TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሕብር ሙዳይ የቁጠባ ሒሳብ

ሙዳይ ተቀማጭ ሒሳብ በአነስተኛ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች የሚከፍቱት የቁጠባ ሒሳብ ሲሆን፤ አገልግሎቱ የቁጠባ ባህልን ለማዳበር አነስተኛ ገቢ ያላቸው ቆጣቢዎችን ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ ደንበኞችን ለማበረታታት በነፃ የገንዘብ ቁጠባ ሣጥኖች የሚሰጥበት የቁጠባ ሒሳብ ነው፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡

#HibirMudai #savings #financialwellness
🎁 ቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠቀሙ፤ ተጨማሪ ስጦታዎችን ያግኙ!

🚀 ገና ቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ሲጭኑ በ 100ሜ.ባ ስጦታ እንቀበልዎታለን!
💥 የመጀመሪያውን ግብይት ሲፈጽሙ ደግሞ የ15 ብር ስጦታ ይበረከትልዎታል!

በተጨማሪም በቴሌብር 100 ብር እና ከዚያ በላይ የሞባይል አየር ሰዓት ሲሞሉ 25%፣ ከ100 ብር በታች ሲሞሉ 15% እንዲሁም ጥቅል ሲገዙ 10% ተጨማሪ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

▶️ ለተጨማሪ፡ https://youtu.be/l7sSDPhPig4 ይመልከቱ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ ብቻ ባልመከኑ ተተኳሾች ከ51 በላይ ወገኖች ሲቀጠፉ ፤ ከ286 በላይ ሰዎች የአካል ጉዳት ሰለባ ሆኗል " - በትግራይ ማእከላይ ዞን የየጭላ አበርገለ ወረዳ የፀጥታ ፅ/ቤት በትግራይ በነበረው አውዳሚ እና አሰቃቂ ጦርነት ወቅት ተቀብረው እና ተጥለው ያልመከኑ ተተኳሾች የንፁሃን ዜጎችን ህይወት መቅጠፍና አካል ማጉደል ቀጥለዋል። በየጭላ አሸርገለ ወረዳ የእምባ…
#ትግራይ

ያልመከነ ተተኳሽ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወት ቀጠፈ።

ጥቅምት 21 /2017 ዓ.ም በትግራይ ማእከላይ ዞን አበረገለ ጭላ ወረዳ ስምረት ቀበሌ ገበሬ ማህበር ዘገልዋ መንደር ውስጥ ባልመከነ ተተኳሽ  ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸው ጠፍቷል።

ህይወታቸው የጠፋው ባል እና ሚስት ከ5 ዓመት ልጃቸው ጋር ነው።

የወረዳው ፓሊስ አከባቢው በትግራዩ ጦርነት ከባድ ውግያ የተካሄደበት ከመሆኑ  ጋር ተያይዞ ያልመከኑ ተተኳሾች አደጋ ሲያደርሱ ቆይቷል እያደረሱም ይገኛሉ ብሏል።

ፓሊስ እንዳለው ህይወቱ የተቀጠፈው ህፃን ወድቆ ያገኘውን ተተኳሽ ወደ ቤቱ ወስዶ ከእሳት በማነካካቱ ፈንድቶ ሦስቱ የቤተሰቡ አባላት ወድያውኑ ሞተዋል።

በወረዳው ከፕሪቶሪያ ስምምነት ወዲህ ብቻ ባልመከኑ ተተኳሾች የአሁኑን ጨምሮ ከ53 ሰዎች በላይ መሞታቸው ያስታወቀው የሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት በበኩሉ አሁንም የሚመለከተው አካል አከባቢው ካልመከኑ ተተኳሾች በማፅዳት ህዝቡ እንዲታደግ ተማጽኗል። 

መረጃው  ከወረዳው የህዝብ ግንኙነት ፅህፈት ቤት ነው የተገኘው። 

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#ኮንታ

ዛሬ በኮንታ በደረሰ የመሬት መሸራተት አደጋ 6 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ጫሬ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በቀበሌው ትናንት ምሽት የጣለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ ዛሬ ጠዋት 2 ሠዓት ላይ የመሬት መንሸራተት መከሰቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት ሲሆን ከአንደኛው ቤተሰብ አራት እንዲሁም ከሌላኛው ቤተሰብ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

መረጃው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ነው።

@tikvahethiopia
#ኦሮሚያ

በኦሮሚያ ክልል ፣ ሰሜን ሸዋ ዞን ወጫሌ ወረዳ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በርካታ ሰዎች ተገድለዋል።

ዛሬ ጥዋት ወጫሌ ወረዳ በተፈጸመው ጥቃት የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ንጉሴ ኮሩን ጨምሮ በርካቶች ነው የተገደሉት።

የወጫሌ ወረዳ አጎራባች ይሆነው አለልቱ ወረዳ ፥ የቀድሞው የወረዳው አሁን ደግሞ የወጫሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጉሴ ኮሩ መገደላቸውን አረጋግጧል።

ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ አንዲት ነዋሪው " የወረዳው አስተዳዳሪን ጨምሮ ብዙዎች ህይወታቸው አልፏል። የጉዳቱ መጠን እስካሁን የተጣራ አይመስለኝም " ብለዋል።

ጉዳት የደረሰባቸው ሆስፒታል መግባታቸው ተሰምቷል።

የወረዳው ዋና ከተማ ሙከጡሪ ከአዲስ አበባ 82 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ተቀራረቦ እንደመነጋገር የመሰለ ነገር የለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ምሽት ብዙዎችን ያነጋገር መልእክትና ፎቶ በይፋዊና በተረጋገጠ የX ገጻቸው ላይ አጋርተዋል። ፎቶው ከደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ጋር አብረው ያሉበት ነው። አቶ ጌታቸው ፤ " ከሩቅ የሚመጣ ሰው አያስፈልግም ለመቀራረቡ እኛ እንቀርባለን ብላችሁ እኛን ለማገናኘት…
ፎቶ ፦ የህወሓት አመራሮች ዛሬ በመቐለ ከተማ ፊት ለፊት ተገናኝተዋል።

የፊት ለፊት ግንኙነቱ በክልሉ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አባቶች የተመራ ነበር።

ጥዋት በመቐለ ኖርዘርን ስታር ሆቴል አዳራሽ  የነበረው የፊት ለፊት ውይይት ግማሽ ቀን የፈጀ እንደነበር ታውቋል።

የሃይማኖት አባቶቹ ፥ " ችግራቸውን በውይይት እንዲፈቱ ባቀረብናላቸው ጥሪ መሰረት ተገናኝተው ችግራቸውን በፓለቲካዊ እና በህጋዊ አሰራር እንፈታለን ብለውናል " ሲሉ አብስረዋል።

ሁለቱ ቡድኖች በመወከልና በመምራት በፊት ለፊት ውይይቱ የተገኙት ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሚድያ የሰጡት መግለጫ የለም።

አቶ ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ከቀናት በፊት ተገናኝተው አብረው የተነሱትን ፎቶ አቶ ጌታቸው በ X ገጻቸው ላይ አጋርተው መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahethiopia            
" ህጻናት ፣ እናቶች፣ አሮጊቶች ፣ ሽማግሌዎች ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " - ነዋሪዎች

በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።

በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።

ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።

" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።

" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።

" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።

ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።

" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።

ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።

" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።

በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።

" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።

አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።

" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።

" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።

የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።

" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።

ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።

ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ

@tikavhethiopia
#ኢትዮጵያ

የኩላሊት እጥበት ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ በሳምንት 3 ጊዜ እጥበት የሚያደርጉ ሕሙማን ከባድ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን፣ የኩላሊት ሕክምና እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት አስታውቋል።

ከሰሞኑም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ " መንግሥት የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ካደረገ በኋላ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም የሕክምና ተቋማት የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት አንድ ታካሚ የኩላሊት እጥበት ለአንድ ጊዜ ሲያደርግ ይፈጸም የነበረው ክፍያ 2,000 ብር እንደነበር፣ ነገር ግን የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ሲደረግ አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ተቋማት ከ3,000 እስከ 4,100 ብር እያስከፈሉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

ለኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ከውጭ ስለሚገቡ፣ የአገልግሎት ክፍያው በእጥፍ መጨመሩንና በሳምንት ሦስት ጊዜ የሚጠቀም ታካሚ አንድ ጊዜ ብቻ ለማድረግ መገደዱን አክለው ገልጸዋል፡፡

በሞት ከተለዩ ሰዎች ኩላሊት እንዲወሰድ የሚፈቅድ የሕግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ድርጅቱ ጥረት ማድረጉን፣ ጉዳዩም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን ተናግረዋል፡፡

ጉዳዩ በሕግ ማዕቀፍ ሲታገዝ በርካታ ሰዎች የኩላሊት ንቅለ ተከላ በቀላሉ እንደሚያደርጉ፣ እስከዚያው ግን ማኅበረበሰቡ ለኩላሊት ሕሙማን የተሻለ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡  

አሁን ላይ የሚመሩት ድርጅት ድጋፍ በዘውዲቱ፣ በምኒልክና በጳውሎስ የሕክምና ተቋማት የሚገኙ 210 ሕሙማን ነፃ የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ናቸው።

ይሁን እንጂ በግል ሆስፒታሎች አገልግሎት የሚያገኙ ሕሙማን በ15 ቀናት ውስጥ እጥበት ሲያደርጉ፣ ከፍተኛ ወጪ እንደሚጠብቃቸው ተጠቁሟል። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia