TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ጊዜያዊ አስታዳደሩ የወሰደው እርምጃ ህዝቡን ወደአላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ ነው " - የመቐለ ከተማ ምክር ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ
የመቐለ ከተማ ም/ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከህዳር 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰጠው የመቐለ ከንቲባ ሹመት ከመቃወም አልፎ " ህገ-መንግስት የጣሰ ተግባር " ብሎታል።
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ህዳር 24/ 2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር በምክር ቤት አብላጫ ድምፅ የተሾሙ ከንቲባ በስራ ላይ እያሉ የምክር ቤት እና የህዝብ ሉአላውነት በመጣስ ፓሊስ ስራቸው እንዳይሰሩ አግዷል ብሏል።
" በዚያው ቀን ከሰዓት በኋላ ህጋዊ ያልሆኑ ከንቲባ በአስተዳደሩ አንድ አዳራሽ መግለጫ እንዲሰጡ ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።
" በምክር ቤት በስርዓት የተሾሙ ከንቲባ ወደ ቢሯቸው እንዳይገቡ የመቐለ ፓሊስ ከህግ አገባብ ውጪ ፅህፈት ቤታቸው በማሸግ ህዝብ አገልግሎት እንዳይገኝ አስተጓጉለዋል " ሲል ከሷል።
" የፓሊስ ኢ-ህጋዊ ተግባር አገልግሎት ያጣ ህዝብ ወዳልተፈለገ ሽብርና ቀውስ እንዲገባ አድርገዋል " ብሏል።
በተጨማሪ የቋም ኮሚቴው በመግለጫ ምን አለ ?
👉 " በህገ-መንግስት የተሰጠ ስልጣን በመቀማት አምባገነን ስርዓት ለመትከል የተፈፀመ ተግባር ነው ይህንን እንኮንናለን። የተፈፀመው አግባብነት የጎደለው ተግባር በአስቸኳይ እንዲታረም ጥሪ እናቀርባለን። "
👉 " የመቐለ ፓሊስ አመራር በህገ-መንግስት የተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው የፈፀመው ህገ-ወጥ ተግባር በማስተካከል በምክር ቤት የተሾሙ ከንቲባ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ሳይውል ሳያድር ስራቸው እንዲሰሩ እና አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲያደርግ እንጠይቃለን "
👉 " የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመው የህግ ጥሰት በመገንዘብ ህግ እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን "
👉 " የመቐለ ከተማ ህዝብ ህገ-ወጥ ተግባሩ በመቃወም ከምክር ቤቱ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን "
👉 " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የምክር ቤቶች ሉአላዊ ስልጣን በመጣስ የወሰደው እርምጃ ህዝቡ ወደ አላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ መሆኑ በመገንዘብ በዚሁ በህገ-መንግስት ጥሰት የተሳተፉት አካላት በህግ እንዲጠይቃቸው ጥሪ እናቀርባለን "
... ብሏል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሸሙት አዲሱ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ መደበኛ ህዝባዊ አገልግሎት መስጠት አንደሚጀምሩ ታማኝ ምንጮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ ሰጥተውታል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ጊዜያዊ አስታዳደሩ የወሰደው እርምጃ ህዝቡን ወደአላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ ነው " - የመቐለ ከተማ ምክር ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ
የመቐለ ከተማ ም/ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከህዳር 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰጠው የመቐለ ከንቲባ ሹመት ከመቃወም አልፎ " ህገ-መንግስት የጣሰ ተግባር " ብሎታል።
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ህዳር 24/ 2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር በምክር ቤት አብላጫ ድምፅ የተሾሙ ከንቲባ በስራ ላይ እያሉ የምክር ቤት እና የህዝብ ሉአላውነት በመጣስ ፓሊስ ስራቸው እንዳይሰሩ አግዷል ብሏል።
" በዚያው ቀን ከሰዓት በኋላ ህጋዊ ያልሆኑ ከንቲባ በአስተዳደሩ አንድ አዳራሽ መግለጫ እንዲሰጡ ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።
" በምክር ቤት በስርዓት የተሾሙ ከንቲባ ወደ ቢሯቸው እንዳይገቡ የመቐለ ፓሊስ ከህግ አገባብ ውጪ ፅህፈት ቤታቸው በማሸግ ህዝብ አገልግሎት እንዳይገኝ አስተጓጉለዋል " ሲል ከሷል።
" የፓሊስ ኢ-ህጋዊ ተግባር አገልግሎት ያጣ ህዝብ ወዳልተፈለገ ሽብርና ቀውስ እንዲገባ አድርገዋል " ብሏል።
በተጨማሪ የቋም ኮሚቴው በመግለጫ ምን አለ ?
👉 " በህገ-መንግስት የተሰጠ ስልጣን በመቀማት አምባገነን ስርዓት ለመትከል የተፈፀመ ተግባር ነው ይህንን እንኮንናለን። የተፈፀመው አግባብነት የጎደለው ተግባር በአስቸኳይ እንዲታረም ጥሪ እናቀርባለን። "
👉 " የመቐለ ፓሊስ አመራር በህገ-መንግስት የተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው የፈፀመው ህገ-ወጥ ተግባር በማስተካከል በምክር ቤት የተሾሙ ከንቲባ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ሳይውል ሳያድር ስራቸው እንዲሰሩ እና አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲያደርግ እንጠይቃለን "
👉 " የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመው የህግ ጥሰት በመገንዘብ ህግ እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን "
👉 " የመቐለ ከተማ ህዝብ ህገ-ወጥ ተግባሩ በመቃወም ከምክር ቤቱ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን "
👉 " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የምክር ቤቶች ሉአላዊ ስልጣን በመጣስ የወሰደው እርምጃ ህዝቡ ወደ አላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ መሆኑ በመገንዘብ በዚሁ በህገ-መንግስት ጥሰት የተሳተፉት አካላት በህግ እንዲጠይቃቸው ጥሪ እናቀርባለን "
... ብሏል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሸሙት አዲሱ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ መደበኛ ህዝባዊ አገልግሎት መስጠት አንደሚጀምሩ ታማኝ ምንጮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ ሰጥተውታል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ልመና አልነበረም ማለት አይደለም ፤ አሁን ግን እየተባባሰ ሄዷል ! ... የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው " - አቶ አበረ አዳሙ
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።
በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?
" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።
ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።
የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።
ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።
ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።
ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።
በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።
ጥቅሙን የሚያገኘው በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።
በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።
ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?
2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)
ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።
👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤
👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤
👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።
የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።
በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።
ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።
ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?
3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።
የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።
ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።
ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "
ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።
በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?
" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።
ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።
የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።
ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።
ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።
ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።
በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።
ጥቅሙን የሚያገኘው በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።
በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።
ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?
2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)
ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።
👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤
👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤
👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።
የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።
በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።
ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።
ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?
3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።
የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።
ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።
ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "
ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#TecnoAI
የስራዎች መደራረብ ህይወቶን ፕሮግራም አልባ አድርጎታል? በላቁ ቴክኖሎጂዎች የተዋቀረው አዲሱ ቴክኖ ኤ አይ ፕሮፌሽናል አጋዥ በመሆን ህይወቶን ለማቅለል እየመጣ ነው፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ በሆነው የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
የስራዎች መደራረብ ህይወቶን ፕሮግራም አልባ አድርጎታል? በላቁ ቴክኖሎጂዎች የተዋቀረው አዲሱ ቴክኖ ኤ አይ ፕሮፌሽናል አጋዥ በመሆን ህይወቶን ለማቅለል እየመጣ ነው፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ በሆነው የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ጊዜያዊ አስታዳደሩ የወሰደው እርምጃ ህዝቡን ወደአላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ ነው " - የመቐለ ከተማ ምክር ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የመቐለ ከተማ ም/ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከህዳር 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰጠው የመቐለ ከንቲባ ሹመት ከመቃወም አልፎ " ህገ-መንግስት የጣሰ ተግባር " ብሎታል። የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ህዳር 24/ 2017…
" በምክር ቤት የተሾሙትን አመራር በግርግር ነው ከፅህፈት ቤቱ ያወጣው " - በድብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት
በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ትላንት ምሽት መግለጫ አውጥቷል።
ደርጅቱ በመግለጫው ለአቶ ጌታቸው ረዳ ሰጥቷቸው የነበረው የፕሬዜዳንት ውክልና አንስቶ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት እንዴት እና በማን እንዲሚተኩ ከፌደራል መንግስት እየተወያየበት እንደሚገኝ አስታውሷል።
' ቡድን ' ሲል የገለፀው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን የጊዚያዊ አስተዳደር በመምራት ላይ የሚገኘውን ህወሓት " የህዝብ ውክልና የያዙ ምክር ቤቶች እውቅና በመንሳት እና ውሳኔዎቻቸው በመጣስ በማን አለበኝነት ምስለኔዎች በመሾም አስተዳደራዊ እና ህዝባዊ ስራዎች እያደናቀፍ ይገኛል " ሲል ከሷል።
የአቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን ህገ-መንግስት ላይ የተቀመጠውን የህዝብ እና የመንግስት ከፍተኛ መገለጫ የሆነው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በመጣስ በህዝብ ላይ አምባገነንነት ለመጫን በሙሉ አቅሙ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ብሏል።
" ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ምክር ቤት የተሾሙትን አመራር በግርግር ከፅህፈት ቤቱ በማውጣት በራሱ ምስሌኔ የአስተዳደሩ ፅህፈት ቤት ለመቆጣጠር መክሮዋል " ሲል አክሏል።
" ህገ-ወጥ ሙከራው ከግለሰባዊ አምባገነንነት የሚነሳ ነው " ያለው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ፤ አባላቱ ትግላቸው አጠናክረው እንዲቀጥሉ በማስታውስ ፣ የፀጥታ እና የፍትህ አካላት ህጋዊ ተጠያቂነት ፣ ህግ እና ስርዓት እንዲያስከብሩ በማለት ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ትላንት ምሽት መግለጫ አውጥቷል።
ደርጅቱ በመግለጫው ለአቶ ጌታቸው ረዳ ሰጥቷቸው የነበረው የፕሬዜዳንት ውክልና አንስቶ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት እንዴት እና በማን እንዲሚተኩ ከፌደራል መንግስት እየተወያየበት እንደሚገኝ አስታውሷል።
' ቡድን ' ሲል የገለፀው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን የጊዚያዊ አስተዳደር በመምራት ላይ የሚገኘውን ህወሓት " የህዝብ ውክልና የያዙ ምክር ቤቶች እውቅና በመንሳት እና ውሳኔዎቻቸው በመጣስ በማን አለበኝነት ምስለኔዎች በመሾም አስተዳደራዊ እና ህዝባዊ ስራዎች እያደናቀፍ ይገኛል " ሲል ከሷል።
የአቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን ህገ-መንግስት ላይ የተቀመጠውን የህዝብ እና የመንግስት ከፍተኛ መገለጫ የሆነው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በመጣስ በህዝብ ላይ አምባገነንነት ለመጫን በሙሉ አቅሙ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ብሏል።
" ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ምክር ቤት የተሾሙትን አመራር በግርግር ከፅህፈት ቤቱ በማውጣት በራሱ ምስሌኔ የአስተዳደሩ ፅህፈት ቤት ለመቆጣጠር መክሮዋል " ሲል አክሏል።
" ህገ-ወጥ ሙከራው ከግለሰባዊ አምባገነንነት የሚነሳ ነው " ያለው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ፤ አባላቱ ትግላቸው አጠናክረው እንዲቀጥሉ በማስታውስ ፣ የፀጥታ እና የፍትህ አካላት ህጋዊ ተጠያቂነት ፣ ህግ እና ስርዓት እንዲያስከብሩ በማለት ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " - ማርክ ጉዬ
➡️ የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ወደ ሜዳ ገብቶ ጨዋታውን አድርጓል !
ማርክ ጉዬ የተባለው እግር ኳስ ተጫዋች በድጋሚ ክንድ ላይ በሚጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " የሚል ፅሁፍ በመፃፍ ወደ ሜዳ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ክሪስታል ፓላስ ለተባለው ክለብ የሚጫወተውና የቡድኑ አምበል የሆነው ጉዬ ከቀናት በፊት ኒውካስል ዩናይትድ ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስን እወደዋለሁ " ብሎ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳዳሪዎች አስቆጥቶ ነበር።
ይኸው ተጫዋች ትላንት ምሽት ቡድኑ ኢፒስዊች ታውን ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባለው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ብሎ በመፃፍ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ባለፈው ቅዳሜ ከፃፈው " ኢየሱስን እወደዋለሁ ! " ከሚለው ፅሁፍ በኃላ ፉትቦል አሶሲዬሽን የተባለው የሊጉ አስተዳዳሪ " ኃይማኖታዊ ምልክቶች የእግር ኳስ ማሊያ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ላይ መፃፍ ክልክል ነው " ሲል ለክለቡ እና ለአምበሉ ማስጠንቀቂያ ቢልክም ማስጠንቀቂያው ወዲያ በሉት ብሎ ትላንት ምሽት በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ሲል በመፃፍ ገብቶ ተጫውቷል።
የሊጉ አስተዳዳሪ ቅጣት ሊጥልበት ይችላል እየተባለ ነው።
በሌላ በኩል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ሳም ሞርሲ የተባለው የኢፒስዊች ታውን ተጫዋች ትላንትም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ያለበትን የአምበልነት መለያ ሳያደርግ ነው የገባው።
ተጫዋቹ " ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ባለፈው ቅዳሜም ይህንን የግብረሰዶሞች ምልክት ሳያደርግ መግባቱ የሚዘነጋ አይደለም።
' እኩልነት እና ብዝሃነት ' በሚል ሰብሰብ በዓለም ላይ የግብረሰዶማውያንን እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅ እና ሰዎች ጋር ለማድረስ የግብረሰዶማውያን ደጋፊዎች ብዙ አይነት መንገድ ይከተላሉ።
አንዱ ግብረሰዶማውያንን ለማስተዋወቅ የሚጠቀሙት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ በተለይም ወጣት ተመልካቾች ያሉትን የእግር ኳስ ፍልሚያ ነው።
ከነዚህ የእግር ኳስ ፍልሚያዎች አንዱ ደግሞ በኢትዮጵያ / አፍሪካ ሆነ በዓለም ላይ ብዙ ተመልካች ያለውን እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው።
በዚሁ ሊግ የሊጉ አስተዳዳሪ አካላት በ ' እኩልነት እና ብዝሃነት ' ሰበብ የክለብ አምበሎች ክንዳቸው ላይ የግብረሰዶማውያንን ምልክት እንዲያጠልቁ አድርገው ለግብረሰዶማውያን ማስታወቂያ እንዲሰሩ ያደርጋሉ።
ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ የሊጉ ፍልሚያ በሚጋጋልበት ወቅት ነው።
ግብረሰዶማውያን እና የነሱ ደጋፊዎች እጅግ በጣም ተወዳጁን የእግር ኳስ ፍልሚያን ተጠቅመው ግብረሰዶምን የሚያስተዋውቁት በልጆች ፣ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች ዘንድ ድርጊቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግና እነሱን ለማነሳሳት ነው።
#TikvahEthiopia
#Guehi #Christian #PremierLeague
#SamMorsy #Muslim
@tikvahethiopia
➡️ የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ወደ ሜዳ ገብቶ ጨዋታውን አድርጓል !
ማርክ ጉዬ የተባለው እግር ኳስ ተጫዋች በድጋሚ ክንድ ላይ በሚጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " የሚል ፅሁፍ በመፃፍ ወደ ሜዳ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ክሪስታል ፓላስ ለተባለው ክለብ የሚጫወተውና የቡድኑ አምበል የሆነው ጉዬ ከቀናት በፊት ኒውካስል ዩናይትድ ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስን እወደዋለሁ " ብሎ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳዳሪዎች አስቆጥቶ ነበር።
ይኸው ተጫዋች ትላንት ምሽት ቡድኑ ኢፒስዊች ታውን ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባለው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ብሎ በመፃፍ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ባለፈው ቅዳሜ ከፃፈው " ኢየሱስን እወደዋለሁ ! " ከሚለው ፅሁፍ በኃላ ፉትቦል አሶሲዬሽን የተባለው የሊጉ አስተዳዳሪ " ኃይማኖታዊ ምልክቶች የእግር ኳስ ማሊያ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ላይ መፃፍ ክልክል ነው " ሲል ለክለቡ እና ለአምበሉ ማስጠንቀቂያ ቢልክም ማስጠንቀቂያው ወዲያ በሉት ብሎ ትላንት ምሽት በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ሲል በመፃፍ ገብቶ ተጫውቷል።
የሊጉ አስተዳዳሪ ቅጣት ሊጥልበት ይችላል እየተባለ ነው።
በሌላ በኩል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ሳም ሞርሲ የተባለው የኢፒስዊች ታውን ተጫዋች ትላንትም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ያለበትን የአምበልነት መለያ ሳያደርግ ነው የገባው።
ተጫዋቹ " ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ባለፈው ቅዳሜም ይህንን የግብረሰዶሞች ምልክት ሳያደርግ መግባቱ የሚዘነጋ አይደለም።
' እኩልነት እና ብዝሃነት ' በሚል ሰብሰብ በዓለም ላይ የግብረሰዶማውያንን እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅ እና ሰዎች ጋር ለማድረስ የግብረሰዶማውያን ደጋፊዎች ብዙ አይነት መንገድ ይከተላሉ።
አንዱ ግብረሰዶማውያንን ለማስተዋወቅ የሚጠቀሙት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ በተለይም ወጣት ተመልካቾች ያሉትን የእግር ኳስ ፍልሚያ ነው።
ከነዚህ የእግር ኳስ ፍልሚያዎች አንዱ ደግሞ በኢትዮጵያ / አፍሪካ ሆነ በዓለም ላይ ብዙ ተመልካች ያለውን እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው።
በዚሁ ሊግ የሊጉ አስተዳዳሪ አካላት በ ' እኩልነት እና ብዝሃነት ' ሰበብ የክለብ አምበሎች ክንዳቸው ላይ የግብረሰዶማውያንን ምልክት እንዲያጠልቁ አድርገው ለግብረሰዶማውያን ማስታወቂያ እንዲሰሩ ያደርጋሉ።
ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ የሊጉ ፍልሚያ በሚጋጋልበት ወቅት ነው።
ግብረሰዶማውያን እና የነሱ ደጋፊዎች እጅግ በጣም ተወዳጁን የእግር ኳስ ፍልሚያን ተጠቅመው ግብረሰዶምን የሚያስተዋውቁት በልጆች ፣ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች ዘንድ ድርጊቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግና እነሱን ለማነሳሳት ነው።
#TikvahEthiopia
#Guehi #Christian #PremierLeague
#SamMorsy #Muslim
@tikvahethiopia
#MPESASafaricom
🎁 ስድስት ወር ሙሉ ዳታ እንደልብ! በየትኘውም ሰአት ያልተገደበ ፍጥነት እና ደስታ! ለረጅም ጊዜ የሚቆዩትን ሜጋ የኢንተርኔት ጥቅሎች በM-PESA በመግዛት እስከ 1,000 ብር የሚደርስ ቅናሽ አግኝተን ፏ እንበል! 🌐🤳 ከሳፋሪኮም አስተማማኝ ኔትወርክ ጋር ወደፊት!⚡
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
🎁 ስድስት ወር ሙሉ ዳታ እንደልብ! በየትኘውም ሰአት ያልተገደበ ፍጥነት እና ደስታ! ለረጅም ጊዜ የሚቆዩትን ሜጋ የኢንተርኔት ጥቅሎች በM-PESA በመግዛት እስከ 1,000 ብር የሚደርስ ቅናሽ አግኝተን ፏ እንበል! 🌐🤳 ከሳፋሪኮም አስተማማኝ ኔትወርክ ጋር ወደፊት!⚡
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#Namibia
በናሚቢያ ምርጫ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት አሸንፈዋል፡፡
የገዢው ስዋፖ ፓርቲ (SWAPO) እጩ የሆኑት ኔቱምቦ ናንዲ-ንዳይትዋህ ከ57 በመቶ በላይ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን አሳውቋል፡፡
ተቀናቃኛቸው ፓንዱሌኒ ኢቱላ ደግሞ 26 በመቶ ድምጽ አጊኝተዋል፡፡
የሎጂስቲክ ችግር እና በተወሰኑ አካባቢዎች የነበረን እስከ ሦስት ቀናት የዘለቀ የድምጽ አሰጣጥ መዘግየትን ተከትሎ የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት ተቃዋሚው ኢቱላ አሳውቀዋል፡፡
በዚህም በመዲናዋ ዊንድሆክ ትናንት ማምሻውን ውጤቱ ይፋ ሲደረግ በርካታ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች አልተገኙም ነበር፡፡
የውጤቱን ይፋ መሆን ተከትሎ " የናሚቢያ ህዝብ ሰላም እና መረጋጋትን መርጧል " ሲሉ ተመረጯ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል፡፡
SWAPO ፓርቲ አገሪቱ ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣችበት እንደ አውሮፓውያኑ 1990 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል፡፡
ተመረጯ ፕሬዝዳንት በቅርቡ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑ ሲሆን በተለያዩ የመንግስት ኃላፊነተች ላለፉት 25 ዓመታት አገልግለዋል፡፡
ተመረጯ ፕሬዝዳንት ከታንዛኒያዋ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሀሰን በመቀጠል በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሴት ፕሬዝዳንት ይሆናሉ፡፡
@tikvahethiopia
በናሚቢያ ምርጫ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት አሸንፈዋል፡፡
የገዢው ስዋፖ ፓርቲ (SWAPO) እጩ የሆኑት ኔቱምቦ ናንዲ-ንዳይትዋህ ከ57 በመቶ በላይ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን አሳውቋል፡፡
ተቀናቃኛቸው ፓንዱሌኒ ኢቱላ ደግሞ 26 በመቶ ድምጽ አጊኝተዋል፡፡
የሎጂስቲክ ችግር እና በተወሰኑ አካባቢዎች የነበረን እስከ ሦስት ቀናት የዘለቀ የድምጽ አሰጣጥ መዘግየትን ተከትሎ የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት ተቃዋሚው ኢቱላ አሳውቀዋል፡፡
በዚህም በመዲናዋ ዊንድሆክ ትናንት ማምሻውን ውጤቱ ይፋ ሲደረግ በርካታ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች አልተገኙም ነበር፡፡
የውጤቱን ይፋ መሆን ተከትሎ " የናሚቢያ ህዝብ ሰላም እና መረጋጋትን መርጧል " ሲሉ ተመረጯ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል፡፡
SWAPO ፓርቲ አገሪቱ ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣችበት እንደ አውሮፓውያኑ 1990 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል፡፡
ተመረጯ ፕሬዝዳንት በቅርቡ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑ ሲሆን በተለያዩ የመንግስት ኃላፊነተች ላለፉት 25 ዓመታት አገልግለዋል፡፡
ተመረጯ ፕሬዝዳንት ከታንዛኒያዋ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሀሰን በመቀጠል በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሴት ፕሬዝዳንት ይሆናሉ፡፡
@tikvahethiopia
“ ችግራችን ብዙ ነው። ዘርፈ ብዙ የሆነ ምላሽ ያስፈልገናል ” - ማኀበሩ
የአካል ጉዳተኞችን ዘርፈ ብዙ ችግሮች መንግስትን ጭምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሁሉ ትኩረት እንዲሰጡ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ አካል ጉዳተኞች ማኀበር በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል በአጽንኦት አሳሰበ።
የማኀበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ጥላሁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ብዙ ጉዳዮች ላይ ሕጎች የሉም። እንደሚባለው አይደለም። በቂና ተፈጻሚ ሕጎች አሉ ማለት አይቻልም” ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ በዝርዝር ምን አሉ?
“ለምሳሌ ዓይነ ስውራንን በተመለከተ በተለይ ገጠር አካባቢ ያሉት ህፃናት ብሬል/የሚፅፉበት ማተሪያል ያስፈልጋቸዋል።
የኮሚፒዩተር አቅርቦት እንኳ ቢኖር ለመጠቀም የሚያስችል ስክሪን/ማንበቢያ ሶፍትዌር ያስፈፍጋል። ያ የለም።
በዘርፉ የሰለጠኑ ብሬል ማስተማር የሚችሉ መምህራን የሉም ለዓይነ ስውራን። መስማት የተሳናቸው ወገኖች ውስጥ የምልክት ቋንቋ የሚችል የለም ማለት ይቻላል።
በከፊል መስማት የተሳናቸው የመስሚያ መርጃ መሳሪያ ቢያገኙ ከማህበረሰቡ ጋር መቀላቀልና መማር ይችላሉ። በተለይ በገጠር አካባቢ ያሉ ያሉ አካል ጉዳተኞች በባትሪ የሚሰሩ ጠንካራ ዌልቸሮችን ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል።
ችግራችን ብዙ ነው። ዘርፈ ብዙ የሆነ ምላሽ ይፈልጋል። አመለካከትን፣ ተጠያቂነትን ከማስፈን አኳያ ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች አሉ።
➡️ የትምህርት መብት፣
➡️ የመስራት መብት፣
➡️ የተደራሽነት መብት፣
➡️ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት፣
➡️ የመኖሪያ ቤት መብት፣
➡️ ከቀረጥ ነጻ የአካል ጉዳተኞች መገልገያ እቃዎች አገር ወደ ውስጥ እንዲገቡ ከማድረግ የሚያስችል ሁኔታ፣
➡️ የአካል ጉዳተኞችን ሁኔታ በበላይነት የሚመራ ራሱን የቻለ ተቋም ከማቋቋም አኳያ፣
➡️ ሕጉን የሚጥሱ አካላት ላይ ተጠያቂ ማድረግን የሚያስችሉ ሁሉን አቀፍ አሰራሮች ያስፈፍጋሉ።
አንድ ጊዜ ሕግ ማውጣት ብቻም በቂ ላይሆን ይቻላል። ለምሳሌ የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት ዐዋጅ የሚባል አለ። ከወጣ 17 ዓመታት ሆነው።
ነገር ግን በቂ በቂ መመሪያ እንኳ በየጊዜው እየተሻሻለለት አይደለም። ለማሻሻልም ምንም አይነት እንቅስቃሴ ተደርጎ አያውቅም” ሲሉ ተናግረዋል።
ከ20 ሚሊዮን በላይ የአካል ጉዳተኞች ከ90 በመቶ በላይ ህፃናት የትምህርት እድል እንደሌላቸው፣ 95 በመቶ ከድኀነት ወለል በታች እንደሚኖሩ፣ 98 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላቸው ወይም ተቀጥረው የማይሰሩ መሆናቸው ተነግሯል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአካል ጉዳተኞችን ዘርፈ ብዙ ችግሮች መንግስትን ጭምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሁሉ ትኩረት እንዲሰጡ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ አካል ጉዳተኞች ማኀበር በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል በአጽንኦት አሳሰበ።
የማኀበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ጥላሁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ብዙ ጉዳዮች ላይ ሕጎች የሉም። እንደሚባለው አይደለም። በቂና ተፈጻሚ ሕጎች አሉ ማለት አይቻልም” ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ በዝርዝር ምን አሉ?
“ለምሳሌ ዓይነ ስውራንን በተመለከተ በተለይ ገጠር አካባቢ ያሉት ህፃናት ብሬል/የሚፅፉበት ማተሪያል ያስፈልጋቸዋል።
የኮሚፒዩተር አቅርቦት እንኳ ቢኖር ለመጠቀም የሚያስችል ስክሪን/ማንበቢያ ሶፍትዌር ያስፈፍጋል። ያ የለም።
በዘርፉ የሰለጠኑ ብሬል ማስተማር የሚችሉ መምህራን የሉም ለዓይነ ስውራን። መስማት የተሳናቸው ወገኖች ውስጥ የምልክት ቋንቋ የሚችል የለም ማለት ይቻላል።
በከፊል መስማት የተሳናቸው የመስሚያ መርጃ መሳሪያ ቢያገኙ ከማህበረሰቡ ጋር መቀላቀልና መማር ይችላሉ። በተለይ በገጠር አካባቢ ያሉ ያሉ አካል ጉዳተኞች በባትሪ የሚሰሩ ጠንካራ ዌልቸሮችን ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል።
ችግራችን ብዙ ነው። ዘርፈ ብዙ የሆነ ምላሽ ይፈልጋል። አመለካከትን፣ ተጠያቂነትን ከማስፈን አኳያ ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች አሉ።
➡️ የትምህርት መብት፣
➡️ የመስራት መብት፣
➡️ የተደራሽነት መብት፣
➡️ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት፣
➡️ የመኖሪያ ቤት መብት፣
➡️ ከቀረጥ ነጻ የአካል ጉዳተኞች መገልገያ እቃዎች አገር ወደ ውስጥ እንዲገቡ ከማድረግ የሚያስችል ሁኔታ፣
➡️ የአካል ጉዳተኞችን ሁኔታ በበላይነት የሚመራ ራሱን የቻለ ተቋም ከማቋቋም አኳያ፣
➡️ ሕጉን የሚጥሱ አካላት ላይ ተጠያቂ ማድረግን የሚያስችሉ ሁሉን አቀፍ አሰራሮች ያስፈፍጋሉ።
አንድ ጊዜ ሕግ ማውጣት ብቻም በቂ ላይሆን ይቻላል። ለምሳሌ የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት ዐዋጅ የሚባል አለ። ከወጣ 17 ዓመታት ሆነው።
ነገር ግን በቂ በቂ መመሪያ እንኳ በየጊዜው እየተሻሻለለት አይደለም። ለማሻሻልም ምንም አይነት እንቅስቃሴ ተደርጎ አያውቅም” ሲሉ ተናግረዋል።
ከ20 ሚሊዮን በላይ የአካል ጉዳተኞች ከ90 በመቶ በላይ ህፃናት የትምህርት እድል እንደሌላቸው፣ 95 በመቶ ከድኀነት ወለል በታች እንደሚኖሩ፣ 98 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላቸው ወይም ተቀጥረው የማይሰሩ መሆናቸው ተነግሯል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#EthiopianInvestmentHoldings
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕን ጨምሮ 8 ተቋማት ከአሁን በኃላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንደሚተዳደሩ ተነገር።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 8 ተጨማሪ የመንግስት ድርጅቶችን በስሩ በማካተት ፖርትፎሊዮውን ማስፋቱን በላከልን መግለጫ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) በስሩ ከሚገኘትና ከሚያስተዳድራቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች በተጨማሪ 8 አዳዲስ ቁልፍ ተቋማትን በስሩ በማካተት የድርጅቶቹን ቁጥር ጨምሯል።
8ቱ ተቋማት እነማን ናቸው ?
- ኢትዮ ፖስት፣
- ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፐ
- የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት፣
- የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣
- የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣
- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣
- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን እና ለኢትዮ ፋርማ ግሩT ተጠሪ የሆኑት ብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥቢታ ተቋምና ሺልድ ቫክስ ናቸው።
እነዚህ ቀደም ሲል ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ተጠሪ የነበሩት የልማት ድርጅቶች ከአሁን ጀምሮ በባለቤትነት የሚተዳደሩትና የሚመሩት በኢኢሆ ስር ሆኗል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕን ጨምሮ 8 ተቋማት ከአሁን በኃላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንደሚተዳደሩ ተነገር።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 8 ተጨማሪ የመንግስት ድርጅቶችን በስሩ በማካተት ፖርትፎሊዮውን ማስፋቱን በላከልን መግለጫ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) በስሩ ከሚገኘትና ከሚያስተዳድራቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች በተጨማሪ 8 አዳዲስ ቁልፍ ተቋማትን በስሩ በማካተት የድርጅቶቹን ቁጥር ጨምሯል።
8ቱ ተቋማት እነማን ናቸው ?
- ኢትዮ ፖስት፣
- ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፐ
- የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት፣
- የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣
- የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣
- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣
- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን እና ለኢትዮ ፋርማ ግሩT ተጠሪ የሆኑት ብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥቢታ ተቋምና ሺልድ ቫክስ ናቸው።
እነዚህ ቀደም ሲል ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ተጠሪ የነበሩት የልማት ድርጅቶች ከአሁን ጀምሮ በባለቤትነት የሚተዳደሩትና የሚመሩት በኢኢሆ ስር ሆኗል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
" እናንተም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የወጣችሁት፣ አታንገላቱን ወዴት እንደሚሄድ ንገሩን ብንል ምላሽ አላገኘንም ! ” - ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ
የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር እና የኦሮሚያ ክልል ም/ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ ከፈቀደላቸው እና ዛሬ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ከወጡ በኃላ በር ላይ ተይዘው እስካሁን ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል።
አቶ ታዬ ደንደአ በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነው የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ባለፈው ሰኞ በዋለው ችሎት ነው።
ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ምን አሉ ?
" ከሰዓት በኋላ ወደ 11 ሰዓት ገደማ ላይ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤቱ በር ላይ ነው የተወሰደው ፤ እስካሁን ድረስ ወደየት እንደተወሰዱ ማወቅ አልቻልንም።
ሰኞ በዋለው ችሎት ይግባኝ ብሎ ስለነበር በ20 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ እና ጉዳዩን ከውጭ ሆኖ እንዲከታተል ተወስኖለት ነበር።
ለአንድ ዓመት ተለያይተን ስለነበር ጓጉተን ስንጠብቀው ነበር።
ከማረሚያ ቤቱ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ሲቪል የለበሱ እና ማስክ ያደረጉ ሁለት የደኅንነት አባላት እንዲሁም ሌሎች የታጠቁ ሰዎችም ነበሩ። የፌደራል ፖሊስ ዩኒፎርም የለበሱም ነበሩ።
ተለቆ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ሊወጣ ሲል ውጭ ላይ የነበሩት ያዙት።
ከጠዋት 5 ሰዓት አንስቶ በዋስ ይወጣል ብለን ስንጠብቅ ነበር።
እኔን ጨምሮ የተቀረው ቤተሰብ ማረሚያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ነበርን።
ሲቪል የለበሱና ማስክ ያደረጉት ሁለት የደኅንነት አባላት ሲገቡ እና ሲወጡ፣ በስልክ በተደጋጋሚ ሲነጋገሩም እያየን ነበር።
ከእኛ ቀድመው ነው በፍጥነት ሄደው ደርሰው ነው የያዙት። ሲይዙት ግብግብ ነበር።
ለዚህ እንደተዘጋጁ የሚያሳዩ ብዙ እንቅስቃሴዎች ስለታዘብኩ፣ በሕግ አምላክ ይሄ ሰው ሊያመልጥ አይደለም፤ በዋስ ወጥቶ ጉዳዩን ከውጭ ሆኖ ሊከታተል ነው። እናንተም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የወጣችሁት፣ አታንገላቱን ወዴት እንደሚሄድ ንገሩን ብንል ምላሽ አላገኘንም።
በፓትሮል መኪና ነው የወሰዱት።
አሁን የት እንዳለ አላውቅም።
እዚ ነው ያለው መጥታችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ ያለንም አካል የለም።
በወቅቱ አንዱን ስጠይቅ ‘ ወዴት እንደምንወስደው አናውቅም፤ ይዛችሁት ኑ ነው የተባልነው ’ አሉኝ።
‘ለሌላ የሕግ ጉዳይ ይፈለጋሉ’ የሚል አንድ ቃል ብቻ ከፖሊስ ሰምቻለሁ። ጠመንጃ የያዙት ሁለቱ ግን ግብግብ ነው የጀመሩት።
እሱ (ታዬም) በወቅቱ ' ምንድን ነው የሆነው ነገር? ወዴት ነው የምሄደው? ' ብሎ ሲጠይቅ ሰምቻለሁ። ምላሽ ግን አልተሰጠውም።
የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ አክብሮ ለመልቀቅ ቢወስንም የያዙት አካላት ከውስጥ መረጃ እየተከታተሉ ነበር።
የተሰጠው ወረቅት እንኳን ምን እንደሚል በውል ሳያነብ እና ሳይረዳ በቅርብ የነበረው ፓትሮል ውስጥ እየተገፈተረ ሄዷል።
የሕግ አካል እጅ ከሆነ ያለው ሊደወለልን ይችላል ብለን እናስባለን። ካልሆነ ደግሞ አድረን እንፈልጋለን " ብለዋል።
የአቶ ታዬ ደንደአ የፍርድ ሂደት ምን ይመስላል ?
° አቶ ታዬ ባለፈው ዓመት ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
° ዐቃቤ ሕግ 3 ተደራራቢ ክሶችን ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2016 ዓ. ም. መስርቷል።
° ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት፣ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እንዲሁም የጦር መሣሪያ ሕጉን በመተላለፍ ወንጀሎች ተከሰዋል።
° የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ከዚህ ቀደም ከሦስቱ ክሶች መካከል በሁለቱ፣ ሁከት እና ብጥብት በማነሳሳት እና የፀረ- ሰላም ኃይሎችን ድጋፍ ማድረግ ክሶች በነጻ አሰናብቷቸዋል።
° የጦር መሣሪያ ወንጀሎችን በተመለከተ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል።
° የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቶ ታዬ ደንደአ 20 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ በማስያዝ ወይም በዋስ እንዲፈቱ / ጉዳያቸውን ከውጭ እንዲከታተሉ ብያኔ አሳልፏል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር እና የኦሮሚያ ክልል ም/ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ ከፈቀደላቸው እና ዛሬ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ከወጡ በኃላ በር ላይ ተይዘው እስካሁን ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል።
አቶ ታዬ ደንደአ በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነው የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ባለፈው ሰኞ በዋለው ችሎት ነው።
ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ምን አሉ ?
" ከሰዓት በኋላ ወደ 11 ሰዓት ገደማ ላይ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤቱ በር ላይ ነው የተወሰደው ፤ እስካሁን ድረስ ወደየት እንደተወሰዱ ማወቅ አልቻልንም።
ሰኞ በዋለው ችሎት ይግባኝ ብሎ ስለነበር በ20 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ እና ጉዳዩን ከውጭ ሆኖ እንዲከታተል ተወስኖለት ነበር።
ለአንድ ዓመት ተለያይተን ስለነበር ጓጉተን ስንጠብቀው ነበር።
ከማረሚያ ቤቱ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ሲቪል የለበሱ እና ማስክ ያደረጉ ሁለት የደኅንነት አባላት እንዲሁም ሌሎች የታጠቁ ሰዎችም ነበሩ። የፌደራል ፖሊስ ዩኒፎርም የለበሱም ነበሩ።
ተለቆ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ሊወጣ ሲል ውጭ ላይ የነበሩት ያዙት።
ከጠዋት 5 ሰዓት አንስቶ በዋስ ይወጣል ብለን ስንጠብቅ ነበር።
እኔን ጨምሮ የተቀረው ቤተሰብ ማረሚያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ነበርን።
ሲቪል የለበሱና ማስክ ያደረጉት ሁለት የደኅንነት አባላት ሲገቡ እና ሲወጡ፣ በስልክ በተደጋጋሚ ሲነጋገሩም እያየን ነበር።
ከእኛ ቀድመው ነው በፍጥነት ሄደው ደርሰው ነው የያዙት። ሲይዙት ግብግብ ነበር።
ለዚህ እንደተዘጋጁ የሚያሳዩ ብዙ እንቅስቃሴዎች ስለታዘብኩ፣ በሕግ አምላክ ይሄ ሰው ሊያመልጥ አይደለም፤ በዋስ ወጥቶ ጉዳዩን ከውጭ ሆኖ ሊከታተል ነው። እናንተም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የወጣችሁት፣ አታንገላቱን ወዴት እንደሚሄድ ንገሩን ብንል ምላሽ አላገኘንም።
በፓትሮል መኪና ነው የወሰዱት።
አሁን የት እንዳለ አላውቅም።
እዚ ነው ያለው መጥታችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ ያለንም አካል የለም።
በወቅቱ አንዱን ስጠይቅ ‘ ወዴት እንደምንወስደው አናውቅም፤ ይዛችሁት ኑ ነው የተባልነው ’ አሉኝ።
‘ለሌላ የሕግ ጉዳይ ይፈለጋሉ’ የሚል አንድ ቃል ብቻ ከፖሊስ ሰምቻለሁ። ጠመንጃ የያዙት ሁለቱ ግን ግብግብ ነው የጀመሩት።
እሱ (ታዬም) በወቅቱ ' ምንድን ነው የሆነው ነገር? ወዴት ነው የምሄደው? ' ብሎ ሲጠይቅ ሰምቻለሁ። ምላሽ ግን አልተሰጠውም።
የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ አክብሮ ለመልቀቅ ቢወስንም የያዙት አካላት ከውስጥ መረጃ እየተከታተሉ ነበር።
የተሰጠው ወረቅት እንኳን ምን እንደሚል በውል ሳያነብ እና ሳይረዳ በቅርብ የነበረው ፓትሮል ውስጥ እየተገፈተረ ሄዷል።
የሕግ አካል እጅ ከሆነ ያለው ሊደወለልን ይችላል ብለን እናስባለን። ካልሆነ ደግሞ አድረን እንፈልጋለን " ብለዋል።
የአቶ ታዬ ደንደአ የፍርድ ሂደት ምን ይመስላል ?
° አቶ ታዬ ባለፈው ዓመት ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
° ዐቃቤ ሕግ 3 ተደራራቢ ክሶችን ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2016 ዓ. ም. መስርቷል።
° ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት፣ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እንዲሁም የጦር መሣሪያ ሕጉን በመተላለፍ ወንጀሎች ተከሰዋል።
° የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ከዚህ ቀደም ከሦስቱ ክሶች መካከል በሁለቱ፣ ሁከት እና ብጥብት በማነሳሳት እና የፀረ- ሰላም ኃይሎችን ድጋፍ ማድረግ ክሶች በነጻ አሰናብቷቸዋል።
° የጦር መሣሪያ ወንጀሎችን በተመለከተ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል።
° የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቶ ታዬ ደንደአ 20 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ በማስያዝ ወይም በዋስ እንዲፈቱ / ጉዳያቸውን ከውጭ እንዲከታተሉ ብያኔ አሳልፏል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
#ኡሙሩ
🔴 " ሹፌሩን ጨምሮ 6 ሰዎች ተገድለዋል " - ነዋሪዎች
🔵 " መኪናውን መተው ከጣሉት በኃላ 5 ሰዎች ሞተዋል " - የአጋምሳ ከንቲባ
በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ ከአጋምሳ ከተማ ወደ ጫቦ ሲሄድ በነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ ላይ በተከፈተ ጥቃት 6 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከትላንት በስቲያ ጥዋት የተፈጸመ ሲሆን ነዋሪዎቹ " ሰዎችን እና በጎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ተሽከርካሪ ላይ አባይ ሸለቆ አካባቢ ነው ጥቃት የተከፈከተው " ብለዋል።
አንድ ነዋሪ ፤ የሞቱት ሰዎች ከአጋምሳ እና ጫቦ እንደሆኑ በዚሁ ቦታ ላይ ሁለት ጊዜ ተመሳሳይ ጥቃት እንደተፈጸመ ፤ ከዚህ በፊት አንድ ሲኖ ላይ ጥቃት ተፈጽሞ ሰዎች መጎዳታቸውን ተናግረዋል።
ቃላቸውም የሰጡ ነዋሪዎች ሹፌርን ጨምሮ የሞቱት 6 ናቸው ብለዋል።
የአጋምሳ ከንቲባ ጌታሁን ደሳለኝ የጥቃቱን መፈጸም አረጋግጠው የተገደሉት ሰዎች 5 ናቸው ብለዋል።
" መኪናውን መተው ከጣሉ በኃላ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ቆስለዋል " ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
🔴 " ሹፌሩን ጨምሮ 6 ሰዎች ተገድለዋል " - ነዋሪዎች
🔵 " መኪናውን መተው ከጣሉት በኃላ 5 ሰዎች ሞተዋል " - የአጋምሳ ከንቲባ
በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ ከአጋምሳ ከተማ ወደ ጫቦ ሲሄድ በነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ ላይ በተከፈተ ጥቃት 6 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከትላንት በስቲያ ጥዋት የተፈጸመ ሲሆን ነዋሪዎቹ " ሰዎችን እና በጎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ተሽከርካሪ ላይ አባይ ሸለቆ አካባቢ ነው ጥቃት የተከፈከተው " ብለዋል።
አንድ ነዋሪ ፤ የሞቱት ሰዎች ከአጋምሳ እና ጫቦ እንደሆኑ በዚሁ ቦታ ላይ ሁለት ጊዜ ተመሳሳይ ጥቃት እንደተፈጸመ ፤ ከዚህ በፊት አንድ ሲኖ ላይ ጥቃት ተፈጽሞ ሰዎች መጎዳታቸውን ተናግረዋል።
ቃላቸውም የሰጡ ነዋሪዎች ሹፌርን ጨምሮ የሞቱት 6 ናቸው ብለዋል።
የአጋምሳ ከንቲባ ጌታሁን ደሳለኝ የጥቃቱን መፈጸም አረጋግጠው የተገደሉት ሰዎች 5 ናቸው ብለዋል።
" መኪናውን መተው ከጣሉ በኃላ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ቆስለዋል " ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የሪል_ስቴት_ልማት_እና_የማይንቀሳቀስ_ንብረት_ግብይትና_ግመታ_አዋጅ_1.pdf
1.7 MB
የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?
👉 የሪል ስቴት አልሚ የቦታና የተናጠል ይዞታ ማረጋገጫ አሰጣጥን በተመለከተ ፦
1) በከተሞች ለሪል ስቴት ልማት የሚውል ቦታ በሚከተለው አግባብ የሚቀርብ ይሆናል፤
ሀ. በአዲስ አበባ ከ5 ሺህ በላይ ቤት የሚገነባና የሚያስተላልፍ ወይም፤
ለ. እንደከተሞች ተጨባጭ የቤት ፍላጎትና ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባለ ከተሞች ከ1 ሺህ በላይ ቤት የሚገነባና የሚያስተላልፍ ወይም፣
ሐ. ከነዚህ ባነሰ ስፋት ቤት ለሚፈልጉ ከተሞች ደግሞ 500 ቤት በላይ የሚገነባና የሚያስተላልፍ የሪል ስቴት አልሚ መሬት ቅድሚያ ተሰጥቶት በስፋት እንዲቀርብለት ይደረጋል።
2) የሪል ስቴት አልሚው የገነባውን ቤት በተናጠል ለቤት ፈላጊ በሽያጭ ለማስተላለፍ ግንባታው የተፈቀደለትን መስፈርት አሟልቶ 80 በመቶ ሲጠናቀቅ ለየቤቱ የተናጠል የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ እንዲሰጠው ሊጠይቅ ይችላል፤
👉 የሪል ስቴት አልሚ ግዴታዎች ምንድናቸው ?
የሪልስቴት አልሚ በውል ሰነዱ በህንጻ እዋጁ እና በሌሎች የህግ ማዕቀፎች የተመላከቱ ግዴታዎችን ማክበር እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨማሪነት የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል ፡-
1) ያለደንበኛው ፍላጎትና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ #አይችልም፡፡
2) በሪል ስቴት ልማት ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል #የውሸት_ማስታወቂያ ማስነገር አይችልም፡፡
3) ቤቶቹን ለመገንባት የሚያስችለውን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከመረከቡ በፊት ደንበኞችን መመዝገብና ቅድመ ክፍያዎችን መሰብሰብ አይችልም፡፡
4) በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም።
5) የመኖሪያ ቤት ገዢ ደንበኞች ማኀበር እንዲያቋቋም ያበረታታል ፤ የህንጻ መግለጫ ያስረክባል።
6) ከሚመለከተው የመንግሥት አካል የተሰጠውን የይዞታ ማረጋገጫ፣ የቤቱ የግንባታ ዕቃዎች ዓይነት፣ አርክቴክቸራል፤ ሳኒተሪ ፣ ስትራክቸራል እና ኤሌክትሪካል ዲዛይን፤ የግንባታ ፍቃድና የሪል ስቴት ልማት ፍቃዱን ቅጂዎች ከውል ሰነዱ ጋር አያይዞ ለደንበኛው መስጠት አለበት።
7) ደንበኛው ለከፈለው ገንዘብ ሕጋዊ ደረሰኝ መስጠት አለበት።
👉 ዋስትና ስለመስጠት ፦
የአገር ውስጥ አልሚ ቤቱን ሳይገነባ ለቤት ፈላጊዎች በቅድሚያ በሚሽጥበት ወቅት የሚከተሉትን የዋስትና ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላት አለበት፡፡
1) የሪል ስቴት አልሚው በቤት ቅድሚያ ሽያጭ ስልት ለመስራት መፈለጉን አግባብ ላለው አካለ አሳውቆ ፈቃድ ማግኘት፡፡
2) ከቤት ገዥዎች የሚሰበስበውን ገንዘብ አግባብ ካለው አካለ ፈቃድ መሰረት በሚከፈተው የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ፣
3) የሪል ስቴት አልሚው በቅድሚያ መሽጥ የሚፈልገውን ቤት የመስሪያ ቦታ የይዞታ ማስረጃ ቤቱ ለተጠቃሚዎች ተገንብቶ እስከሚተላለፍ ድረስ በሚመለከተው አካል እንዳይሽጥ እንዳይለወጥ እንዲታገድ ማድረግ፤
⚫ በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ በደንብ ይወሰናል፡፡
(ሙሉ ረቂቁን ከላይ አያይዘናል ያንብቡ)
@tikvahethiopia
👉 የሪል ስቴት አልሚ የቦታና የተናጠል ይዞታ ማረጋገጫ አሰጣጥን በተመለከተ ፦
1) በከተሞች ለሪል ስቴት ልማት የሚውል ቦታ በሚከተለው አግባብ የሚቀርብ ይሆናል፤
ሀ. በአዲስ አበባ ከ5 ሺህ በላይ ቤት የሚገነባና የሚያስተላልፍ ወይም፤
ለ. እንደከተሞች ተጨባጭ የቤት ፍላጎትና ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባለ ከተሞች ከ1 ሺህ በላይ ቤት የሚገነባና የሚያስተላልፍ ወይም፣
ሐ. ከነዚህ ባነሰ ስፋት ቤት ለሚፈልጉ ከተሞች ደግሞ 500 ቤት በላይ የሚገነባና የሚያስተላልፍ የሪል ስቴት አልሚ መሬት ቅድሚያ ተሰጥቶት በስፋት እንዲቀርብለት ይደረጋል።
2) የሪል ስቴት አልሚው የገነባውን ቤት በተናጠል ለቤት ፈላጊ በሽያጭ ለማስተላለፍ ግንባታው የተፈቀደለትን መስፈርት አሟልቶ 80 በመቶ ሲጠናቀቅ ለየቤቱ የተናጠል የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ እንዲሰጠው ሊጠይቅ ይችላል፤
👉 የሪል ስቴት አልሚ ግዴታዎች ምንድናቸው ?
የሪልስቴት አልሚ በውል ሰነዱ በህንጻ እዋጁ እና በሌሎች የህግ ማዕቀፎች የተመላከቱ ግዴታዎችን ማክበር እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨማሪነት የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል ፡-
1) ያለደንበኛው ፍላጎትና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ #አይችልም፡፡
2) በሪል ስቴት ልማት ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አካል #የውሸት_ማስታወቂያ ማስነገር አይችልም፡፡
3) ቤቶቹን ለመገንባት የሚያስችለውን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከመረከቡ በፊት ደንበኞችን መመዝገብና ቅድመ ክፍያዎችን መሰብሰብ አይችልም፡፡
4) በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም።
5) የመኖሪያ ቤት ገዢ ደንበኞች ማኀበር እንዲያቋቋም ያበረታታል ፤ የህንጻ መግለጫ ያስረክባል።
6) ከሚመለከተው የመንግሥት አካል የተሰጠውን የይዞታ ማረጋገጫ፣ የቤቱ የግንባታ ዕቃዎች ዓይነት፣ አርክቴክቸራል፤ ሳኒተሪ ፣ ስትራክቸራል እና ኤሌክትሪካል ዲዛይን፤ የግንባታ ፍቃድና የሪል ስቴት ልማት ፍቃዱን ቅጂዎች ከውል ሰነዱ ጋር አያይዞ ለደንበኛው መስጠት አለበት።
7) ደንበኛው ለከፈለው ገንዘብ ሕጋዊ ደረሰኝ መስጠት አለበት።
👉 ዋስትና ስለመስጠት ፦
የአገር ውስጥ አልሚ ቤቱን ሳይገነባ ለቤት ፈላጊዎች በቅድሚያ በሚሽጥበት ወቅት የሚከተሉትን የዋስትና ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላት አለበት፡፡
1) የሪል ስቴት አልሚው በቤት ቅድሚያ ሽያጭ ስልት ለመስራት መፈለጉን አግባብ ላለው አካለ አሳውቆ ፈቃድ ማግኘት፡፡
2) ከቤት ገዥዎች የሚሰበስበውን ገንዘብ አግባብ ካለው አካለ ፈቃድ መሰረት በሚከፈተው የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ፣
3) የሪል ስቴት አልሚው በቅድሚያ መሽጥ የሚፈልገውን ቤት የመስሪያ ቦታ የይዞታ ማስረጃ ቤቱ ለተጠቃሚዎች ተገንብቶ እስከሚተላለፍ ድረስ በሚመለከተው አካል እንዳይሽጥ እንዳይለወጥ እንዲታገድ ማድረግ፤
⚫ በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ በደንብ ይወሰናል፡፡
(ሙሉ ረቂቁን ከላይ አያይዘናል ያንብቡ)
@tikvahethiopia