#Oromia
🕊 " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም ! " - ነዋሪዎች
🟢 " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
⚪ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው፤... ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ ይሰጣል " - ጃል ሰኚ
⚫ " ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው " - ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ለድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት
ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የቀድሞው የማዕከላዊ ዞን አዛዥ ጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል።
የስምምነት ሰነዱ ምን እንደያዘ ፣ ምን ምን ጉዳዮች ላይ መግባባት ተደርሶ ስምምነት እንደተፈረመ ፣ በጃል ሰኚ ስር ምን ያህል ታጣቂ ወደ ሰላም እንደሚመለስ (በቁጥር) ፣ የነዚህ ታጣቂዎች ቀጣይ እጣ ፋንታ ምን እንደሆነ በይፋና በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።
ነገር ግን የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ይህ የሰላም ስምምነት ለዜጎች እረፍትን የሚሰጥ ሰላም የሚያሰርጽ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፤ " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " ብለዋል።
" የኦሮሞ ህዝብ በባህልና በወጉ መሰረት በሮቹን ጠምዶና ፈረሶችን ጭኖ በመውጣት ሰላም ይውረድ ባለው መሰረት ጥሪውን ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በራሴና በክልሉ መንግስት ስም አመሠግናለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህ ሂደት ትልቁን ስራ ለሰራው ሀገር መከላከያ ሠራዊት ምስጋና አቅርበዋል።
ጃል ሰኚ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የኦሮሞ ህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዓለም ላይ የሰው ልጅ የፖለቲካ ልዩነት አለው ፤ እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት ይልቅ በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው " ብለዋል።
ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ውጭ ሀገር ለሰላም ድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ባወጣው መግለጫ " ስምምነቱ ህዝቡን ለማምታታ የተፈጸመ ነው " ሲል ተችቷል።
ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው ብሏል።
ያም ሆነ ይህ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተነግሯል።
ለመሆኑ ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በርካታ ታጣቂዎች ወደተዘጋጀላቸው ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የታጣቂ አባላት የሰላም መንገድ መርጠው በተለይ በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እየተመለሱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ምዕራብ ሸዋ ጮቢ፣ ኢልፈታ፣ ዳኖ እና ጅባት ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ እና ዳው በሚባሉ ወረዳዎች የቡድኑ አባላት ቅብላ እየተደተገላቸው ነው።
ጃለታ አበበ ፤ " ትላንት እና ዛሬ ብቻ 7 መኪና ነው የተሃድሶ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ዞን ከተማ የገቡት። የሰላም ጥሪውን ከተቀበሉት ምንም የቀሩ አይመስለኝም ፤ ክላሽ መትረየስ እና ስናይፐር ይዘው ነው ያሉት " ብለዋል።
" ኢልፈታ፣ ግንደበረት ፣ ወዴሳና አምቦ አጠቃላይ ምእራብ ሸዋ ላይ ብዙ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባል የሰላም ጥሪ ተቀብሎ እየገባ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በዚህ ልክ የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የተመለሰ የታጣቂ ቡድን አባላትን አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጀልዱ ወረዳ በተመሳሳይ ቅበላ እየተደረገላቸው እንደነበር ተሰምቷል።
አቶ ግርማ ሌሎ የጀልዱ ወረዳ ኪልቤ ቀበሌ አስታዳዳሪ ፥ " በትክክልም በሁሉም አቅጣጫ እየተመለሱ ናቸው። ዛሬ እና ትላንት ጀልዱ ወረዳ ጉጁ ከተማ ሲደረሱ ሰው ሁሉ ወጥቶ ሲመለከታቸው ነበር " ብለዋል።
" መጀመሪያ ሲመጡ በየቀበሌያቸው በየቦታው ይሰበሰባሉ ከዛ ወደ መንግሥት ኃይሎች ስልክ ደውለው ነው የቅበላ ሰርዓት የሚደረገው። በጀልዱ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ነው እየተበልን ያለነው " ሲሉ አክለዋል።
ዊቱሺኩቴ፣ ኢልኬ ፣ጎሮ ቀበሌዎች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የመጡባቸው እንደሆኑ ጠቁመዋል።
አሁን ላይ በጃል ሰኚ የሚመሩት የሰላም አማራጭ ተከትለው እየተመለሱ ቢሆንም የሌሎች የቀሩትን እንደማያውቁ አቶ ግርማ ገልጸዋል።
" የህዝቡን ፍላጎት ተመልክተው ይመለሳሉ ብለን እናምናለን " ብለዋል።
ባለፈው ጥቅምት ወር በኪልቤ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና በመንግሥት የፀጥታ አካላት መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ የብዙ ሰው ህይወት አልፏል።
" አሁን ሰላም መውረዱ መሰል የሰው ህይወት ቀጥፈትን ይታደጋል " ሲሉ አቶ ግርማ ተናግረዋል።
እርስ በእርስ መተኳኮሱ ከቆመ በአካባቢው የተደናቀፈው ልማት ይቀጥላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ፤ የህዝቡ ፍላጎትን ስለሚያስጠብቅ ሰላም መውረዱ አስደሳች እንደሚሆን አክለዋል።
የጮቢ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ጃለታ በቀለ ፤ " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም። አሁን ህዝቡ ለ5 ዓመታት በቀጠለው ጦርነት ተጎድቷል መንግሥት እና ግብረሰናይ ድርጅቶች የህዝቡ ህይወት የሚንሰራራበትን መላ ይዘው ቢመጡ መልካም ነው " ብለዋል።
[ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዋሪዎች ቃል ምንጭ ቪኦኤ አፋን ኦሮሞ ሬድዮ እንደሆነ ይገልጻል ]
ኦሮሚያ ባለፉት አመታት ?
ከ6 ዓመታት በፊት " ለውጥ መጥቷል " ከተባለና መንግሥት ኤርትራ አስመራ ላይ ከኦነግ ጋር ስምምነት ደርሷል ከተባለ በኃላ (ምንም እንኳን የስምምነት ሰነዱ ለህዝብ ይፋ ባይደረግም) ወደ ክልሉ በርካታ ታጣቂዎች ገብተዋል።
ከነዚህም ውስጥ ትጥቅ ሳይፈቱ የገቡ በርካቶች ነበሩ።
ወደ ሃገር ከገቡት ውስጥ " ከኦነግ ፓርቲ ጋር ተለያይተናል " ያሉ አባላት " መንግሥትን በትጥቅ ነው የምንታገለው " ብለው ወደ ጫካ ገብተዋል።
ይህን ተከትሎ በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች መካከል በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ በርካቶች አልቀዋል።
እገታ፣ ዘረፋ ተስፋፍቷል።
ተማሪዎች ትምህርት መማር አልቻሉም ፡ ገበሬዎች ማረስ አልቻሉም። ንፁሃን ዛሬም ድረስ ፍዳቸውን እያዩ ነው።
ሰላም ወጥቶ መግባትም የማይታሰብ የሆነባቸው በርካታ ቦታዎች ተፈጥረዋል።
በተለያዩ ቦታዎች ትጥቅ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ትንንሽ ቡድኖችንም እንዲበዙ ሆኗል።
በክልሉ ያለውን የትጥቅ እንቅስቃሴ ሆነ ሰላም የራቃቸውን ቦታዎች ወደ ሰላም ለመመለስ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና መንግሥት መካከል የጠረጴዛ ድርድር ሁለት ጊዜ ከሀገር ውጭ ቢደረግም ጠብ ያለ ተስፋ ያለው ውጤት ሳይመጣ ቀርቶ የትጥቅ እንቅስቃሴ በክልሉ ቀጥሏል።
አሁን ተደርጓል የተባለው የሰላም ስምምነት በጃል ሰኚ ከሚመራው ቡድን ጋር ቢሆንም ሌሎችም የሚመሯቸው ታጣቂዎች በክልሉ ይንቀሳቀሳሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ኦሮሚያ
@tikvahethiopia
🕊 " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም ! " - ነዋሪዎች
🟢 " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
⚪ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው፤... ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ ይሰጣል " - ጃል ሰኚ
⚫ " ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው " - ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ለድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት
ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የቀድሞው የማዕከላዊ ዞን አዛዥ ጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል።
የስምምነት ሰነዱ ምን እንደያዘ ፣ ምን ምን ጉዳዮች ላይ መግባባት ተደርሶ ስምምነት እንደተፈረመ ፣ በጃል ሰኚ ስር ምን ያህል ታጣቂ ወደ ሰላም እንደሚመለስ (በቁጥር) ፣ የነዚህ ታጣቂዎች ቀጣይ እጣ ፋንታ ምን እንደሆነ በይፋና በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።
ነገር ግን የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ይህ የሰላም ስምምነት ለዜጎች እረፍትን የሚሰጥ ሰላም የሚያሰርጽ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፤ " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " ብለዋል።
" የኦሮሞ ህዝብ በባህልና በወጉ መሰረት በሮቹን ጠምዶና ፈረሶችን ጭኖ በመውጣት ሰላም ይውረድ ባለው መሰረት ጥሪውን ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በራሴና በክልሉ መንግስት ስም አመሠግናለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህ ሂደት ትልቁን ስራ ለሰራው ሀገር መከላከያ ሠራዊት ምስጋና አቅርበዋል።
ጃል ሰኚ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የኦሮሞ ህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዓለም ላይ የሰው ልጅ የፖለቲካ ልዩነት አለው ፤ እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት ይልቅ በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው " ብለዋል።
ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ውጭ ሀገር ለሰላም ድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ባወጣው መግለጫ " ስምምነቱ ህዝቡን ለማምታታ የተፈጸመ ነው " ሲል ተችቷል።
ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው ብሏል።
ያም ሆነ ይህ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተነግሯል።
ለመሆኑ ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በርካታ ታጣቂዎች ወደተዘጋጀላቸው ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የታጣቂ አባላት የሰላም መንገድ መርጠው በተለይ በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እየተመለሱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ምዕራብ ሸዋ ጮቢ፣ ኢልፈታ፣ ዳኖ እና ጅባት ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ እና ዳው በሚባሉ ወረዳዎች የቡድኑ አባላት ቅብላ እየተደተገላቸው ነው።
ጃለታ አበበ ፤ " ትላንት እና ዛሬ ብቻ 7 መኪና ነው የተሃድሶ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ዞን ከተማ የገቡት። የሰላም ጥሪውን ከተቀበሉት ምንም የቀሩ አይመስለኝም ፤ ክላሽ መትረየስ እና ስናይፐር ይዘው ነው ያሉት " ብለዋል።
" ኢልፈታ፣ ግንደበረት ፣ ወዴሳና አምቦ አጠቃላይ ምእራብ ሸዋ ላይ ብዙ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባል የሰላም ጥሪ ተቀብሎ እየገባ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በዚህ ልክ የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የተመለሰ የታጣቂ ቡድን አባላትን አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጀልዱ ወረዳ በተመሳሳይ ቅበላ እየተደረገላቸው እንደነበር ተሰምቷል።
አቶ ግርማ ሌሎ የጀልዱ ወረዳ ኪልቤ ቀበሌ አስታዳዳሪ ፥ " በትክክልም በሁሉም አቅጣጫ እየተመለሱ ናቸው። ዛሬ እና ትላንት ጀልዱ ወረዳ ጉጁ ከተማ ሲደረሱ ሰው ሁሉ ወጥቶ ሲመለከታቸው ነበር " ብለዋል።
" መጀመሪያ ሲመጡ በየቀበሌያቸው በየቦታው ይሰበሰባሉ ከዛ ወደ መንግሥት ኃይሎች ስልክ ደውለው ነው የቅበላ ሰርዓት የሚደረገው። በጀልዱ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ነው እየተበልን ያለነው " ሲሉ አክለዋል።
ዊቱሺኩቴ፣ ኢልኬ ፣ጎሮ ቀበሌዎች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የመጡባቸው እንደሆኑ ጠቁመዋል።
አሁን ላይ በጃል ሰኚ የሚመሩት የሰላም አማራጭ ተከትለው እየተመለሱ ቢሆንም የሌሎች የቀሩትን እንደማያውቁ አቶ ግርማ ገልጸዋል።
" የህዝቡን ፍላጎት ተመልክተው ይመለሳሉ ብለን እናምናለን " ብለዋል።
ባለፈው ጥቅምት ወር በኪልቤ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና በመንግሥት የፀጥታ አካላት መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ የብዙ ሰው ህይወት አልፏል።
" አሁን ሰላም መውረዱ መሰል የሰው ህይወት ቀጥፈትን ይታደጋል " ሲሉ አቶ ግርማ ተናግረዋል።
እርስ በእርስ መተኳኮሱ ከቆመ በአካባቢው የተደናቀፈው ልማት ይቀጥላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ፤ የህዝቡ ፍላጎትን ስለሚያስጠብቅ ሰላም መውረዱ አስደሳች እንደሚሆን አክለዋል።
የጮቢ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ጃለታ በቀለ ፤ " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም። አሁን ህዝቡ ለ5 ዓመታት በቀጠለው ጦርነት ተጎድቷል መንግሥት እና ግብረሰናይ ድርጅቶች የህዝቡ ህይወት የሚንሰራራበትን መላ ይዘው ቢመጡ መልካም ነው " ብለዋል።
[ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዋሪዎች ቃል ምንጭ ቪኦኤ አፋን ኦሮሞ ሬድዮ እንደሆነ ይገልጻል ]
ኦሮሚያ ባለፉት አመታት ?
ከ6 ዓመታት በፊት " ለውጥ መጥቷል " ከተባለና መንግሥት ኤርትራ አስመራ ላይ ከኦነግ ጋር ስምምነት ደርሷል ከተባለ በኃላ (ምንም እንኳን የስምምነት ሰነዱ ለህዝብ ይፋ ባይደረግም) ወደ ክልሉ በርካታ ታጣቂዎች ገብተዋል።
ከነዚህም ውስጥ ትጥቅ ሳይፈቱ የገቡ በርካቶች ነበሩ።
ወደ ሃገር ከገቡት ውስጥ " ከኦነግ ፓርቲ ጋር ተለያይተናል " ያሉ አባላት " መንግሥትን በትጥቅ ነው የምንታገለው " ብለው ወደ ጫካ ገብተዋል።
ይህን ተከትሎ በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች መካከል በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ በርካቶች አልቀዋል።
እገታ፣ ዘረፋ ተስፋፍቷል።
ተማሪዎች ትምህርት መማር አልቻሉም ፡ ገበሬዎች ማረስ አልቻሉም። ንፁሃን ዛሬም ድረስ ፍዳቸውን እያዩ ነው።
ሰላም ወጥቶ መግባትም የማይታሰብ የሆነባቸው በርካታ ቦታዎች ተፈጥረዋል።
በተለያዩ ቦታዎች ትጥቅ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ትንንሽ ቡድኖችንም እንዲበዙ ሆኗል።
በክልሉ ያለውን የትጥቅ እንቅስቃሴ ሆነ ሰላም የራቃቸውን ቦታዎች ወደ ሰላም ለመመለስ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና መንግሥት መካከል የጠረጴዛ ድርድር ሁለት ጊዜ ከሀገር ውጭ ቢደረግም ጠብ ያለ ተስፋ ያለው ውጤት ሳይመጣ ቀርቶ የትጥቅ እንቅስቃሴ በክልሉ ቀጥሏል።
አሁን ተደርጓል የተባለው የሰላም ስምምነት በጃል ሰኚ ከሚመራው ቡድን ጋር ቢሆንም ሌሎችም የሚመሯቸው ታጣቂዎች በክልሉ ይንቀሳቀሳሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ኦሮሚያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩስያ ከዚህ ቀደም ማንኛውም አይነት #የግብረሰዶም እንቀስቃሴን #ሕገወጥ እና #ጽንፈኛ በማለት ፈርጃ የነበረችው ሩስያ አሁን ደግሞ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን #የአክራሪነት እና #የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥ አካታዋለች። በዚህም ማንኛውም ዓለም አቀፍ የግብረሰዶም እንቅስቃሴ በሩስያ በአሸባሪነት እና በአክራሪነት ዝርዝር ውስጥ ተካቷል። ውሳኔው የተደረሰው የሩስያ የፍትህ ሚኒስቴር የቀረበለትን አቤቱታ…
#Russia #Putin
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የሩስያ ፖሊስ ሞስኮ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባሮችን እና የምሽት መዝናኛ ክለቦችን ሲያስስ ነው ያደረው።
አሰሳው ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው።
በሩስያ ማንኛውም አይነት የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ማስተዋወቅ ወይም ፕሮፖጋንዳ መስራት በህገወጥነት መፈረጁ ይታወሳል።
ፖሊስ በቅዳሜ ምሽት አሰሳው በየባሩና በየምሽት ክለቡ እየገባ ጥብቅ ፍተሻ አድርጓል።
በወቅቱም ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ የቪድዮ ካሜራዎች ተወርሰዋል።
በየመሸታ ቤቶቹ የተገኙ ሰዎች ዶክመንታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ አድሯል።
የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ፤ የታገደውን የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ፖሮፖጋንዳ ሲያሰራጭ እንደነበር በተጠረጠረ አንድ በስም ባልገልጸው የምሽት ክለብ ውስጥም አሰሳና ፍተሻ መደረጉን ገልጿል።
ታስ እንደዘገበው ደግሞ " Men Travel " የተባለ የጉዞ ኤጀንሲ ኃላፊ ከፀረ ግብረሰዶማውያን ህግ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ሰውየው በሩስያ አዲስ አመት ወቅት ወደ ግብፅ " መደበኛ ያልሆኑ የወሲብ እሴቶችን " የሚደግፉ ደጋፊዎችን ጉዞ ሊያዘጋጅ እንደሆነ በመጠርጠሩ ነው።
የሩስያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴን " የፅንፈኞች እና አክራሪዎች እንቅስቃሴ " በማለት በህገወጥነት ፈርጆ ካገደ ሰሞኑን አንድ አመት ደፍኗል።
ሩስያ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥም ያካተተች ሲሆን የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት በሀገሪቱ እውቅና የለውም።
በሌላ በኩል ፥ ባለፈው ቅዳሜ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፤ ጄንደር አፊርሚንግ ኬር (የአንድን ሰው የጾታ ማንነት መደገፍ እና ማረጋገጥ) ወይም ጾታ መቀየር ህጋዊ የሆነባቸው ሀገራት ዜጎች የሩስያ ልጆችን በጉዲፈቻ እንዳይወስዱ የሚያግድ ህግ ላይ ፈርመዋል።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ፑቲን ሰዎች ልጅ እንዳይወልዱ የሚያበረታታ ማንኛውም አይነት እንቅስቃሴ / ስርጭትን የሚያግድ ህግ አፅድቀዋል።
#TikvahEthiopia
#Russia #TASS
@tikvahethiopia
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የሩስያ ፖሊስ ሞስኮ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባሮችን እና የምሽት መዝናኛ ክለቦችን ሲያስስ ነው ያደረው።
አሰሳው ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው።
በሩስያ ማንኛውም አይነት የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ማስተዋወቅ ወይም ፕሮፖጋንዳ መስራት በህገወጥነት መፈረጁ ይታወሳል።
ፖሊስ በቅዳሜ ምሽት አሰሳው በየባሩና በየምሽት ክለቡ እየገባ ጥብቅ ፍተሻ አድርጓል።
በወቅቱም ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ የቪድዮ ካሜራዎች ተወርሰዋል።
በየመሸታ ቤቶቹ የተገኙ ሰዎች ዶክመንታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ አድሯል።
የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ፤ የታገደውን የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ፖሮፖጋንዳ ሲያሰራጭ እንደነበር በተጠረጠረ አንድ በስም ባልገልጸው የምሽት ክለብ ውስጥም አሰሳና ፍተሻ መደረጉን ገልጿል።
ታስ እንደዘገበው ደግሞ " Men Travel " የተባለ የጉዞ ኤጀንሲ ኃላፊ ከፀረ ግብረሰዶማውያን ህግ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ሰውየው በሩስያ አዲስ አመት ወቅት ወደ ግብፅ " መደበኛ ያልሆኑ የወሲብ እሴቶችን " የሚደግፉ ደጋፊዎችን ጉዞ ሊያዘጋጅ እንደሆነ በመጠርጠሩ ነው።
የሩስያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴን " የፅንፈኞች እና አክራሪዎች እንቅስቃሴ " በማለት በህገወጥነት ፈርጆ ካገደ ሰሞኑን አንድ አመት ደፍኗል።
ሩስያ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥም ያካተተች ሲሆን የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት በሀገሪቱ እውቅና የለውም።
በሌላ በኩል ፥ ባለፈው ቅዳሜ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፤ ጄንደር አፊርሚንግ ኬር (የአንድን ሰው የጾታ ማንነት መደገፍ እና ማረጋገጥ) ወይም ጾታ መቀየር ህጋዊ የሆነባቸው ሀገራት ዜጎች የሩስያ ልጆችን በጉዲፈቻ እንዳይወስዱ የሚያግድ ህግ ላይ ፈርመዋል።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ፑቲን ሰዎች ልጅ እንዳይወልዱ የሚያበረታታ ማንኛውም አይነት እንቅስቃሴ / ስርጭትን የሚያግድ ህግ አፅድቀዋል።
#TikvahEthiopia
#Russia #TASS
@tikvahethiopia
#TecnoAI
ሀሳብዎን በቀላሉ መሬት ላይ ለማውረድ ሁነኛ አጋዥ ይፈልጋሉ? ምንም አይነት የስራ ዘርፍ ላይ ቢሰማሩ ቴክኖ ኤ አይ ካለ የተማረ አጋዥ አለ፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
ሀሳብዎን በቀላሉ መሬት ላይ ለማውረድ ሁነኛ አጋዥ ይፈልጋሉ? ምንም አይነት የስራ ዘርፍ ላይ ቢሰማሩ ቴክኖ ኤ አይ ካለ የተማረ አጋዥ አለ፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
TIKVAH-ETHIOPIA
" እናንተም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የወጣችሁት፣ አታንገላቱን ወዴት እንደሚሄድ ንገሩን ብንል ምላሽ አላገኘንም ! ” - ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር እና የኦሮሚያ ክልል ም/ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ ከፈቀደላቸው እና ዛሬ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ከወጡ በኃላ በር ላይ ተይዘው እስካሁን ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። አቶ ታዬ ደንደአ በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነው…
#Update
የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደዓ ዛሬ መኖርያ ቤታቸዉ ገቡ።
ከቤተሰቦቻቸው ጋርም ተቀላቅለዋል።
ትናንት አመሻሹን ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተለቀው ቤተሰቦቻቸውን ሳይቀላቀሉ ከማረሚያ ቤቱ በራፍ በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸው ይታወሳል።
በኃልም የተወሰዱት ሜክሲኮ የወንጀል ምርመራ እነደነበር ታውቋል።
ዛሬ እኩለ ቀን ደግሞ ሜክሲኮ ከሚገኘው የወንጅል ምርመራ ማዕከል ተለቀው ቤታቸው መድረሳቸውን ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ስንታየሁ " ጠዋት ቤተሰብ ሜክሲኮ ምግብ አድርሶላቸው ከተመለሰና ደህንነታው ከጠየቀ በኋላ ዛሬ እኩለ ቀን ምሳ ሰዓት ከማቆያው እንዲወጡ ተወስኖ 7 ሰዓት ግድም መኖራቸው ቤት ደርሰዋል " ብለዋል።
ባለፈው ሰኞ በፍርድ ቤት በ20 ሺህ ብር ዋስትና ክሳቸውን ከውጪ መከታተል እንዲችሉ በታዘዘው መሰረት ትናንት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ቢለቀቁም ለምን ወደ ሜክሲኮ የወንጀል ምርመራ ማዕከል እንደተወሰዱ ግን ቤተሰብ እንዳልተረዳ ነው የተነገረው፡፡
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደዓ ዛሬ መኖርያ ቤታቸዉ ገቡ።
ከቤተሰቦቻቸው ጋርም ተቀላቅለዋል።
ትናንት አመሻሹን ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተለቀው ቤተሰቦቻቸውን ሳይቀላቀሉ ከማረሚያ ቤቱ በራፍ በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸው ይታወሳል።
በኃልም የተወሰዱት ሜክሲኮ የወንጀል ምርመራ እነደነበር ታውቋል።
ዛሬ እኩለ ቀን ደግሞ ሜክሲኮ ከሚገኘው የወንጅል ምርመራ ማዕከል ተለቀው ቤታቸው መድረሳቸውን ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ስንታየሁ " ጠዋት ቤተሰብ ሜክሲኮ ምግብ አድርሶላቸው ከተመለሰና ደህንነታው ከጠየቀ በኋላ ዛሬ እኩለ ቀን ምሳ ሰዓት ከማቆያው እንዲወጡ ተወስኖ 7 ሰዓት ግድም መኖራቸው ቤት ደርሰዋል " ብለዋል።
ባለፈው ሰኞ በፍርድ ቤት በ20 ሺህ ብር ዋስትና ክሳቸውን ከውጪ መከታተል እንዲችሉ በታዘዘው መሰረት ትናንት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ቢለቀቁም ለምን ወደ ሜክሲኮ የወንጀል ምርመራ ማዕከል እንደተወሰዱ ግን ቤተሰብ እንዳልተረዳ ነው የተነገረው፡፡
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሪል_ስቴት_ልማት_እና_የማይንቀሳቀስ_ንብረት_ግብይትና_ግመታ_አዋጅ_1.pdf
የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ።
የህ/ተ/ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁ፤ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ሆኖ በሁለት ተቃውሞና በአንድ ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።
ዛሬ በምክር ቤት የፀደቀው ረቂቅ አዋጅ የሪል ስቴት አልሚ ድርጅት ያለደንበኛው ፍላጎትና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ እንደማይችል አስቀምጧል።
በተጨማሪ በሪል ስቴት ልማት ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል #የውሸት_ማስታወቂያ ማስነገር እንደማይችልም አስቀምጧል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ትላንት ያያዝነውን ሙሉ ሰነዱን በዚህ ያገኙታል👇
https://t.iss.one/tikvahethiopia/92613
@tikvahethiopia
የህ/ተ/ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁ፤ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ሆኖ በሁለት ተቃውሞና በአንድ ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።
ዛሬ በምክር ቤት የፀደቀው ረቂቅ አዋጅ የሪል ስቴት አልሚ ድርጅት ያለደንበኛው ፍላጎትና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ እንደማይችል አስቀምጧል።
በተጨማሪ በሪል ስቴት ልማት ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል #የውሸት_ማስታወቂያ ማስነገር እንደማይችልም አስቀምጧል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ትላንት ያያዝነውን ሙሉ ሰነዱን በዚህ ያገኙታል👇
https://t.iss.one/tikvahethiopia/92613
@tikvahethiopia
#DStvEthiopia
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ቀጥለዋል 💥
⚽️ Fulham vs Brighton ከምሽቱ 04:30 በSS Liyu በሜዳ ፓኬጅ
⚽️ Bournemouth vs Tottenham ከምሽቱ 05:15 በSS Premier League በሜዳ ፓኬጅ
👉እነዚህን ድንቅ ፍልሚያዎች ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ቀጥለዋል 💥
⚽️ Fulham vs Brighton ከምሽቱ 04:30 በSS Liyu በሜዳ ፓኬጅ
⚽️ Bournemouth vs Tottenham ከምሽቱ 05:15 በSS Premier League በሜዳ ፓኬጅ
👉እነዚህን ድንቅ ፍልሚያዎች ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
TIKVAH-ETHIOPIA
" በምክር ቤት የተሾሙትን አመራር በግርግር ነው ከፅህፈት ቤቱ ያወጣው " - በድብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ትላንት ምሽት መግለጫ አውጥቷል። ደርጅቱ በመግለጫው ለአቶ ጌታቸው ረዳ ሰጥቷቸው የነበረው የፕሬዜዳንት ውክልና አንስቶ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት እንዴት እና በማን እንዲሚተኩ ከፌደራል መንግስት እየተወያየበት እንደሚገኝ…
#Tigray
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ ክልል የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በውይይቱ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዛዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር።
ከነሱ በተጨማሪ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናትም ነበሩ።
ምንም እንኳን የውይይቱ ዝርዝር ይፋ ባይደረግም በክልሉ የሚታዩ ችግሮችን እንዴት በጋራ መፍታት እንደሚገባ ውይይት መደረጉ ተገልጿል።
በውይይቱ በተለዩ አንኳር ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ የጋራ አቅጣጫዎች መሠረት በጋራ ለመስራትና የክልሉ ህዝብ የፀጥታ፣ የመልካም አስተዳደር እና የልማት ፍላጎት ለማሟላት አስቻይ ሁኔታ ለመፍጠር መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።
በተለይ ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቀያቸው የሚመለሱበትን ሁኔታና ታጣቂዎችን ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ሂደት በትኩረት የሚሰራበት እና የሚሳለጥበት ሁኔታ ላይ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።
በተጨማሪ በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሃብቶች አጠቃቀም ህጋዊ በሆነ አግባብ የህዝብንና የሀገርን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሆን፣ ለህዝብ የሚቀርቡ የመንግስት አገልግሎቶች የሚሻሻሉበትና የህዝብን ፍላጎት የሚመጥኑ እንዲሆኑ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ስራ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በዚሁ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት ላይ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ክልላዊ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ያለበትን ሃላፊነት ለመወጣት በሚያስችለው አግባብ ላይም አቅጣጫ ተቀምጧል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው መከፋፈል ወደየት እያመራ ነው ? በሚል ብዙዎችን ማስጋቱ ይታወቃል።
በተለይ ሰሞኑን በአቶ ጌታቸው እና በደብረጾን (ዶ/ር) ቡድኖች መካከል ጠንከር ያሉ የመግለጫና የሚዲያ ምልልሶች ሲደረጉ ሰንብተዋል።
ከመግለጫና የሚዲያ ምልልስ ባለፈ በደብረፅዮ ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በምክር ቤት አማካኝነት የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሹመኞች በማንሳት የራሱን ሲሾም በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር በበኩሉ በደብረጽዮን በሚመራው ቡድን የሚሾሙ ሹመኞችን በማንሳት የራሱን አመራሮች ሲመድብ ነበር።
@tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ ክልል የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በውይይቱ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዛዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር።
ከነሱ በተጨማሪ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናትም ነበሩ።
ምንም እንኳን የውይይቱ ዝርዝር ይፋ ባይደረግም በክልሉ የሚታዩ ችግሮችን እንዴት በጋራ መፍታት እንደሚገባ ውይይት መደረጉ ተገልጿል።
በውይይቱ በተለዩ አንኳር ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ የጋራ አቅጣጫዎች መሠረት በጋራ ለመስራትና የክልሉ ህዝብ የፀጥታ፣ የመልካም አስተዳደር እና የልማት ፍላጎት ለማሟላት አስቻይ ሁኔታ ለመፍጠር መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።
በተለይ ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቀያቸው የሚመለሱበትን ሁኔታና ታጣቂዎችን ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ሂደት በትኩረት የሚሰራበት እና የሚሳለጥበት ሁኔታ ላይ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።
በተጨማሪ በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሃብቶች አጠቃቀም ህጋዊ በሆነ አግባብ የህዝብንና የሀገርን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሆን፣ ለህዝብ የሚቀርቡ የመንግስት አገልግሎቶች የሚሻሻሉበትና የህዝብን ፍላጎት የሚመጥኑ እንዲሆኑ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ስራ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በዚሁ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት ላይ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ክልላዊ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ያለበትን ሃላፊነት ለመወጣት በሚያስችለው አግባብ ላይም አቅጣጫ ተቀምጧል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው መከፋፈል ወደየት እያመራ ነው ? በሚል ብዙዎችን ማስጋቱ ይታወቃል።
በተለይ ሰሞኑን በአቶ ጌታቸው እና በደብረጾን (ዶ/ር) ቡድኖች መካከል ጠንከር ያሉ የመግለጫና የሚዲያ ምልልሶች ሲደረጉ ሰንብተዋል።
ከመግለጫና የሚዲያ ምልልስ ባለፈ በደብረፅዮ ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በምክር ቤት አማካኝነት የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሹመኞች በማንሳት የራሱን ሲሾም በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር በበኩሉ በደብረጽዮን በሚመራው ቡድን የሚሾሙ ሹመኞችን በማንሳት የራሱን አመራሮች ሲመድብ ነበር።
@tikvahethiopia