና ተመርቆ ይርጋለም ሆስፒታል ለ2 ዓመት አገልግሎ ለማህፀንና ፅንስ ስፔሻላይዜሽን ትምህርት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (ጥቁር አንበሳ) ተቀላቅሎ ትምህርቱን ሲከታተል ነበር።

ዶ/ር ታዘባቸው ከልጅነቱ ጀምሮ በአንድ አይኑ ላይ የመሸዋረር ችግር ያለበት ሲሆን ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲመረቅ ሆነ ወደ አ/አ ጥቁር አንበሳ ሲቀላቀል አንድም ቀን ስለአይኑ ጉዳይ ተነስቶም፤ ተጠይቆ አያውቅም።

ጥቁር አንበሳን ሲቀላቀልም በቃል እና በፁሁፍ ፈተና ተፈትኖ ብቃቱን አስመስክሮ ተቋሙ ገብተህ መማር ትችላለህ ብሎት ነው።

ነገር ግን 4 ዓመት እጅግ ከፍተኛ ድካምና ጥረት የሚጠይቀውን የስፔሻላይዜሽን ትምህርቱን ቀንና ሌት እንቅልፍ አጥቶ ተምሮ ሊመረቅ ጥቂት ቀናት ሲቀረው ድንገት የዓይን ምርመራ አድርግ ይባላልና ብቁ አይደለህም ተብሎ ወደሌላ ዲፓርትመንት ገብቶ (ኒውሮሎጂ) ከአንደኛ አመት እንዲጀምር ተደርጓል።

ዶ/ር ታዘባቸው ከዚህ ቀደም እንዲህ አይነት ነገር ሰምቶ እንደማያውቅ ተናግሮ እሱ ብቻውን ከሌሎች በተለየ የአይን ምርመራ እንዲያደርግ ታዞ ምርመራ ካደረገ በኃላ በአጭር ፅሁፍ ትምህርቱን መቀጠል እንደማይችል እና አንደማይመረቅ እንደተነገረው ያስረዳል።

የአይኑ መንሸዋረር አንድም ቀን ለስራው ፣ለትምህርቱ እንቅፋት ሆኖበትና በዚህ ምክንያት በርካታ የቀዶ ጥገና ስራ ሲሰራ ችግር ተፈጥሮ እንደማያውቅም ይገልፃል።

4 ዓመት ከለፋበት ትምህርት ወጥቶ ወደሌላ ዲፓርትመንት እንዲገባ የተደረገው ዶ/ር ታዘባቸው ዩኒቨርሲቲው ውሳኔውን ዳግም እንዲያጤነው ካልሆነ መብቱን ለማስከበር ወደህግ እንደሚወስደው ከጠበቃው ጋር አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የመኪና ዝርፊያ ! ከጥቂት ቀናት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ የኤሌክትሮኒክ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ወገኖች ላይ የሚፈፀመው ዝርፊያ አሳሳቢ መሆኑን አመልክተን ነበር። በወቅቱ አንድ የቤተሰባችን አባል ራሱንና ቤተሰቡን ለማስተዳደር የሚሰራባትን መኪና ዘራፊዎች በስለት አስፈራርተውት እንደዘረፉት መግለፁ አይዘነጋም። ትናንት አርብ ምሽት 4:00 ላይ ደግሞ ሌላ አንድ ወንድማችን ከፍየል ቤት ወደ ሀያሁለት…
#አዲስ_አበባ

አዲስ አበባ ውስጥ የቀጠለው ዝርፊያና ጥቃት !

ከሰሞኑን የኤሌክትሮኒክ ትራንስፖርት የሚሰጡ ወገኖች ላይ እየደረሰ ስላለው ወንጀል መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም።

ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው ማመልከታችንም የሚታወስ ነው።

ለማስታወስ ፦

👉 አንድ የቤተሰባችን አባል ራሱንና ቤተሰቡን ለማስተዳደር የሚሰራበትን መኪና ዘራፊዎች በስለት አስፈራርተውት እንደዘረፉት : t.iss.one/tikvahethiopia/71682?single

👉 ባለፈው አርብ ምሽት አንድ ወንድማችን ከፍየል ቤት ወደ 22 ከመገድ ላይ ሰው ጭኖ አውራሪስ አካባቢ ሲደርስ አንገቱን አንቀው እራሱን እንዲስት በማድረግ ከመኪናው አሰወጥተው በመወርወር መኪናውን ይዘው መሰወራቸውን አሳውቀን ነበር : t.iss.one/tikvahethiopia/72020?single

የአሁኑ ግን ከዝርፈያም ባለፈ የሰው ህይወት የተቀጠፈበት ነው።

ከላይ በፎቶ የምትመለከቱ ሳላዲን ሐሰን ይባላል።

የምትመለከቷት መኪናም የእሱ ነበረች።

ትናንት ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ እጅግ በጣም አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ተገድሎ መኪናው ተዘርፏል።

ሳላዲን የራሱን እና የቤተሰቦቹን ኑሮ ለማሻሻል ሲል ይተዳደርበት በነበረው የመኪና እጥበት ስራ ከሚያገኘው ገቢ በመቆጠብ ነው መኪናዋን ገዝቷት የነበረው።

ሳላዲን በጩቤ ተወግቶ ተገድሎ መኪናው ከመዘረፉ በፊት የመጨረሻ አገልግሎት ለመስጠት የተደወለበት አካባቢ ገርጂ 24 ልዩ ቦታ ኤርትራ ቆንጽላ ጽ/ቤት አካባቢ መሆኑን የሚሰራበት ድርጅት እንደነገራቸው ጓደኞቹ ገልፀዋል።

ቤተሰቦቹ ከባድ በሆነ መሪር ሀዘን ውስጥ የሚገኙ ሲሆን ጓደኞቹም በተፈጠረው ሁኔታ እጅግ መደናገጣቸውንና ከባድ ሀዘን ውስጥ እንዳሉ ነግረውናል።

ለበለጠ መረጃ፦ 0944322244 (አብዲ ሰይድ) ፤ 0967803785 (ካሊድ አብዱልቃድር)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ🇪🇹

የሴቶች 5 ሺ ሜትር ማጣሪያ እየተካሄደ ይገኛል።

#ዳዊት_ስዩም እና #ጉዳፍ_ፀጋይ በአንድ ምድብ ውስጥ ሆነው ማጣሪያውን እየተወዳደሩ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጠናቋል 🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ 👉 1ኛ 🇪🇹 ዳዊት ስዩም 👉 2ኛ በመሆን ወደ ፍፃሜው አልፈዋል። #የሴቶች_5000_ሺህ_ሜትር @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

የ10 ሺህ ሜትር ባለ ወርቅ ባለቤቷ ለተሰንበት ግደይ በሁለተኛው ምድብ የ5 ሺህ ሜትር ማጣሪያ ውድድሯን እያካሄደች ትገኛለች።

@tikvahethiopia
#Update #ኢትዮጵያ🇪🇹

በወንዶች 800 ሜትር ማጣሪያ በተደረገ ውድድር የሀገራች ልጅ ቶሎሳ ቦደና ወደ ግ/ፍፃሜ ውድድሩ ማለፍ ችሏል (ባስመዘገበው ፈጣን ሰዓት) ።

ሌላኛው የማጣሪያ ውድድር ተሳታፊው ኤርሚያስ ግርማ ወደ ግ/ፍፃሜው ማለፍ ሳይችል ቀርቷል።

የማጣሪያ ውድድሮቹ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ፉክክር የነበረባቸው ነበሩ።

More : https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethiopia