TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ፤ በአዲስ አበባ በሁከትና ብጥብጥ በግንባር ቀደምትነት ተሳትፈዋል ያላቸውን 76 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል። ግብረ ኃይሉ ፤ " ከሀይማኖታዊ ሥርዓቱ ውጭ ሌላ የሁከትና ብጥብጥ ዓላማ ያላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ለብጥብጥ መነሻ በማይሆን ምክንያት ከስታዲየም ውጭ በተለምዶ ' የቀይ ሽብር ሰማዕታት መታሰቢያ ሙዚየም ' አጠገብ ሆነው ባስነሱት…
ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፦
" . . . ልክ ወደ መጨረሻው ፕሮግራም ላይ ልንገባ ስንል ነው ድንገት ድምፅ ሰማን፤ እየተረበሸ እንደሆነ ተነገረን።
ምንድነው ? ብዬ የሚመለከተው የመንግስት የስራ ኃላፊ ከፀጥታ መዋቅር ውስጥ አንዱ አመራር ጋር ደውዬ ስጠይቅ ያለው ነገር ' ሀያት ሬጀንሲ አካባቢ ጭስ ነው ' ይረጋጉ አሉኝ።
ሰው ይረጋጋ ብዬ ለመድረክ አስተባባሪው ነገርኳቸው ፤ ሰውን አረጋጋነው ፤ መልሶ ግን ቀጠለ ረብሻው ፣ ድምፁም የሚረብሽ ስለነበር ትንሽ ጥሩ አልነበረምና ምንድነው በሚል ጉዳዮችን ለመከታተል ሞከርን።
መልሼ ስጠይቅ ፤ ' አይ አስለቃሽ ጋዝ ከአንድ ፖሊስ በአጋጣሚ አምልጦት ፤ ድንገት ባርቆበት ' ተባለ ፤ ይህንን የሰማሁት ከፀጥታ መዋቅሩ ነው።
...በጣም ደስ የሚል እና ያማረ ፣ በጣም በጥሩ ሁኔታ ያሳለፍንበት ኢድ ነበር ነገር ግን ይሄ ክስተት መጥቶ ትንሽ ነገሮችን ረባበሻቸው።
በትክክል ለማጣራት ሞክሪያለሁ አንድ የፀጥታ ኃላፊ ከሚመለከታቸው ኮሚሽነር ጋር ተነጋግሬ የነገሩኝ ' ፌዴራል ፖሊሱ ባርቆበት ነው ' አሉ።
ከዛም ደግሞ በትክክል አካባቢው ላይ የመደብናቸው የእኛ አስተናጋጆች በአጋጣሚ ሴቶች ያሉበትና የሚሰግዱበት ቦታ ነበር።
የ 'ሰማዕታት ሀውልት' አካባቢ ላይ ነው፤ ሚኒስትሮች ሳይቀሩ የመንግስት ሙስሊም ሴት ሚኒስትሮች ቦታው ላይ የነበሩ አግኝቻቸው ያዩትን ክፍተት ነግረውኛል።
ከአንድ የ 'ፌዴራል ፖሊስ' ነው ተወርውሯል የሚሉት ምክንያቱም ፤ የሚባርቅ ነገር ዝም ብሎ የሚወድቅ አይደለም ፤ ተፈቶ መለቀቅ አለበት አስለቃሽ ጭሱ ፤ ተፈቶ ነው የተለቀቀው ወደ ሰው ነው የተጣለው።
ሴቶችና ህፃናቶች ወዳሉበት ቦታ ነው የተወረወረው።
ሰው በዛ ሰዓት ወደ መራባበሽ ስሜት ውስጥ ገባ ፤ ሴቶችም በድንጋጤ መሮጥ፤ መነሳት ያፍናል አይነት ሁኔታ ተፈጠረ።
በዚህ ሂደት ላይ እያሉ ሰውን አትውጣ ወደዛ አትሂድ የሚለው ግፊት መጣ ፤ በዚህ መካከል ሰውየውንም ይዘውት ነበር ፤ የእኛ አስተባባሪዎች ከያዙት በኃላ ሌሎች ፌዴራል ፖሊሶች ልቀቁት ብለው ያስለቀቁት፤ እሱም ይቅርታ ጠይቋል ' እኔ ባርቆብኝ ነው፤ ሳላስብ ነው ' ብሎ ደንግጦ የተናገረበት ሂደት ነበር የነበረው።
ያ ሁኔታ ተከሰተ ሰው ስሜት ውስጥ ገባ ፤ እንደገና መገፋት ፣ ወደዛ አትሄድም ወደዚህ አትመጣም ፣ ሶላት አልሰገደም በዚህ አይነት ነገር ውስጥ ሲገባ ተኩስ ተጀመረ ወደ አየር ፤ አስለቃሽ ጭሶች መሰል ነገራቶች እየተደረጉ ሲሄዱ አቅጣጫ ስተው ረብሻዎች ደስ የማይል ነገር ተከስቷል።
እስካሁን ባለኝ መረጃ የሞተ ሰው የለም። የተጎዱ ሰዎች አሉ።
የተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ የገቡ አይናቸው አካባቢ ተመተው...በተለያየ ነገር የተመቱ ሰዎች ሆስፒታል የገቡ አሉ። ይሄ ነው ክስተቱ።
መጣራት አለበት ለምን ?፤ ማን ?፤ እንዴት ? የሚሉት ነገሮች መታየት አለባቸው። ይሄ በጣም ትልቅ የሆነ ታሪካዊ የሆነ፣ እንደ አትዮጵያ ያለ ሙስሊም የውጭ እንግዳ ጠርተን ፣ በልዩ ሁኔታ ያከበርነው ኢድ ስለነበር እነዚህ ነገሮች ከባድ ናቸው። "
@tikvahethiopia
" . . . ልክ ወደ መጨረሻው ፕሮግራም ላይ ልንገባ ስንል ነው ድንገት ድምፅ ሰማን፤ እየተረበሸ እንደሆነ ተነገረን።
ምንድነው ? ብዬ የሚመለከተው የመንግስት የስራ ኃላፊ ከፀጥታ መዋቅር ውስጥ አንዱ አመራር ጋር ደውዬ ስጠይቅ ያለው ነገር ' ሀያት ሬጀንሲ አካባቢ ጭስ ነው ' ይረጋጉ አሉኝ።
ሰው ይረጋጋ ብዬ ለመድረክ አስተባባሪው ነገርኳቸው ፤ ሰውን አረጋጋነው ፤ መልሶ ግን ቀጠለ ረብሻው ፣ ድምፁም የሚረብሽ ስለነበር ትንሽ ጥሩ አልነበረምና ምንድነው በሚል ጉዳዮችን ለመከታተል ሞከርን።
መልሼ ስጠይቅ ፤ ' አይ አስለቃሽ ጋዝ ከአንድ ፖሊስ በአጋጣሚ አምልጦት ፤ ድንገት ባርቆበት ' ተባለ ፤ ይህንን የሰማሁት ከፀጥታ መዋቅሩ ነው።
...በጣም ደስ የሚል እና ያማረ ፣ በጣም በጥሩ ሁኔታ ያሳለፍንበት ኢድ ነበር ነገር ግን ይሄ ክስተት መጥቶ ትንሽ ነገሮችን ረባበሻቸው።
በትክክል ለማጣራት ሞክሪያለሁ አንድ የፀጥታ ኃላፊ ከሚመለከታቸው ኮሚሽነር ጋር ተነጋግሬ የነገሩኝ ' ፌዴራል ፖሊሱ ባርቆበት ነው ' አሉ።
ከዛም ደግሞ በትክክል አካባቢው ላይ የመደብናቸው የእኛ አስተናጋጆች በአጋጣሚ ሴቶች ያሉበትና የሚሰግዱበት ቦታ ነበር።
የ 'ሰማዕታት ሀውልት' አካባቢ ላይ ነው፤ ሚኒስትሮች ሳይቀሩ የመንግስት ሙስሊም ሴት ሚኒስትሮች ቦታው ላይ የነበሩ አግኝቻቸው ያዩትን ክፍተት ነግረውኛል።
ከአንድ የ 'ፌዴራል ፖሊስ' ነው ተወርውሯል የሚሉት ምክንያቱም ፤ የሚባርቅ ነገር ዝም ብሎ የሚወድቅ አይደለም ፤ ተፈቶ መለቀቅ አለበት አስለቃሽ ጭሱ ፤ ተፈቶ ነው የተለቀቀው ወደ ሰው ነው የተጣለው።
ሴቶችና ህፃናቶች ወዳሉበት ቦታ ነው የተወረወረው።
ሰው በዛ ሰዓት ወደ መራባበሽ ስሜት ውስጥ ገባ ፤ ሴቶችም በድንጋጤ መሮጥ፤ መነሳት ያፍናል አይነት ሁኔታ ተፈጠረ።
በዚህ ሂደት ላይ እያሉ ሰውን አትውጣ ወደዛ አትሂድ የሚለው ግፊት መጣ ፤ በዚህ መካከል ሰውየውንም ይዘውት ነበር ፤ የእኛ አስተባባሪዎች ከያዙት በኃላ ሌሎች ፌዴራል ፖሊሶች ልቀቁት ብለው ያስለቀቁት፤ እሱም ይቅርታ ጠይቋል ' እኔ ባርቆብኝ ነው፤ ሳላስብ ነው ' ብሎ ደንግጦ የተናገረበት ሂደት ነበር የነበረው።
ያ ሁኔታ ተከሰተ ሰው ስሜት ውስጥ ገባ ፤ እንደገና መገፋት ፣ ወደዛ አትሄድም ወደዚህ አትመጣም ፣ ሶላት አልሰገደም በዚህ አይነት ነገር ውስጥ ሲገባ ተኩስ ተጀመረ ወደ አየር ፤ አስለቃሽ ጭሶች መሰል ነገራቶች እየተደረጉ ሲሄዱ አቅጣጫ ስተው ረብሻዎች ደስ የማይል ነገር ተከስቷል።
እስካሁን ባለኝ መረጃ የሞተ ሰው የለም። የተጎዱ ሰዎች አሉ።
የተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ የገቡ አይናቸው አካባቢ ተመተው...በተለያየ ነገር የተመቱ ሰዎች ሆስፒታል የገቡ አሉ። ይሄ ነው ክስተቱ።
መጣራት አለበት ለምን ?፤ ማን ?፤ እንዴት ? የሚሉት ነገሮች መታየት አለባቸው። ይሄ በጣም ትልቅ የሆነ ታሪካዊ የሆነ፣ እንደ አትዮጵያ ያለ ሙስሊም የውጭ እንግዳ ጠርተን ፣ በልዩ ሁኔታ ያከበርነው ኢድ ስለነበር እነዚህ ነገሮች ከባድ ናቸው። "
@tikvahethiopia
#የነዳጅ_ዋጋ !
አሁን በዓለም ገበያ 1 በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ 106.6 ዶላር እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት አንድ በርሜል ነዳጅ 104.3 ዶላር በሆነ ዋጋ እየተሸጠ ይገኛል።
#OilPrice
@tikvahethiopia
አሁን በዓለም ገበያ 1 በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ 106.6 ዶላር እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት አንድ በርሜል ነዳጅ 104.3 ዶላር በሆነ ዋጋ እየተሸጠ ይገኛል።
#OilPrice
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ያለበት ቦታ ሳይታወቅ ቀናት መቆጠራቸው እንዳሳሰባቸው ጠበቃው ተናገሩ።
እሁድ ሚያዚያ 23/2014 ዓ.ም. በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎ በቁጥጥር ሥር ውሏል የተባለውን የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ አድራሻን ማወቅ እንዳልተቻላቸው ጠበቃው አዲሱ አልጋው ተናግረዋል።
ጠበቃው እንዳሉት እሁድ ረፋድ ላይ የታጠቁ እና ሲቪል የለበሱ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች ጋዜጠኛው ተከራይቶ ወደ ሚኖርበት ጊቢ በአጥር ዘለው ከገቡ በኋላ 'ለጥያቄ ትፈለጋለህ' ብለው ደንበኛቸውን ይዘው መሄዳቸውን ተናግረዋል።
ጋዜጠኛው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ከዋለ 48 ሰዓታት ቢያልፉም እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረቡ እና ታስሮ የሚገኝበትን ቦታ ለማወቅ ያደረጉት ጥረት አለመሳካቱ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
እሁድ ሚያዚያ 23/2014 ዓ.ም. በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎ በቁጥጥር ሥር ውሏል የተባለውን የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ አድራሻን ማወቅ እንዳልተቻላቸው ጠበቃው አዲሱ አልጋው ተናግረዋል።
ጠበቃው እንዳሉት እሁድ ረፋድ ላይ የታጠቁ እና ሲቪል የለበሱ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች ጋዜጠኛው ተከራይቶ ወደ ሚኖርበት ጊቢ በአጥር ዘለው ከገቡ በኋላ 'ለጥያቄ ትፈለጋለህ' ብለው ደንበኛቸውን ይዘው መሄዳቸውን ተናግረዋል።
ጋዜጠኛው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ከዋለ 48 ሰዓታት ቢያልፉም እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረቡ እና ታስሮ የሚገኝበትን ቦታ ለማወቅ ያደረጉት ጥረት አለመሳካቱ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
#GONDAR
የአማራ ክልል ሰላም እና ህዝብ ደህንነት ቢሮ በጎንደር ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም የተባሉ 6 የፖለቲካ እና የፀጥታ መዋቅር አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ነው ብሏል።
እነዚህ ስድስት የፖለቲካና የፀጥታ መዋቅር አመራሮች ስማቸው በይፋ ያልተገለፀ ሲሆን በምን አይነት የአመራርነት ቦታ ላይ ያሉ እንደሆኑ አልተብራራም።
ቢሮው ፤ ከህዝቡ ፣ ከፖለቲካ አመራሩ እና ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ውይይት እና ግምገማ ከተደረገ በኃላ የማስተካከያ እና የእርምት እርምጃዎች እንደሚወሰዱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የአማራ ክልል ሰላም እና ህዝብ ደህንነት ቢሮ በጎንደር ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም የተባሉ 6 የፖለቲካ እና የፀጥታ መዋቅር አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ነው ብሏል።
እነዚህ ስድስት የፖለቲካና የፀጥታ መዋቅር አመራሮች ስማቸው በይፋ ያልተገለፀ ሲሆን በምን አይነት የአመራርነት ቦታ ላይ ያሉ እንደሆኑ አልተብራራም።
ቢሮው ፤ ከህዝቡ ፣ ከፖለቲካ አመራሩ እና ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ውይይት እና ግምገማ ከተደረገ በኃላ የማስተካከያ እና የእርምት እርምጃዎች እንደሚወሰዱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሁለተኛውን ብሔራዊ የሥራ ጉባኤ አስመልክቶ ንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡
ውድድሩ በ2 ዙር የሚደረግ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ምርጥ አስር የንግድ ሥራ ሀሳቦች የሚለዩ ሲሆን በሁለተኛው ዙር ምርጥ ሦስቱ ተለይተው የሥራ ማስኬጃ ካፒታል የሚሰጣቸው ይሆናል ተብሏል።
መስፈርቶች፦
- የሥራ ፈጠራው ኦርጂናል እና ፈጽሞ ያልተተገበረ መሆን አለበት፤
- የንግድ ሀሳቡ ባለቤት/ቶች ኢትዮጵያዊ/ያን መሆን አለባቸው፤
- የንግድ ሀሳቡ ኢትዮጵያ ውስጥ መተግበር አለበት
- ሴቶች፤ አካል ጉዳተኞች፤ ተፈናቃዮች እና ቤት አልባ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ይበረታታሉ።
የማመልከቻ ጊዜው ግንቦት 02 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰዓት የሚያበቃ ይሆናል።
ሙሉ መረጃውን በማግኘት ለመወዳደር ተከታዩን አድራሻ ይክፈቱ https://forms.gle/c1kNcPAKQUMA459J7
@tikvahethmagazine
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሁለተኛውን ብሔራዊ የሥራ ጉባኤ አስመልክቶ ንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡
ውድድሩ በ2 ዙር የሚደረግ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ምርጥ አስር የንግድ ሥራ ሀሳቦች የሚለዩ ሲሆን በሁለተኛው ዙር ምርጥ ሦስቱ ተለይተው የሥራ ማስኬጃ ካፒታል የሚሰጣቸው ይሆናል ተብሏል።
መስፈርቶች፦
- የሥራ ፈጠራው ኦርጂናል እና ፈጽሞ ያልተተገበረ መሆን አለበት፤
- የንግድ ሀሳቡ ባለቤት/ቶች ኢትዮጵያዊ/ያን መሆን አለባቸው፤
- የንግድ ሀሳቡ ኢትዮጵያ ውስጥ መተግበር አለበት
- ሴቶች፤ አካል ጉዳተኞች፤ ተፈናቃዮች እና ቤት አልባ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ይበረታታሉ።
የማመልከቻ ጊዜው ግንቦት 02 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰዓት የሚያበቃ ይሆናል።
ሙሉ መረጃውን በማግኘት ለመወዳደር ተከታዩን አድራሻ ይክፈቱ https://forms.gle/c1kNcPAKQUMA459J7
@tikvahethmagazine
" ሀገር ፈርሳ ተቅበዝባዥ ከመሆናችን በፊት ሁሉም ለሀልዎቷ ዘብ ይቁም " - እናት ፓርቲ
እናት ፓርቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ልኮልናል።
ፓርቲው ፤ በመግለጫው ከሰሞኑን በጎንደር ከተማ የተፈጠረውን ክስተት ይህን ተከትሎም በስልጤ ዞን የተፈጠረውን ክስተት ዳሷል።
በተጨማሪ ሰሞኑን በደራሼ ስለተፈጠረው ችግር አንስቷል።
እናት ፓርቲ ፤ ከሰሞኑን ከሃይማኖት ጋር የተፈጠሩ ክስተቶችን በቅርበት ሲከታተል መቆየቱን አመልክቶ አሰባሰብኩኝ ባለው መረጃና ማስረጃም ጉዳዩ ለሀገር አንድነት የሚቆሙ የሃይማኖት ተቋማትን በማፍረስ ሀገር የማፍረስ ተልዕኮ እንጂ ሃይማኖታዊ ግጭት አይደለም ብሏል።
ፓርቲው በጎንደር ከተማ እና በስልጤ ዞን ወራቤ በደረሰው ነገር ሁሉ ማዘኑን ገልጾ ፤ ጥቃት የተሰነዘረባቸው ወገኖች ሲሳደዱ በየቤታቸው አስገብተው ከጥቃት የመታደግ ሥራ በመሥራት ኢትዮጵያዊ ከፍታቸውን በመከራ ወቅት ላሳዩ ወገኖች ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል፣ በደራሼ ልዩ ወረዳ፣ ጊዶሌ ከተማና አካባቢው ላይ በዚሁ ሰሞን " የጠየቅነውና ቃል የተገባልን ለምን አይፈጸምም ? " በሚል መነሻ እንዲሁም በአስተዳደሩ እንዝህላልነት ችግር ተከስቶ ቀላል የማይባል የሰው ሕይወት እንደጠፋ፣ ንብረት እንደወደመ አመልክቶ ይህም ሀዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገበት ገልጿል።
(ሙሉ መገለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
እናት ፓርቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ልኮልናል።
ፓርቲው ፤ በመግለጫው ከሰሞኑን በጎንደር ከተማ የተፈጠረውን ክስተት ይህን ተከትሎም በስልጤ ዞን የተፈጠረውን ክስተት ዳሷል።
በተጨማሪ ሰሞኑን በደራሼ ስለተፈጠረው ችግር አንስቷል።
እናት ፓርቲ ፤ ከሰሞኑን ከሃይማኖት ጋር የተፈጠሩ ክስተቶችን በቅርበት ሲከታተል መቆየቱን አመልክቶ አሰባሰብኩኝ ባለው መረጃና ማስረጃም ጉዳዩ ለሀገር አንድነት የሚቆሙ የሃይማኖት ተቋማትን በማፍረስ ሀገር የማፍረስ ተልዕኮ እንጂ ሃይማኖታዊ ግጭት አይደለም ብሏል።
ፓርቲው በጎንደር ከተማ እና በስልጤ ዞን ወራቤ በደረሰው ነገር ሁሉ ማዘኑን ገልጾ ፤ ጥቃት የተሰነዘረባቸው ወገኖች ሲሳደዱ በየቤታቸው አስገብተው ከጥቃት የመታደግ ሥራ በመሥራት ኢትዮጵያዊ ከፍታቸውን በመከራ ወቅት ላሳዩ ወገኖች ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል፣ በደራሼ ልዩ ወረዳ፣ ጊዶሌ ከተማና አካባቢው ላይ በዚሁ ሰሞን " የጠየቅነውና ቃል የተገባልን ለምን አይፈጸምም ? " በሚል መነሻ እንዲሁም በአስተዳደሩ እንዝህላልነት ችግር ተከስቶ ቀላል የማይባል የሰው ሕይወት እንደጠፋ፣ ንብረት እንደወደመ አመልክቶ ይህም ሀዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገበት ገልጿል።
(ሙሉ መገለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#መግቢያ_ቀናት
የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አዲስ የተመደቡላቸውን ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትን እና ሪፖርት የሚያደርጉበትን ቀን እያሳወቁ ይገኛሉ።
እስካሁን ባለው የመግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ቀን ያሳወቁ ተቋማት እና የአዲስ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መግቢያ/ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ፦
👉 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ማድረጊያ ሚያዚያ 24 እና 25/2014 ዓ/ም ፤ በረመዷን በዓል ምክንያት መድረስ ለማይችሉ እስከ አርብ ሚያዚያ 28 /2014 ዓ/ም ድረስ
👉 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የኦንላይን ምዝገባ ግንቦት 01 እስከ 05/2014 ዓ/ም ፤ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ግንቦት 8 እና 9/2014 ዓ/ም
👉 ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 08 እና 09/2014 ዓ.ም
👉 ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 27 እና 28/2014 ዓ/ም
👉 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 1 እና 2 /2014 ዓ/ም
👉 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 01 እና 02/2014 ዓ/ም
👉 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 29 እና 30 /2014 ዓ/ም
👉 ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 28 እስከ 30 /2014 ዓ/ም
👉 ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 28 እና 29/2014 ዓ/ም
👉 ASTU / AASTU ሚያዚያ 28 እና 29 /2014 ዓ/ም በቅጣት ግንቦት 1 /2014 ዓ/ም
👉 ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን ግንቦት 8 እና 9 ፤ ምዝገባ ግንቦት 10 እና 11
👉 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን ግንቦት 01 እና 02 /2014 ዓ/ም
👉 ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ግንቦት 12፣ 13 እና 14
ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች ጥሪ ሲያቀርቡ ተከታትለን የምናሳውቅ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጉዳይ ብቻ በ @tikvahuniversity መከታተል ይቻላል።
@tikvahethiopia
የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አዲስ የተመደቡላቸውን ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትን እና ሪፖርት የሚያደርጉበትን ቀን እያሳወቁ ይገኛሉ።
እስካሁን ባለው የመግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ቀን ያሳወቁ ተቋማት እና የአዲስ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መግቢያ/ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ፦
👉 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ማድረጊያ ሚያዚያ 24 እና 25/2014 ዓ/ም ፤ በረመዷን በዓል ምክንያት መድረስ ለማይችሉ እስከ አርብ ሚያዚያ 28 /2014 ዓ/ም ድረስ
👉 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የኦንላይን ምዝገባ ግንቦት 01 እስከ 05/2014 ዓ/ም ፤ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ግንቦት 8 እና 9/2014 ዓ/ም
👉 ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 08 እና 09/2014 ዓ.ም
👉 ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 27 እና 28/2014 ዓ/ም
👉 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 1 እና 2 /2014 ዓ/ም
👉 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 01 እና 02/2014 ዓ/ም
👉 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 29 እና 30 /2014 ዓ/ም
👉 ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 28 እስከ 30 /2014 ዓ/ም
👉 ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 28 እና 29/2014 ዓ/ም
👉 ASTU / AASTU ሚያዚያ 28 እና 29 /2014 ዓ/ም በቅጣት ግንቦት 1 /2014 ዓ/ም
👉 ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን ግንቦት 8 እና 9 ፤ ምዝገባ ግንቦት 10 እና 11
👉 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን ግንቦት 01 እና 02 /2014 ዓ/ም
👉 ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ግንቦት 12፣ 13 እና 14
ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች ጥሪ ሲያቀርቡ ተከታትለን የምናሳውቅ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጉዳይ ብቻ በ @tikvahuniversity መከታተል ይቻላል።
@tikvahethiopia
" የኢትዮጵያ እና አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲሻሻል በትኩረት ይሰራል " - አምባሳደር ስለሺ በቀለ
በአሜሪካ የኢፌዴሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ስለሺ በቀለ የሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲሻሻል በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
አምባሳደሩ ይህን ያሉት ዋሽንግተን ዲሲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና ሰራተኞች ጋር ትውውቅ ባደረጉበት ወቅት ነው።
አምባሳደር ስለሺ እንደገለጹት የሚሲዮኑ ባልደረቦች ዋና ትኩረት ዘመናትን ያስቆጠረው የሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲሻሻል ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ ላይ ይሆናል።
በዳያስፖራ ተሳትፎ፣ ህዝብ ለህዝብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ንግድና ኢንቨስትመንት፣ ገጽታ ግንባታ፣ ቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች ያለውን ትብብር ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል።
የሚሲዮኑ ባልደረቦች የአገራቱ ግንኙነት ዘመናትን ያስቆጠረውን ዲፕሎማሲያዊ መስተጋብር የሚመጥን እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በሙሉ አቅም እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
መረጃው የኤምባሲው ነው።
@tikvahethiopia
በአሜሪካ የኢፌዴሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ስለሺ በቀለ የሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲሻሻል በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
አምባሳደሩ ይህን ያሉት ዋሽንግተን ዲሲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና ሰራተኞች ጋር ትውውቅ ባደረጉበት ወቅት ነው።
አምባሳደር ስለሺ እንደገለጹት የሚሲዮኑ ባልደረቦች ዋና ትኩረት ዘመናትን ያስቆጠረው የሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲሻሻል ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ ላይ ይሆናል።
በዳያስፖራ ተሳትፎ፣ ህዝብ ለህዝብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ንግድና ኢንቨስትመንት፣ ገጽታ ግንባታ፣ ቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች ያለውን ትብብር ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል።
የሚሲዮኑ ባልደረቦች የአገራቱ ግንኙነት ዘመናትን ያስቆጠረውን ዲፕሎማሲያዊ መስተጋብር የሚመጥን እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በሙሉ አቅም እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
መረጃው የኤምባሲው ነው።
@tikvahethiopia
#Hawassa
የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ለኢንቨስትመንት የተሰጡ እና እስካሁን ያልለሙ መሬቶች ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ ወስኛለሁ አለ።
በከተማው ውስጥ ለኢንቨስትመንትና ለተለያዩ አገልግሎቶች መሬት ወስደው ካላለሙና ከአቅም በታች ካለሙ ግለሰቦችና ተቋማት እጅ መሬት ለመንጠቅ መወሰኑን አስተዳደሩ አሳውቋል።
የከተማው ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ በተለያዩ ጊዜያት ለኢንቨስትመንት ከተሰጡ በርካታ መሬቶች ውስጥ 17ቱን ከዛሬ ጀምሮ የመንጠቅና ወደ መሬት ባንክ የማስገባት ስራ ይሰራል ብሏል።
ዛሬ የሚጀመረው የመጀመሪያ ዙር ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት ያልለሙ መሬቶች ላይም እርምጃው ይቀጥላል ብሏል፤ ስራው ጥንቃቄ ሚፈልግና በባለሀብቱ ዘንድ ቅሬታ በማይፈጥር መልኩ ስለሚሰራ በዙር ማከናወን አስፈላጊ ይሆናል ሲል መምሪያው ገልጿል።
ዛሬ እርምጃው ተግባራዊ የሚሆንባቸው 10ሩ በአገልግሎት ዘርፍ ፣ 6ቱ በኢንደስትሪው ዘርፍና 1ዱ በግብርና ዘርፍ ለመሰማራት የተሰጡ መሬቶች ሲሆኑ በጥቅሉ ከ321 ሄክታር በላይ መሬት ወደ መሬት ባንክ ይገባል መባሉን የከተማው ኮሚኒኬሽን መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ለኢንቨስትመንት የተሰጡ እና እስካሁን ያልለሙ መሬቶች ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ ወስኛለሁ አለ።
በከተማው ውስጥ ለኢንቨስትመንትና ለተለያዩ አገልግሎቶች መሬት ወስደው ካላለሙና ከአቅም በታች ካለሙ ግለሰቦችና ተቋማት እጅ መሬት ለመንጠቅ መወሰኑን አስተዳደሩ አሳውቋል።
የከተማው ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ በተለያዩ ጊዜያት ለኢንቨስትመንት ከተሰጡ በርካታ መሬቶች ውስጥ 17ቱን ከዛሬ ጀምሮ የመንጠቅና ወደ መሬት ባንክ የማስገባት ስራ ይሰራል ብሏል።
ዛሬ የሚጀመረው የመጀመሪያ ዙር ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት ያልለሙ መሬቶች ላይም እርምጃው ይቀጥላል ብሏል፤ ስራው ጥንቃቄ ሚፈልግና በባለሀብቱ ዘንድ ቅሬታ በማይፈጥር መልኩ ስለሚሰራ በዙር ማከናወን አስፈላጊ ይሆናል ሲል መምሪያው ገልጿል።
ዛሬ እርምጃው ተግባራዊ የሚሆንባቸው 10ሩ በአገልግሎት ዘርፍ ፣ 6ቱ በኢንደስትሪው ዘርፍና 1ዱ በግብርና ዘርፍ ለመሰማራት የተሰጡ መሬቶች ሲሆኑ በጥቅሉ ከ321 ሄክታር በላይ መሬት ወደ መሬት ባንክ ይገባል መባሉን የከተማው ኮሚኒኬሽን መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
#ችሎት
በአዲስ አበባ ከተማ በተከበረው በዒድ አል ፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ አካባቢ የአድማ ብተና የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ፍርድ ቤት ቀረበ።
የፌደራል ፖሊስ የ 'አድማ ብተና ዘርፍ አባል' የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ከትናንት በስቲያ ሰኞ በአ/አ በተከበረው የዒድ አል ፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ ከፈነዳው የአድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውሎ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዛሬ ረፋድ ላይ ቀርቧል።
መርማሪ ፖሊስ ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በዓሉ ዕለት በተመደበበት ወንጀል የመከላከል ምደባ ላይ እያለ የታጠቀውን አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ በአግባቡ መታጠቅ ሲገባው በአግባቡ ባለመታጠቅ የጭስ ቦንቡ እንዲፈነዳና ሁከት እና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርጓል ያለው መርማሪ በዚህ በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ የመንግስትና የግለሰብ ንብረት ጉዳት መድረሱን አብራርቷል።
በተጠረጠረበት ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ወንጀል ለተጨማሪ ማስረጃ አሰባስቦ ለመቅረብ 14 ቀን እንዲሰጠው መርማሪው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ተጠርጣሪው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በበኩሉ በዕለቱ አስቀድሞ በተመደበበት ቦታ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ እንደነበር እና በሰዓቱ በቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች ቁጥር መጨመርና መጨናነቁን ተከትሎ ከታጠቀው ሶስት አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ውስጥ አንደኛው በማያውቀው ሁኔታ መሬት ላይ ወድቆበት በድንገት መፈንዳቱን ገልጿል።
ሆኖም ምንም አይነት ተንኮልም ሆነ ክፋት በውስጤ አልነበረም ወድቆ ሲፈነዳ እኔ እራሴ ደንግጬ ነበር ሲል እያለቀሰ ሁኔታውን ለችሎቱ አስረድቷል።
በተጨማሪም ተጠርጣሪው ወላጆቹን በሞት ማጣቱን ገልጾ እህትና ወንድሙን በሱ እርዳታ እያስተማራቸው እንደሆነ እና ከለሊት 7:00 ጀምሮ ለጥበቃ ስራ ከመሰማራቴ ውጪ ሌላ ክፋት በውስጤ የለም ሲል ለችሎቱ አብራርቷል።
ጉዳዩን የተከታለው ፍርድ ቤቱ ለተጨማሪ ምርመራ ለፖሊስ 14 ቀን ፈቅዷል። ለግንቦት 10 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ በተከበረው በዒድ አል ፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ አካባቢ የአድማ ብተና የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ፍርድ ቤት ቀረበ።
የፌደራል ፖሊስ የ 'አድማ ብተና ዘርፍ አባል' የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ከትናንት በስቲያ ሰኞ በአ/አ በተከበረው የዒድ አል ፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ ከፈነዳው የአድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውሎ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዛሬ ረፋድ ላይ ቀርቧል።
መርማሪ ፖሊስ ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በዓሉ ዕለት በተመደበበት ወንጀል የመከላከል ምደባ ላይ እያለ የታጠቀውን አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ በአግባቡ መታጠቅ ሲገባው በአግባቡ ባለመታጠቅ የጭስ ቦንቡ እንዲፈነዳና ሁከት እና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርጓል ያለው መርማሪ በዚህ በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ የመንግስትና የግለሰብ ንብረት ጉዳት መድረሱን አብራርቷል።
በተጠረጠረበት ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ወንጀል ለተጨማሪ ማስረጃ አሰባስቦ ለመቅረብ 14 ቀን እንዲሰጠው መርማሪው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ተጠርጣሪው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በበኩሉ በዕለቱ አስቀድሞ በተመደበበት ቦታ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ እንደነበር እና በሰዓቱ በቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች ቁጥር መጨመርና መጨናነቁን ተከትሎ ከታጠቀው ሶስት አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ውስጥ አንደኛው በማያውቀው ሁኔታ መሬት ላይ ወድቆበት በድንገት መፈንዳቱን ገልጿል።
ሆኖም ምንም አይነት ተንኮልም ሆነ ክፋት በውስጤ አልነበረም ወድቆ ሲፈነዳ እኔ እራሴ ደንግጬ ነበር ሲል እያለቀሰ ሁኔታውን ለችሎቱ አስረድቷል።
በተጨማሪም ተጠርጣሪው ወላጆቹን በሞት ማጣቱን ገልጾ እህትና ወንድሙን በሱ እርዳታ እያስተማራቸው እንደሆነ እና ከለሊት 7:00 ጀምሮ ለጥበቃ ስራ ከመሰማራቴ ውጪ ሌላ ክፋት በውስጤ የለም ሲል ለችሎቱ አብራርቷል።
ጉዳዩን የተከታለው ፍርድ ቤቱ ለተጨማሪ ምርመራ ለፖሊስ 14 ቀን ፈቅዷል። ለግንቦት 10 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
የአለም ዋንጫ ወደ ሀገራችን ይመጣል !
የ ኳታሩ የአለም ዋንጫ ከመጀመሩ አስቀድሞ የ አለም ዋንጫ ለእይታ ከሚቀርቡባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ሀገራችን ቀዳሚዋ ነች ።
የአለም ዋንጫው በዚህ ዓመት በቀዳሚነት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ የሁለት ቀን ቆይታ እንደሚኖረው ተገልጿል ።
የአለም ዋንጫው ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ሀገራችን ሲመጣ በዘንድሮው አመት ግንቦት 16 እና 17 በሀገራችን ቆይታን ያደርጋል ።
ከአለም ዋንጫው ጋር የ 1998ቱ የአለም ዋንጫ አሸናፊ የፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ ዴቪድ ትሪዝጌት እንደሚመጣ ተነግሯል ።
https://t.iss.one/tikvahethsport
@tikvahethsport
የ ኳታሩ የአለም ዋንጫ ከመጀመሩ አስቀድሞ የ አለም ዋንጫ ለእይታ ከሚቀርቡባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ሀገራችን ቀዳሚዋ ነች ።
የአለም ዋንጫው በዚህ ዓመት በቀዳሚነት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ የሁለት ቀን ቆይታ እንደሚኖረው ተገልጿል ።
የአለም ዋንጫው ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ሀገራችን ሲመጣ በዘንድሮው አመት ግንቦት 16 እና 17 በሀገራችን ቆይታን ያደርጋል ።
ከአለም ዋንጫው ጋር የ 1998ቱ የአለም ዋንጫ አሸናፊ የፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ ዴቪድ ትሪዝጌት እንደሚመጣ ተነግሯል ።
https://t.iss.one/tikvahethsport
@tikvahethsport
#Kenya
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አቅራቢያ በርካታ የፀጥታ ኃይሎችን አሰማርታለች።
በሀገሪቱ የማርሳቢት ግዛት ውስጥ በተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት ምክንያት በርካታ ሰዎች መገዳላቸውን ተከትሎ ነው በሺዎች የሚቆጠሩ ፖሊሶችና የፀጥታ ኃይሎች የተሰማሩት።
የሀገሪቱ መንግስት ለተፈጠረው የፀጥታ ችግር ድርቅ፣ ፖለቲካዊ ቅስቀሳ እና ከኢትዮጵያ የጦር መሳሪያ በቀላሉ መገኘቱ ነው ብሏል።
የኬንያ የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትር ፖሊስ ከደቡብ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ የገቡ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እና ጥይቶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ተናግረዋል።
የኬንያ መንግሥት በማርሳቢት የፀጥታ ኃይል ከማሰማራት በተጨማሪ ለአንድ ወር የሚቆይ የሰዓት እላፊ አዋጅ እንዲሁም ትጥቅ እንደሚያስፈታም ገልጿል።
በማርሳቢት ከተማ በቅርቡ የተፈጸመውን ግድያ አረመኔያዊ ሲል የኬንያ መንግሥት ያወገዘው ሲሆን በዚህም የአካባቢው አስተዳዳሪም መገደላቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አቅራቢያ በርካታ የፀጥታ ኃይሎችን አሰማርታለች።
በሀገሪቱ የማርሳቢት ግዛት ውስጥ በተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት ምክንያት በርካታ ሰዎች መገዳላቸውን ተከትሎ ነው በሺዎች የሚቆጠሩ ፖሊሶችና የፀጥታ ኃይሎች የተሰማሩት።
የሀገሪቱ መንግስት ለተፈጠረው የፀጥታ ችግር ድርቅ፣ ፖለቲካዊ ቅስቀሳ እና ከኢትዮጵያ የጦር መሳሪያ በቀላሉ መገኘቱ ነው ብሏል።
የኬንያ የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትር ፖሊስ ከደቡብ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ የገቡ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እና ጥይቶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ተናግረዋል።
የኬንያ መንግሥት በማርሳቢት የፀጥታ ኃይል ከማሰማራት በተጨማሪ ለአንድ ወር የሚቆይ የሰዓት እላፊ አዋጅ እንዲሁም ትጥቅ እንደሚያስፈታም ገልጿል።
በማርሳቢት ከተማ በቅርቡ የተፈጸመውን ግድያ አረመኔያዊ ሲል የኬንያ መንግሥት ያወገዘው ሲሆን በዚህም የአካባቢው አስተዳዳሪም መገደላቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia