TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል። @tikvahethiopia
#ትኩረት🚨
ኦሞራቴ ዙሪያ 500 ሜትር እርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለዉ የመሬት መሰንጠቅ ተከስቷል።
የከተማዉ ነዋሪዎች " የመሬት መሰንጠቁ ውሀዉ መድረሱን ያሳያልና ድረሱልን " እያሉ ነው።
ከሰሞኑን የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በርካታ አርብቶ አደሮች መፈናቀላቸውንና አካባቢው በውሀው ከመጥለቅለቁ ባለፈ የወረዳው ዋና ከተማ ኦሞራቴ መቅረቡ የከተማውን ማህበረሰብ ስጋት ውስጥ እንዳስገባው ነግረናችሁ ነበር።
አሁን ደግሞ የተፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ሌላ የድንጋጤ ምክኒያት ሆኗል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች " ውሀው ከመቅረቡ ባለፈ በአካባቢው የመሬት መሰንጠቅ መፈጠሩ በነዋሪው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል " ብለዋል።
ውሀው ወደ ከተማው መጠጋቱን ለመከላከል እና አቅጣጫውን ለማስቀየር በሰው ሀይል ጥረት ቢደረግም ውሀው ውስጥ ለውስጥ መጠጋቱን የፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ይጠቁማል ብለዋል።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸዉን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አሁን ላይ ህዝቡን ያሰጋዉ አምስት መቶ ሜትር ርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው የመሬት መሰንጠቅ በመፈጠሩ ነው ብለዋል።
አንድ ዶዘር መድረሱንና ስካቫተር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው ይህም የውሀዉን አቅጣጫ ለመቀየርና ለማፍሰስ ይረዳል በማለት ይህም እየተከሰተ ያለውን የመሬት መሰንጠቅ አስቁሞ ማህበረሰቡን ያረጋጋል ብለዋል።
አሁን ላይ ምንም እንኳን ዶዘር መድረሱና ስካቫተር እየመጣ መሆኑ ተስፋ ቢሰጠንም የነዳጅ የሰዉ ሀይልና አጠቃላይ ኦፕሬሽን ኮስት ስለሚያስፈልገን የክልሉና የፌደራሉ መንግስት ሊያግዘን ይገባል ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ኦሞራቴ ዙሪያ 500 ሜትር እርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለዉ የመሬት መሰንጠቅ ተከስቷል።
የከተማዉ ነዋሪዎች " የመሬት መሰንጠቁ ውሀዉ መድረሱን ያሳያልና ድረሱልን " እያሉ ነው።
ከሰሞኑን የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በርካታ አርብቶ አደሮች መፈናቀላቸውንና አካባቢው በውሀው ከመጥለቅለቁ ባለፈ የወረዳው ዋና ከተማ ኦሞራቴ መቅረቡ የከተማውን ማህበረሰብ ስጋት ውስጥ እንዳስገባው ነግረናችሁ ነበር።
አሁን ደግሞ የተፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ሌላ የድንጋጤ ምክኒያት ሆኗል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች " ውሀው ከመቅረቡ ባለፈ በአካባቢው የመሬት መሰንጠቅ መፈጠሩ በነዋሪው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል " ብለዋል።
ውሀው ወደ ከተማው መጠጋቱን ለመከላከል እና አቅጣጫውን ለማስቀየር በሰው ሀይል ጥረት ቢደረግም ውሀው ውስጥ ለውስጥ መጠጋቱን የፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ይጠቁማል ብለዋል።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸዉን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አሁን ላይ ህዝቡን ያሰጋዉ አምስት መቶ ሜትር ርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው የመሬት መሰንጠቅ በመፈጠሩ ነው ብለዋል።
አንድ ዶዘር መድረሱንና ስካቫተር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው ይህም የውሀዉን አቅጣጫ ለመቀየርና ለማፍሰስ ይረዳል በማለት ይህም እየተከሰተ ያለውን የመሬት መሰንጠቅ አስቁሞ ማህበረሰቡን ያረጋጋል ብለዋል።
አሁን ላይ ምንም እንኳን ዶዘር መድረሱና ስካቫተር እየመጣ መሆኑ ተስፋ ቢሰጠንም የነዳጅ የሰዉ ሀይልና አጠቃላይ ኦፕሬሽን ኮስት ስለሚያስፈልገን የክልሉና የፌደራሉ መንግስት ሊያግዘን ይገባል ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨
ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።
" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።
ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።
ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።
" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።
ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።
ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።
#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።
" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።
ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።
ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።
" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።
ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።
ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።
#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
• " ቤንዝል ሙሉ በሙሉ ከጠፋ 4 ቀናት መሆኑን ተከትሎ ከስራ ውጭ ሆነናል " - በሀዋሳ ከተማና አካባቢዉ የሚገኙ አሽከርካሪዎች
• " ከጅቡቲ የተነሱ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች እስኪደርሱ በትእግስት ጠብቁ " - የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ
ከሰሞኑ በነዳጅ እጥረት ምክኒያት አልፎ አልፎ የነዳጅ ፕሮግራም ሲወጣ ቢቆይም ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ ግን ሙሉ በሙሉ ድልድል ባለመውጣቱና በከተማው ውስጥ ያሉ ሁሉም ማደያዎች " ቤንዝል የለም " በማለታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብተናል ያሉ የሀዋሳና አካባቢው አሽከርካሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አሁን ላይ በህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ አሽከርካሪዎች ስራ መፍታታቸዉን ሲገልጹ አንዳንዶች ደግሞ እጅን አጣጥፎ ላለመቀመጥ ከህገወጥ ቤንዝል ሻጮች አንድን ሊትር እስከ ከመቶ ሀምሳ ብር በላይ እየገዙ መሆኑን ይናገራሉ።
በዚህ ደረጃ ቤንዝል መጥፋቱ ግራ አጋብቶናል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ አሁን ላይ አሽከርካሪዉም ማህበረሰቡም ችግር ላይ ነው ብለዋል።
የአሽከርካሪዎቹን ቅሬታ ይዘን ያነጋገርናቸው የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ኃላፊዉ አቶ ተመስገን ችሎት " ላለፉት ሶስት ቀናት ድልድል ያልነበረው ከተማ ውስጥ የሚገኙ ማደያዎች ቤንዝል በመጨረሳቸዉ ነው " ብለዋል።
በዚህ ሰአት መንገድ የጀመሩ ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎች ከጅቡቲ መነሳታቸውን የሚገልጽ መረጃ አለን የሚሉት ኃላፊዉ እነዚህ ቦቴዎች እስኪደርሱ ሁለት ሶስት ቀናት መታገስ ይኖርብናል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" ክፍያችን ከኑሮ ውድነት አንጻር በጣም የወረደ በመሆኑ ህይወት አስቸጋሪ ሆኖብናል " - በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች
" በ1000 ብር ደሞዝ ኑሮን መቋቋም አቃተን " ያሉ የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች የሚከፈለን ገንዘብ ከቤት ኪራይ የማያልፍ በመሆኑ በረሀብ እየተሰቃየን ነው በማለት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
የረከሰ ቤት ፍለጋ ከከተማ ወጣ ያሉ ሰፈሮች በመምረጥ ሶስት አራት ሆነዉ እንደሚከራዩና ጠዋት አንድ ሰአት ለመድረስ ከአስራ ሁለት ሰአት በፊት ተነስተዉ ያውም በባዶ ሆድና በእግር እንደሚመጡ የሚናገሩት ሰራተኞቹ " አሁን ግን ኑሮ ጣሪያ በመንካቱ በዚህ መልክ እንኳን መቀጠል አልቻልንም " ብለዋል።
" ምንም እንኳን የምሳ ድጋፍ ቢደረግልንም በአንድ ከተማ በአንድ የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ያለዉ ልዩነት ያሳዝናል " በማለት በፓርኩ ውስጥ እንኳን ልዩነት መኖሩን ይገልጻሉ።
አንዳንድ ሼዶች የትራንስፖርት አገልግሎትን ጨምሮ የትርፍ ሰአት ስራ የሚያመቻቹ ቢሆንም ሌሎች ደግሞ ከአንድ ሽህ ብር ደሞዝ ውጭ ምንም ትርፍ ነገር አይሰጡም።
" በዚህም ኑሮን መግፋት ተራራ ሆኖብናል " በማለት ያሉበትን የስቃይ ህይወት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ሰራተኞቹ " በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አይደለም የቤት ኪራይ ከፍለንና የምግብ ወጭ ሸፍነን ለመኖር ይቅርና ሰርተዉ ይረዱናል ብለዉ በማሰብ ወደላኩን ቤተሰቦቻችን ለመመለስ እንኳን አስቸጋሪ ሆኖብናል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን የሰራተኞች እሮሮ ይዞ ምላሽ ለማግኘት የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክን ደጋግሞ ቢያናንኳኳም ለጊዜዉ ምላሽ ማግኘት አልቻልንም።
ይሁንና በቅርቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚው አቶ ዘመን ጁነዲን " የሰራተኛውን ምቹ ከባቢ መፍጠር የኛም ፕራይወሪቲ ነው " ብለው ነበር።
አሁን ላይ ከሚመለከታቸዉ አካላት በተለይም ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር እየተነጋገርሩ መሆኑን የገለጹት አቶ ዘመን ከክፍያ በተጨማሪ ትራንስፖርት ምግብና መሰል ድጎማዎች እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Sidama
" በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " - አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ
በሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ግምገማ መደረጉን ተከትሎ በርካታ የፖሊስ አዛዥች ከስልጣን ሲነሱ በጥቂቶች ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንደተጀመረባቸው ተሰምቷል።
ከሰሞኑ በክልሉ ሲካሄድ የሰነበተውን የግምገማና የውይይት መድረክ አሰመልክተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ " በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " ብለዋል።
" በዚህ መሰረት በተደረገ ግምገማ በክልሉ በተለያዩ ዞን ወረዳና ከተማ አስተዳደር ውስጥ
ባሉ መዋቅር ይሰሩ ከነበሩ አመራሮች ውስጥ ሰባት የፖሊስ አዛዦችና ሙሉ የአንድ ክፍለ ከተማ የማኔጅመንት አባላት ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንዲጀመር ታዟል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተደረጉ አመራሮች መካከል ፦
- የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ፣
- የሆኮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ
- የጨቤ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ይገኙበታል።
የዳዬ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ከኃላፊነታቸው ታግደው ከመልካም አስተዳደር ችግሮችና ከህገወጥ ንግድ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች እንዲጣራ ታዟል።
በተጨማሪም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ በዞኑ ህገ-ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመምጣቱና መቆጣጠር ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ሊነሱ ችለዋል።
በወረዳ ደረጃ ደግሞ የሁላ ወረዳ፣ የአለታ ጩኮ ወረዳ፣ የቡርሳ ወረዳና የጠጢቻ ወረዳ ፖሊስ አዛዦች የተነሳባቸው ጉዳዮች ተጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት አቅጣጫ ተቀምጧል።
በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ያሉ ጠቅላላ ማኔጅመንቱ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጋቸው ተነግሯል።
በመድረኩ በርካታ ችግሮች የተነሱ ሲሆን ለአብነትም ኪራይ ሰብሳቢነትና ባለጉዳይን ማማረር ጎልተዉ የተነሱ ክፍተቶች ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " - አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ
በሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ግምገማ መደረጉን ተከትሎ በርካታ የፖሊስ አዛዥች ከስልጣን ሲነሱ በጥቂቶች ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንደተጀመረባቸው ተሰምቷል።
ከሰሞኑ በክልሉ ሲካሄድ የሰነበተውን የግምገማና የውይይት መድረክ አሰመልክተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ " በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " ብለዋል።
" በዚህ መሰረት በተደረገ ግምገማ በክልሉ በተለያዩ ዞን ወረዳና ከተማ አስተዳደር ውስጥ
ባሉ መዋቅር ይሰሩ ከነበሩ አመራሮች ውስጥ ሰባት የፖሊስ አዛዦችና ሙሉ የአንድ ክፍለ ከተማ የማኔጅመንት አባላት ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንዲጀመር ታዟል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተደረጉ አመራሮች መካከል ፦
- የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ፣
- የሆኮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ
- የጨቤ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ይገኙበታል።
የዳዬ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ከኃላፊነታቸው ታግደው ከመልካም አስተዳደር ችግሮችና ከህገወጥ ንግድ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች እንዲጣራ ታዟል።
በተጨማሪም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ በዞኑ ህገ-ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመምጣቱና መቆጣጠር ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ሊነሱ ችለዋል።
በወረዳ ደረጃ ደግሞ የሁላ ወረዳ፣ የአለታ ጩኮ ወረዳ፣ የቡርሳ ወረዳና የጠጢቻ ወረዳ ፖሊስ አዛዦች የተነሳባቸው ጉዳዮች ተጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት አቅጣጫ ተቀምጧል።
በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ያሉ ጠቅላላ ማኔጅመንቱ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጋቸው ተነግሯል።
በመድረኩ በርካታ ችግሮች የተነሱ ሲሆን ለአብነትም ኪራይ ሰብሳቢነትና ባለጉዳይን ማማረር ጎልተዉ የተነሱ ክፍተቶች ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ። በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል። ተማሪዎች ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።…
#MoE #Placement
🔴 " እስካሁን ድረስ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፎርም አልሞላንም ፤ ... ውጤት የመጣላቸውን ደግሞ ዝም ብለው መድበዋል " - ተማሪዎች
⚫️ " እውነት ነው ! ጉዳዩን ለክልል ብናሳውቅም መፍትሔ አልተገኘም " - አቶ ዘሪሁን ደርጫቦ
በ2016 ዓ/ም የ 12ኛ ክፍል መውጫ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ያመጡ እና በሪሚድያል ፕሮግራም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያመሩ ተማሪዎች በተመደቡ መምህራን ፎርም እንዲሞሉ የት/ት ሚንስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወሳል።
በዚህም ሀሙስ ቀን ወደ ክፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
ይሁንና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ላይ በዲምቢቾ፣ ጌቻ እና ገነዶ ት/ት ቤቶችን እንዲሁም በጎምቦራ ወረዳ ሀቢቾ እና ቢሻና ትምህርት ቤቶች ፎርም አለመሙላታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት ጥቆማ ለማወቅ ተችሏል።
በወረዳው ያነጋገርናቸው ተማሪዎች እስካሁን ፎርም እንዳልሞሉ እና ከመምህራኖቻቸው ' ሲስተም አስቸግሮናል ' የሚል ምላሽ እንዳገኙ የነገሩን ሲሆን ውጤት የመጣላቸው እንኳን ያልመረጡት እና ፍጹም ካላቸው ውጤት ጋር የማይገናኝ ዩኒቨርሲቲ እንደደረሳቸው ነግረውናል።
በወረዳዎቹ ፎርሙን እንዲሞሉ የተወከሉት መምህራን ፎርሙን ለመሙላት ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት እንዳስቸገራቸውና መሙላት እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
" እስከ ክልል ደውለን ለማሳወቅ ብንሞክርም ጥረታችን አልተሳካም " ሲሉ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የሀዲያ ዞን ትምህርት መምሪያ አይሲቲ ዳይሬክቶሬት የሆኑት ዘሪሁን ደርጫቦ ነገሩ እውነት መሆኑን አረጋግጠዋል።
" እኚህ ብቻ ወረዳዎች አይደሉም ዛሬ ብቻ ከሻሸጎ፣ ሾኔ እና ሌሎችም ወረዳዎች እስከ 10 ከሚደርሱ ት/ትቤቶች ተደውሎልኛል" ብለውናል።
ምክንያቱ ምን ይሆን ?
" የተማሪ ዳታ ሲሞላ በአምና user name ላይ ነበር እንዲሞላ የተደረገው የአምና ካልጠፋ / Delete ካልተደረገ በስተቀር አያስገባም እኔ ደግሞ በአምና ስገባ እኔን ያስገባኝ ቤንሻንጉል ላይ ነው የኔ አካውንት ካልጠፋ ሌላኛው ዞኑ ላይ መግባት አልችልም ማለት ነው የኔን አካውንት አጥፍታችሁ ዞኑ ላይ መልሱኝ ብዬ ለክልል ባሳውቅም ሳያደርጉ ቀርተዋል እዚህ ጋር ነው ክፍተቱ የተፈጠረው።
በዚህም ምንም ወረዳዎችን ላግዝ አልቻልኩም።
የትኛው ይሙላ አይሙላ የማውቀው ነገር የለም አድሚን ስትሆን አይደለ ሚያሳይህ እኔጋ የሚመጣው የቤንሻንጉል መረጃ ነው። ይህ እንዴት እንደሆነ አላውቅም ምናልባት ፌደራል ላይ መረጃ ሲገባ ሊሆን ይችላል ስህተቱ የተፈጠረው።
ምንም መረጃ ልንለዋወጥ አልቻልንም ሪሚድያል ሙሉ በሙሉ አልተሞላም ማለት ይችላል ክልል ላይ በተደጋጋሚ ለማናገር ሞክረን ነበር ነገር ግን አልተሳካም ከወረዳ ሲደወልልኝ ወደ ክልል እየላኳቸው ቆይቻለው " ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
🔴 " እስካሁን ድረስ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፎርም አልሞላንም ፤ ... ውጤት የመጣላቸውን ደግሞ ዝም ብለው መድበዋል " - ተማሪዎች
⚫️ " እውነት ነው ! ጉዳዩን ለክልል ብናሳውቅም መፍትሔ አልተገኘም " - አቶ ዘሪሁን ደርጫቦ
በ2016 ዓ/ም የ 12ኛ ክፍል መውጫ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ያመጡ እና በሪሚድያል ፕሮግራም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያመሩ ተማሪዎች በተመደቡ መምህራን ፎርም እንዲሞሉ የት/ት ሚንስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወሳል።
በዚህም ሀሙስ ቀን ወደ ክፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
ይሁንና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ላይ በዲምቢቾ፣ ጌቻ እና ገነዶ ት/ት ቤቶችን እንዲሁም በጎምቦራ ወረዳ ሀቢቾ እና ቢሻና ትምህርት ቤቶች ፎርም አለመሙላታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት ጥቆማ ለማወቅ ተችሏል።
በወረዳው ያነጋገርናቸው ተማሪዎች እስካሁን ፎርም እንዳልሞሉ እና ከመምህራኖቻቸው ' ሲስተም አስቸግሮናል ' የሚል ምላሽ እንዳገኙ የነገሩን ሲሆን ውጤት የመጣላቸው እንኳን ያልመረጡት እና ፍጹም ካላቸው ውጤት ጋር የማይገናኝ ዩኒቨርሲቲ እንደደረሳቸው ነግረውናል።
በወረዳዎቹ ፎርሙን እንዲሞሉ የተወከሉት መምህራን ፎርሙን ለመሙላት ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት እንዳስቸገራቸውና መሙላት እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
" እስከ ክልል ደውለን ለማሳወቅ ብንሞክርም ጥረታችን አልተሳካም " ሲሉ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የሀዲያ ዞን ትምህርት መምሪያ አይሲቲ ዳይሬክቶሬት የሆኑት ዘሪሁን ደርጫቦ ነገሩ እውነት መሆኑን አረጋግጠዋል።
" እኚህ ብቻ ወረዳዎች አይደሉም ዛሬ ብቻ ከሻሸጎ፣ ሾኔ እና ሌሎችም ወረዳዎች እስከ 10 ከሚደርሱ ት/ትቤቶች ተደውሎልኛል" ብለውናል።
ምክንያቱ ምን ይሆን ?
" የተማሪ ዳታ ሲሞላ በአምና user name ላይ ነበር እንዲሞላ የተደረገው የአምና ካልጠፋ / Delete ካልተደረገ በስተቀር አያስገባም እኔ ደግሞ በአምና ስገባ እኔን ያስገባኝ ቤንሻንጉል ላይ ነው የኔ አካውንት ካልጠፋ ሌላኛው ዞኑ ላይ መግባት አልችልም ማለት ነው የኔን አካውንት አጥፍታችሁ ዞኑ ላይ መልሱኝ ብዬ ለክልል ባሳውቅም ሳያደርጉ ቀርተዋል እዚህ ጋር ነው ክፍተቱ የተፈጠረው።
በዚህም ምንም ወረዳዎችን ላግዝ አልቻልኩም።
የትኛው ይሙላ አይሙላ የማውቀው ነገር የለም አድሚን ስትሆን አይደለ ሚያሳይህ እኔጋ የሚመጣው የቤንሻንጉል መረጃ ነው። ይህ እንዴት እንደሆነ አላውቅም ምናልባት ፌደራል ላይ መረጃ ሲገባ ሊሆን ይችላል ስህተቱ የተፈጠረው።
ምንም መረጃ ልንለዋወጥ አልቻልንም ሪሚድያል ሙሉ በሙሉ አልተሞላም ማለት ይችላል ክልል ላይ በተደጋጋሚ ለማናገር ሞክረን ነበር ነገር ግን አልተሳካም ከወረዳ ሲደወልልኝ ወደ ክልል እየላኳቸው ቆይቻለው " ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" የመምህራን ደመወዝ አለመከፈልና መቆራረጥ ትምህርታችን ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ ነዉ "- በከምባታ ዞን የሚገኙ ተማሪዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ከምባታ ዞን ስር በሚገኙ ወረዳዎች ዉስጥ ባሉ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች " የበጀት እጥረት " እየተባለ በሚነገራቸዉ ምክንያት የመምህራን ወርሃዊ ደመወዝ መቆራረጥና መዘግየት በትምህርታቸው ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ ስለመሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቅሬታ ካሰሙ ተማሪዎች መካከል በዳንቦያ ወረዳ የፉንጦ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ፣ በቃዲዳ ጋሜላ ወረዳ ጆሬ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ እንዲሁም በሀዳሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ አመሌቃ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህረት ቤት ተማሪዎች ይገኙበታል።
ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያሰሙ ተማሪዎች ምን አሉ ?
- በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ምክንያት መምህራን በተደጋጋሚ ከት/ት ቤት ስለሚቀሩ በየወሩ ከ5-14 ቀናት የማንማርበት አጋጣሚ እየተዘወተረ መጥቷል።
- አንዳንዶቻችን ወደ ትምህርት ቤት ከ30 ደቂቃ በላይ በእግር ተጉዘን ከደረስን በኋላ " በደሞዝ ምክንያት መምህራን አልገቡም " እንባላለን።
- አሁን አሁን በደመወዝ ወቅት መረጃ እየተቀባበልን ለመምህራን ደሞዝ አለመከፈሉን ካረጋገጥን ከትምህርት ቤት እንቀራለን።
- ይህ ተግባር እየተዘወተረ መምጣቱን ተከትሎ በርካታ ወጣቶች ዉሏቸዉን ወደ ፑልና ጆቶኒ ጫወታዎች አዙረዋል።
- ትምህርታቸውን አቋርጠዉ የሚያገቡ ሴት ተማሪዎችም አሉ።
- አከባቢያችን በብዛት ወጣቶች ወደ ዉጪ ሀገራት ከሚሰደዱባቸዉ አንዱና ዋነኛው ነዉ። ባለፈዉ ዓመት በትምህርቱ ላይ ተስፋ ቆርጦ አቋርጦ የተሰደደ ተማሪ አለ።
- ቅሬታችንን ለየትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና ዩኒት ሊደሮች እኛም ወላጆቻችንም በተደጋጋሚ አቅርበናል ግን " የደመወዝ ጉዳይ ከትምህርት ቤት አቅም በላይ ነዉ፤ መምህራን ሳይበሉና ሳይጠጡ አስተምሩ ብለን ማስገደድ አንችልም " የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መከካል ዘንድሮ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ተፈታኞች እንደሆኑ የነገሩን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች " የዘመናት ልፋታችንና የወደፊት ህልማችን አደጋ ላይ እየወደቀ ነዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሔ " ይስጡልን ብለዋል።
" ለሀገር አቀፉ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለመዘጋጀት ተጨማሪ የቲቶሪያል ትምህርት ሊሰጠን ቀርቶ መደበኛ የትምህርት መረሃግብሮች በአግባቡ አይሸፈኑም አሁን በዚህ ወቅት እንኳን አንዳንድ የትምህርት ዓይነቶች ገና አንድና ሁለት ዩኒቶችን (ምዕራፎችን) ብቻ ነዉ በተንጠባጠበ ሁኔታ የተማርነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
መምህራን ምን አሉ ?
" ብዙ ጊዜ ጮኼን ሰሚ አላገኘንም " የሚሉት በከንባታ ዞን የዳንቦያ፣ ሀዳሮ ጡንጦና ቃዲዳ ጋሜላ ወረዳዎች የሚያስተምሩ መምህራን " የደመወዝ በወቅቱ አለመከፈል፣ መቆራረጥና አልፎ አልፎም በፐርሰንት የመክፈል ችግሮች ባላፉት ሁለት ዓመታት እየተባባሱ መጥተዋል ፤ በርካታ መምህራን በዚህ ምክንያት ስራ ገበታቸዉ ላይ በአግባቡ አይገኙም " ሲሉ ገልፀዋል።
የከንባታ ዞን መምህራን ማህበር ተወካይ አቶ አለሙ አቡዬ ምን አሉ ?
° የደመወዝ መዘግየትና እያቆራረጡ መክፈል በከንባታ ዞን ባሉ ሁሉም መዋቅሮች እየተለመደ መጥቷል።
° ችግሩን ለመቅረፍ የሚደረጉ ተግባራት ጉዳዩ ከሚያስፈልገዉ ትኩረትና ከሚያሳድረዉ ተፅእኖ አንፃር በጣም ዝቅተኛ ነዉ።
የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳዊት ለገሠ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ፤ ችግሩ ባለፉት ጊዜያት ዞኑ ያለበትን የብድር ዕዳ ተከትሎ በተከሰተ የበጀት እጥረት በሁሉም የመንግስት መዋቅሮች የሚስተዋል ነው።
" የዞኑ መንግስት ካቢኔ መምህራንን ጨምሮ ለፀጥታ፣ ፍትህ እና የጤና ባለሙያዎች ደመወዝ ቅድሚያ ተሰጥቶ እንዲከፈል ባሳለፈዉ ዉሳኔ መሰረት እየተተገበረ ነዉ " ብለዋል።
" አንዳንድ ወረዳዎች የኋላውን እየሸፈኑና በብድር የተጠቀሟቸዉን በጀቶች እያተካኩ በሚሄዱበት ወቅት የደሞዝ መዘግየቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። የመማር ማስተማሩ ተግባር እንዳይቆራረጥ በተቻለ መጠን ሁሉ የዞኑና የክልሉም መንግስት ትኩረት ነዉ " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ከምባታ ዞን ስር በሚገኙ ወረዳዎች ዉስጥ ባሉ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች " የበጀት እጥረት " እየተባለ በሚነገራቸዉ ምክንያት የመምህራን ወርሃዊ ደመወዝ መቆራረጥና መዘግየት በትምህርታቸው ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ ስለመሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቅሬታ ካሰሙ ተማሪዎች መካከል በዳንቦያ ወረዳ የፉንጦ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ፣ በቃዲዳ ጋሜላ ወረዳ ጆሬ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ እንዲሁም በሀዳሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ አመሌቃ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህረት ቤት ተማሪዎች ይገኙበታል።
ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያሰሙ ተማሪዎች ምን አሉ ?
- በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ምክንያት መምህራን በተደጋጋሚ ከት/ት ቤት ስለሚቀሩ በየወሩ ከ5-14 ቀናት የማንማርበት አጋጣሚ እየተዘወተረ መጥቷል።
- አንዳንዶቻችን ወደ ትምህርት ቤት ከ30 ደቂቃ በላይ በእግር ተጉዘን ከደረስን በኋላ " በደሞዝ ምክንያት መምህራን አልገቡም " እንባላለን።
- አሁን አሁን በደመወዝ ወቅት መረጃ እየተቀባበልን ለመምህራን ደሞዝ አለመከፈሉን ካረጋገጥን ከትምህርት ቤት እንቀራለን።
- ይህ ተግባር እየተዘወተረ መምጣቱን ተከትሎ በርካታ ወጣቶች ዉሏቸዉን ወደ ፑልና ጆቶኒ ጫወታዎች አዙረዋል።
- ትምህርታቸውን አቋርጠዉ የሚያገቡ ሴት ተማሪዎችም አሉ።
- አከባቢያችን በብዛት ወጣቶች ወደ ዉጪ ሀገራት ከሚሰደዱባቸዉ አንዱና ዋነኛው ነዉ። ባለፈዉ ዓመት በትምህርቱ ላይ ተስፋ ቆርጦ አቋርጦ የተሰደደ ተማሪ አለ።
- ቅሬታችንን ለየትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና ዩኒት ሊደሮች እኛም ወላጆቻችንም በተደጋጋሚ አቅርበናል ግን " የደመወዝ ጉዳይ ከትምህርት ቤት አቅም በላይ ነዉ፤ መምህራን ሳይበሉና ሳይጠጡ አስተምሩ ብለን ማስገደድ አንችልም " የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን።
ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መከካል ዘንድሮ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ተፈታኞች እንደሆኑ የነገሩን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች " የዘመናት ልፋታችንና የወደፊት ህልማችን አደጋ ላይ እየወደቀ ነዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሔ " ይስጡልን ብለዋል።
" ለሀገር አቀፉ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለመዘጋጀት ተጨማሪ የቲቶሪያል ትምህርት ሊሰጠን ቀርቶ መደበኛ የትምህርት መረሃግብሮች በአግባቡ አይሸፈኑም አሁን በዚህ ወቅት እንኳን አንዳንድ የትምህርት ዓይነቶች ገና አንድና ሁለት ዩኒቶችን (ምዕራፎችን) ብቻ ነዉ በተንጠባጠበ ሁኔታ የተማርነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
መምህራን ምን አሉ ?
" ብዙ ጊዜ ጮኼን ሰሚ አላገኘንም " የሚሉት በከንባታ ዞን የዳንቦያ፣ ሀዳሮ ጡንጦና ቃዲዳ ጋሜላ ወረዳዎች የሚያስተምሩ መምህራን " የደመወዝ በወቅቱ አለመከፈል፣ መቆራረጥና አልፎ አልፎም በፐርሰንት የመክፈል ችግሮች ባላፉት ሁለት ዓመታት እየተባባሱ መጥተዋል ፤ በርካታ መምህራን በዚህ ምክንያት ስራ ገበታቸዉ ላይ በአግባቡ አይገኙም " ሲሉ ገልፀዋል።
የከንባታ ዞን መምህራን ማህበር ተወካይ አቶ አለሙ አቡዬ ምን አሉ ?
° የደመወዝ መዘግየትና እያቆራረጡ መክፈል በከንባታ ዞን ባሉ ሁሉም መዋቅሮች እየተለመደ መጥቷል።
° ችግሩን ለመቅረፍ የሚደረጉ ተግባራት ጉዳዩ ከሚያስፈልገዉ ትኩረትና ከሚያሳድረዉ ተፅእኖ አንፃር በጣም ዝቅተኛ ነዉ።
የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳዊት ለገሠ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ፤ ችግሩ ባለፉት ጊዜያት ዞኑ ያለበትን የብድር ዕዳ ተከትሎ በተከሰተ የበጀት እጥረት በሁሉም የመንግስት መዋቅሮች የሚስተዋል ነው።
" የዞኑ መንግስት ካቢኔ መምህራንን ጨምሮ ለፀጥታ፣ ፍትህ እና የጤና ባለሙያዎች ደመወዝ ቅድሚያ ተሰጥቶ እንዲከፈል ባሳለፈዉ ዉሳኔ መሰረት እየተተገበረ ነዉ " ብለዋል።
" አንዳንድ ወረዳዎች የኋላውን እየሸፈኑና በብድር የተጠቀሟቸዉን በጀቶች እያተካኩ በሚሄዱበት ወቅት የደሞዝ መዘግየቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። የመማር ማስተማሩ ተግባር እንዳይቆራረጥ በተቻለ መጠን ሁሉ የዞኑና የክልሉም መንግስት ትኩረት ነዉ " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች
ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።
ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።
" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች
ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።
ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።
" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ከ10 ሄክታር በላይ የፓርኩ ክፍል በቃጠሎ ወድሟል " - የማዜ ብሔራዊ ፓርክ
ከትናትና በስቲያ ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5 ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።
የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣ በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።
አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።
በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።
የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣አቦሸማኔ፣የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ከትናትና በስቲያ ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5 ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።
የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣ በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።
አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።
በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።
የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣አቦሸማኔ፣የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በትራፊክ አደጋ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ " ሽቆ " ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ቡና ጭኖ ከሳይት ሲወጣ የነበረ የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 18766 ኦሮ የሆነ የጭነት መኪና ተገልብጦ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱም ታእላውቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነት ቁጥጥር ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ሽንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፥ በመኪናዉ ላይ ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ አስር ሰዎች ነበሩ።
ስምንቱ ገዳ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የቡና ሳይት የሚሰሩ ታዳጊ ወጣቶች እንደነበሩና በአደጋው ወቅት መኪናዉ ሲገለበጥ ቡናዉ በላያቸዉ ላይ በመጫኑ 6ቱ ወዲያዉኑ ሲሞቱ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ የመጀመሪያ ሕክምና በአለታ ወንዶ ሆስፒታል ከተደረገላቸው በኋላ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሀዋሳ መላካቸውን ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል አስታዉቀዋል።
ዋና ኢንስፐክተሩ ሹፌሩና ረዳቱ በአሁኑ ሰዓት በአለታ ወንዶ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።
በክልሉ በቡና ምርት ወቅት የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ለትራፊክ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድልን ከፍ እንደሚያደርጉ በትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዙሪያ በሁሉም መዋቅሮች ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ ቢሆንም በቸልተኝነትና ከልክ ባለፈ በራስ መተማመን በገጠሪቱ አከባቢዎች አደጋዎች እንደሚከሰቱ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ " ሽቆ " ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ቡና ጭኖ ከሳይት ሲወጣ የነበረ የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 18766 ኦሮ የሆነ የጭነት መኪና ተገልብጦ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።
ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱም ታእላውቋል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነት ቁጥጥር ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ሽንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፥ በመኪናዉ ላይ ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ አስር ሰዎች ነበሩ።
ስምንቱ ገዳ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የቡና ሳይት የሚሰሩ ታዳጊ ወጣቶች እንደነበሩና በአደጋው ወቅት መኪናዉ ሲገለበጥ ቡናዉ በላያቸዉ ላይ በመጫኑ 6ቱ ወዲያዉኑ ሲሞቱ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ የመጀመሪያ ሕክምና በአለታ ወንዶ ሆስፒታል ከተደረገላቸው በኋላ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሀዋሳ መላካቸውን ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል አስታዉቀዋል።
ዋና ኢንስፐክተሩ ሹፌሩና ረዳቱ በአሁኑ ሰዓት በአለታ ወንዶ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።
በክልሉ በቡና ምርት ወቅት የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ለትራፊክ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድልን ከፍ እንደሚያደርጉ በትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዙሪያ በሁሉም መዋቅሮች ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ ቢሆንም በቸልተኝነትና ከልክ ባለፈ በራስ መተማመን በገጠሪቱ አከባቢዎች አደጋዎች እንደሚከሰቱ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ከአደጋው በህይወት የተረፈ የለም " - የሶባ ቦሩ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን
በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሶባ ቦሩ ወረዳ በወርቅ ቁፋሮ ስራ ላይ የነበሩ 8 ሰዎች ላይ አፈር ተደርምሶባቸዉ የሁሉም ሕይወት ማለፉን የወረዳዉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ አሸናፊ ድንቆ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋው በትላንትናው ዕለት ከቀኑ 9 ሰዓት አከባቢ ' ቃንጣቻ ' ተብሎ በሚጠራዉ ቀበሌ በባህላዊ መንገድ የወርቅ ማዕድን በማዉጣት ስራ ላይ በነበሩ 8 ሰዎች ላይ መድረሱን ኃላፊዉ ገልጸዋል።
በአከባቢዉ የሚስተዋለዉ ባህላዊ የወርቅ አወጣጥ ስርዓትና በቸልተኝነት የሚደረጉ ሽሚያዎች ለናዳዉ ምክንያት ሊሆን ይችላል ያሉት ኃላፊዉ ሟቾቹ ሁሉም ወንዶች መሆናቸው አስታዉቀዋል።
የአስከሬን ፍለጋዉ ሂደት ፈታኝ እንደነበር ገልጸው አደጋዉ ከደረሰበት ሰዓት አንስቶ እስከ ምሽቱ አምስት ሰዓት ድረስ በሰዉ ሃይልና በማሽን በመታገዝ የፍለጋ ስራዉ መከናወኑንና በዛሬው ዕለት የሁሉም የቀብር ሥነ ስርዓት መፈፀሙን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
አቶ አሸናፊ የጉጂ ዞን ሰባ ቦሮ ወረዳ በወርቅ ፣ ታንታሌም ፣ አምርላንድን በመሳሰሉ የማዕድን ሃብቶች የበለፀገ አካባቢ መሆኑንና ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ በርካታ ሰዎች በማዕድን ማዉጣት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚሰሩ ገልፀዉ ከዚህ ቀደም አከባቢዉ ላይ መሰል አደጋዎች ተከስተዉ እንደማያውቁም ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሶባ ቦሩ ወረዳ በወርቅ ቁፋሮ ስራ ላይ የነበሩ 8 ሰዎች ላይ አፈር ተደርምሶባቸዉ የሁሉም ሕይወት ማለፉን የወረዳዉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ አሸናፊ ድንቆ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋው በትላንትናው ዕለት ከቀኑ 9 ሰዓት አከባቢ ' ቃንጣቻ ' ተብሎ በሚጠራዉ ቀበሌ በባህላዊ መንገድ የወርቅ ማዕድን በማዉጣት ስራ ላይ በነበሩ 8 ሰዎች ላይ መድረሱን ኃላፊዉ ገልጸዋል።
በአከባቢዉ የሚስተዋለዉ ባህላዊ የወርቅ አወጣጥ ስርዓትና በቸልተኝነት የሚደረጉ ሽሚያዎች ለናዳዉ ምክንያት ሊሆን ይችላል ያሉት ኃላፊዉ ሟቾቹ ሁሉም ወንዶች መሆናቸው አስታዉቀዋል።
የአስከሬን ፍለጋዉ ሂደት ፈታኝ እንደነበር ገልጸው አደጋዉ ከደረሰበት ሰዓት አንስቶ እስከ ምሽቱ አምስት ሰዓት ድረስ በሰዉ ሃይልና በማሽን በመታገዝ የፍለጋ ስራዉ መከናወኑንና በዛሬው ዕለት የሁሉም የቀብር ሥነ ስርዓት መፈፀሙን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
አቶ አሸናፊ የጉጂ ዞን ሰባ ቦሮ ወረዳ በወርቅ ፣ ታንታሌም ፣ አምርላንድን በመሳሰሉ የማዕድን ሃብቶች የበለፀገ አካባቢ መሆኑንና ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ በርካታ ሰዎች በማዕድን ማዉጣት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚሰሩ ገልፀዉ ከዚህ ቀደም አከባቢዉ ላይ መሰል አደጋዎች ተከስተዉ እንደማያውቁም ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።
በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።
ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።
" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።
ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?
የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።
" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።
" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።
በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።
ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።
" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።
ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?
የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።
" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።
" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ልታስመርቀዉ ከቤተሰቦቿ ተደብቃ የመጣች እጮኛዉን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የገደለዉ ግለሰብ በ20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ጉርባ በሚባል ቀበሌ የገዛ እጮኛዉን ጭካኔ በተሞላበት መልኩ በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት አንገቷን በመቁረጥ ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገዉ ወጣት በፅኑ እስራት መቀጣቱን የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ ነሐሴ 16/2016 ዓ/ም በአርባምንጭ ከተማ ጉርባ ቀበሌ ነው።
ተከሳሽ ዮናስ ጫፊቄ የተባለው ግለሰብ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ዓመት ተማሪ የሆነችዉን ሟች ሊዲያ ዮሐንስ እሱን ለማስመረቅ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ በመጣችበት ተከራይቶ በሚኖርበት ቤት አሰቃቂ ድርጊቱን መፈፀሙን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።
ወጣቷ " እጮኛዬ ይመረቅልኛል " በሚል ደስታ ከቤተሰቦቿ ተደብቃ ተከሳሽ ተከራይቶ ወደ ሚማርበት ቤት መጥታ በዋዜማዉ ለምረቃዉ የሚሆኑ የዲኮር፣ የዳቦና ለስላሳ መጠጦችና በቡና ዝግጅት ቤቱን አሰማምራ በምሽቱም ግቢ ዉስጥ ያሉ ተከራዮችን ጠርተዉ ከሸኙ በኋላ ሟች ሀገር ሰላም ብላ በተኛችበት ከሌሊቱ 7 ሰዓት ገደማ እራሷን መከላከል በማትችልበት ሁኔታ በቢላዋ አንገቷን አርዶ መግደሉን የምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርገው ፖሊስ አዛዡ ገልፀዋል።
ፖሊስ አዛዡ አክለው እንደገለጹት ፥ በወቅቱ በተደረገዉ ማጣራትም ሆነ በክስ መዝገቡ ላይ እንደሰፈረዉ ወንጀለኛው " ወደ ዩኒቨርሲቲ በሄድሽበት ሌላ የወንድ ጓደኛ ይዘሻል " በሚል ነው በር ዘግቶ አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው።
ፖሊስ በዚህ ዘግናኝ ወንጀል ዙሪያ ተገቢዉን ማጣራትና ምርመራ አድርጎ ለዐቃቤ ሕግ ማቅረቡን አስታውቀዋል።
ዐቃቤ ሕግም ክስ በመመስረት ለፍርድ ቤቱ ተከሳሽ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን የሰዉ፣ የሰነድና የህክምና ማስረጃዎችን በማቅረብ አስረድቷል።
በቀረቡ ማስረጃዎች እና ምስክሮች ግራ ቀኙን ሲያጣራ የቆየዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት በቀን 29/5/2017 ዓም በዋለዉ ችሎት ተከሳሽ ዮናስ ጨፊቄ በተከሰሰበት በአሰቃቂ ሁኔታ ነብስ የማጥፋት ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑንም ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ጉርባ በሚባል ቀበሌ የገዛ እጮኛዉን ጭካኔ በተሞላበት መልኩ በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት አንገቷን በመቁረጥ ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገዉ ወጣት በፅኑ እስራት መቀጣቱን የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ ነሐሴ 16/2016 ዓ/ም በአርባምንጭ ከተማ ጉርባ ቀበሌ ነው።
ተከሳሽ ዮናስ ጫፊቄ የተባለው ግለሰብ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ዓመት ተማሪ የሆነችዉን ሟች ሊዲያ ዮሐንስ እሱን ለማስመረቅ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ በመጣችበት ተከራይቶ በሚኖርበት ቤት አሰቃቂ ድርጊቱን መፈፀሙን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።
ወጣቷ " እጮኛዬ ይመረቅልኛል " በሚል ደስታ ከቤተሰቦቿ ተደብቃ ተከሳሽ ተከራይቶ ወደ ሚማርበት ቤት መጥታ በዋዜማዉ ለምረቃዉ የሚሆኑ የዲኮር፣ የዳቦና ለስላሳ መጠጦችና በቡና ዝግጅት ቤቱን አሰማምራ በምሽቱም ግቢ ዉስጥ ያሉ ተከራዮችን ጠርተዉ ከሸኙ በኋላ ሟች ሀገር ሰላም ብላ በተኛችበት ከሌሊቱ 7 ሰዓት ገደማ እራሷን መከላከል በማትችልበት ሁኔታ በቢላዋ አንገቷን አርዶ መግደሉን የምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርገው ፖሊስ አዛዡ ገልፀዋል።
ፖሊስ አዛዡ አክለው እንደገለጹት ፥ በወቅቱ በተደረገዉ ማጣራትም ሆነ በክስ መዝገቡ ላይ እንደሰፈረዉ ወንጀለኛው " ወደ ዩኒቨርሲቲ በሄድሽበት ሌላ የወንድ ጓደኛ ይዘሻል " በሚል ነው በር ዘግቶ አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው።
ፖሊስ በዚህ ዘግናኝ ወንጀል ዙሪያ ተገቢዉን ማጣራትና ምርመራ አድርጎ ለዐቃቤ ሕግ ማቅረቡን አስታውቀዋል።
ዐቃቤ ሕግም ክስ በመመስረት ለፍርድ ቤቱ ተከሳሽ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን የሰዉ፣ የሰነድና የህክምና ማስረጃዎችን በማቅረብ አስረድቷል።
በቀረቡ ማስረጃዎች እና ምስክሮች ግራ ቀኙን ሲያጣራ የቆየዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት በቀን 29/5/2017 ዓም በዋለዉ ችሎት ተከሳሽ ዮናስ ጨፊቄ በተከሰሰበት በአሰቃቂ ሁኔታ ነብስ የማጥፋት ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑንም ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
🔊 #የሠራተኞችድምጽ
" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።
በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።
ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።
" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።
" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።
የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።
በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።
የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።
በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።
ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።
" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።
" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።
የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።
በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።
የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" በአደጋው ሁለት ሰዎች ወዲያዉኑ ሲሞቱ ስራ ላይ የነበረ አንድ ተረኛ የፖሊስ አባልን ጨምሮ በሶሰት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል" - የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ
ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ገደማ መነሻዉን ሻሸመኔ ያደረገ ኮድ (3) - B311533 AA የሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ሶዶ ከተማ ሲደርስ ባደረሰዉ የትራፊክ አደጋ በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እንደ ፖሊስ አዛዡ ገለፃ ከኦሮሚያ ክልል አርሲ አከባቢ የግብርና ምርት / ሙሉ ቲማቲም / ጭኖ የነበረዉ ተሽከርካሪ ሶዶ ከተማ ' ሲዳር ቄራ ' በሚባለዉ አከባቢ በከተማዉ በሞተር ሳይክል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት ሰዎችን ገጭቶ ወዲያዉ ሕይወታቸዉ አልፏል።
በተመሳሳይ መልኩ የምሽት ተረኛ የነበረ አንድ የፖሊስ መርማሪም ጥሪ ተደርጎለት በሞተር ሳይክል ጥሪ ወደተደረገለት ስፍራ ሲንቀሳቀስ ይሄዉ ተሽከርካሪ ገጭቶት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የፖሊስ አዛዡ ገልጸዋል።
አደጋ አድራሹ ተሽከሪካሪ አራት የመብራት ፖሎችን ከገጨ በኋላ ዲች ዉስጥ ገብቶ የቆመ ሲሆን በአሽከርካሪዉና ረዳቱ ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበት የፖሊስ መርማሪ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸዉ ሹፌሩና ረዳቱም በኦቶና አጠቃላይ ሆስፒታል በሕክምና ላይ መሆናቸዉን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አጠቃላይ በአደጋዉ 2 የሞት፣ 1 ከባድና 2 ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም 7 የንብረት ጉዳት መድረሱን አሳውቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ገደማ መነሻዉን ሻሸመኔ ያደረገ ኮድ (3) - B311533 AA የሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ሶዶ ከተማ ሲደርስ ባደረሰዉ የትራፊክ አደጋ በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እንደ ፖሊስ አዛዡ ገለፃ ከኦሮሚያ ክልል አርሲ አከባቢ የግብርና ምርት / ሙሉ ቲማቲም / ጭኖ የነበረዉ ተሽከርካሪ ሶዶ ከተማ ' ሲዳር ቄራ ' በሚባለዉ አከባቢ በከተማዉ በሞተር ሳይክል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት ሰዎችን ገጭቶ ወዲያዉ ሕይወታቸዉ አልፏል።
በተመሳሳይ መልኩ የምሽት ተረኛ የነበረ አንድ የፖሊስ መርማሪም ጥሪ ተደርጎለት በሞተር ሳይክል ጥሪ ወደተደረገለት ስፍራ ሲንቀሳቀስ ይሄዉ ተሽከርካሪ ገጭቶት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የፖሊስ አዛዡ ገልጸዋል።
አደጋ አድራሹ ተሽከሪካሪ አራት የመብራት ፖሎችን ከገጨ በኋላ ዲች ዉስጥ ገብቶ የቆመ ሲሆን በአሽከርካሪዉና ረዳቱ ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበት የፖሊስ መርማሪ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸዉ ሹፌሩና ረዳቱም በኦቶና አጠቃላይ ሆስፒታል በሕክምና ላይ መሆናቸዉን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አጠቃላይ በአደጋዉ 2 የሞት፣ 1 ከባድና 2 ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም 7 የንብረት ጉዳት መድረሱን አሳውቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia