#ደመወዝ
➡️ " አሁን ላይ ከኑሮ ወድነቱ ጋር ተደምሮ የደመወዝ መዘግየት እየፈተነን ይገኛል " - ሰራተኞች
➡️ " ችግሩ ይቆያል የሚል እምነት የለኝም " - የድርጅቱ አመራር
ደቡብ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በበጀት ምክኒያት መፈተን ከጀመረ እንደቆየ የድርጅቱ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
በዚህም ምክኒያት " ደሞዝ እየዘገዪ ተቸግረናል " የሚሉት ሰራተኞቹ " በ28 ሲገባ የነበረዉ ደሞዛችን እስከ አስራአምስትና አስራ ስድስት ቀናት መዘግየት ጀምሯል " ብለዋል።
የስልክ እና አንዳንድ ወጭዎች ከተቋረጡ መቆየታቸውን ያነሱ ሲሆን አሁን ላይ ከኑሮ ወድነቱ ጋር ተደምሮ የደሞዙ መዘግየት እየፈተናቸዉ መሆኑን አስረድተዋል።
ድርጅቱ ከአራቱ ክልሎች ማለትም ፦
* ከሲዳማ
* ከደቡብ ኢትዮጵያ
* ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ
* ከመአከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚበጀት ገንዘብ እንደሚንቀሳቀስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹት አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አመራር " አሁን ላይ ይህ በጀት በአግባቡ ባለመለቀቁ ምክኒያት የደሞዝም ሆነ የውስጥ ስራ ማስኬጃ እጥረቶች ሊከሰቱ ችለዋል " ብለዋል።
" ችግሩ ይቆያል የሚል እምነት የለኝም " ሲሉም ተናግረዋል።
አመራሩ አክለው ፤ " ደሬቴድ ይፈርሳል፤ ይሰነጣጠቃል " የሚሉ ወሬዎች እንደነበሩና አሁን ላይ በአራቱ ክልል በጀት እየተንቀሳቀሰ ማህበረሰቡን በማገልገል እንዲቀጥል አቅጣጫ በመቀመጡ የህልዉና ችግር እንደሌለበትና በጀትም የመለቀቁ ጉዳይ ብዙ የሚያደክም አይደለም ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
መረጃዉ አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
➡️ " አሁን ላይ ከኑሮ ወድነቱ ጋር ተደምሮ የደመወዝ መዘግየት እየፈተነን ይገኛል " - ሰራተኞች
➡️ " ችግሩ ይቆያል የሚል እምነት የለኝም " - የድርጅቱ አመራር
ደቡብ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በበጀት ምክኒያት መፈተን ከጀመረ እንደቆየ የድርጅቱ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
በዚህም ምክኒያት " ደሞዝ እየዘገዪ ተቸግረናል " የሚሉት ሰራተኞቹ " በ28 ሲገባ የነበረዉ ደሞዛችን እስከ አስራአምስትና አስራ ስድስት ቀናት መዘግየት ጀምሯል " ብለዋል።
የስልክ እና አንዳንድ ወጭዎች ከተቋረጡ መቆየታቸውን ያነሱ ሲሆን አሁን ላይ ከኑሮ ወድነቱ ጋር ተደምሮ የደሞዙ መዘግየት እየፈተናቸዉ መሆኑን አስረድተዋል።
ድርጅቱ ከአራቱ ክልሎች ማለትም ፦
* ከሲዳማ
* ከደቡብ ኢትዮጵያ
* ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ
* ከመአከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚበጀት ገንዘብ እንደሚንቀሳቀስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹት አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አመራር " አሁን ላይ ይህ በጀት በአግባቡ ባለመለቀቁ ምክኒያት የደሞዝም ሆነ የውስጥ ስራ ማስኬጃ እጥረቶች ሊከሰቱ ችለዋል " ብለዋል።
" ችግሩ ይቆያል የሚል እምነት የለኝም " ሲሉም ተናግረዋል።
አመራሩ አክለው ፤ " ደሬቴድ ይፈርሳል፤ ይሰነጣጠቃል " የሚሉ ወሬዎች እንደነበሩና አሁን ላይ በአራቱ ክልል በጀት እየተንቀሳቀሰ ማህበረሰቡን በማገልገል እንዲቀጥል አቅጣጫ በመቀመጡ የህልዉና ችግር እንደሌለበትና በጀትም የመለቀቁ ጉዳይ ብዙ የሚያደክም አይደለም ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
መረጃዉ አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
" ላለፉት ወራት በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ስንፈተን ቆይተናል " ያሉ የዎላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች " ስራችንን በአግባቡ ለመስራት እንችል ዘንድ መንግሥት በአግባቡ ደሞዝ ሊከፍለን ይገባል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸው ከሰጡት የመንግስት ሰራተኞች ውስጥ በተለይም #መምህራን እና #የህክምና_ባለሙያዎች ይገኙበታል።
" ጉዳዩን በተዋረድ ለሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ለወረዳ አመራሮች ካሳወቅን ቆየን " የሚሉት እነዚህ ሰራተኞች " ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ/ም ወደ ክልሉ መንግስት መቀመጫ ወደሆነችዉ ወላይታ ሶዶ ከተማ ብናቀናም ሰሚ አላገኘንም " ብለዋል።
በተለይ ይህ የደሞዝ አለመክፈል እና መቆራረጥ ችግር የተከሰተባቸው በዎላይታ ዞን ስር የሚገኙት የኪንዶ ኮይሻ ፣ የሆብቻ ፣ አባላ ፣ አባያ፣ ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ፑላሳ ፣ ዳሞት ወይዴ ፣ ኪንዶ ዲዳዬ እና አካባቢዉ ወረዳና ቀበሊያት እንደሆኑ ተገልጿል።
በሆብቻ ወረዳ የሚገኘው የሆብቻ ወረዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስራ ካቆመ መሰነባበቱንና ተማሪዎች ቤታቸዉ እየዋሉ መሆኑን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ መምህራን " መንግስት በአፋጣኝ እርምጃ ወስዶ ወደስራችን ይመልሰን " ብለዋል።
ከዚህዉ ጋር ተያይዞ የከልሉን መንግስት ሀሳብ በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወይዘሮ አዜብ ስለጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ዝርዝር ሀሳብ ከመሰንዘር ተቆጥበዋል።
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን እናሳውቃችኃለን።
መረጃዉን አዘጋጅቶ የላከዉ የሀዋሳው ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" ላለፉት ወራት በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ስንፈተን ቆይተናል " ያሉ የዎላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች " ስራችንን በአግባቡ ለመስራት እንችል ዘንድ መንግሥት በአግባቡ ደሞዝ ሊከፍለን ይገባል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸው ከሰጡት የመንግስት ሰራተኞች ውስጥ በተለይም #መምህራን እና #የህክምና_ባለሙያዎች ይገኙበታል።
" ጉዳዩን በተዋረድ ለሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ለወረዳ አመራሮች ካሳወቅን ቆየን " የሚሉት እነዚህ ሰራተኞች " ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ/ም ወደ ክልሉ መንግስት መቀመጫ ወደሆነችዉ ወላይታ ሶዶ ከተማ ብናቀናም ሰሚ አላገኘንም " ብለዋል።
በተለይ ይህ የደሞዝ አለመክፈል እና መቆራረጥ ችግር የተከሰተባቸው በዎላይታ ዞን ስር የሚገኙት የኪንዶ ኮይሻ ፣ የሆብቻ ፣ አባላ ፣ አባያ፣ ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ፑላሳ ፣ ዳሞት ወይዴ ፣ ኪንዶ ዲዳዬ እና አካባቢዉ ወረዳና ቀበሊያት እንደሆኑ ተገልጿል።
በሆብቻ ወረዳ የሚገኘው የሆብቻ ወረዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስራ ካቆመ መሰነባበቱንና ተማሪዎች ቤታቸዉ እየዋሉ መሆኑን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ መምህራን " መንግስት በአፋጣኝ እርምጃ ወስዶ ወደስራችን ይመልሰን " ብለዋል።
ከዚህዉ ጋር ተያይዞ የከልሉን መንግስት ሀሳብ በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወይዘሮ አዜብ ስለጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ዝርዝር ሀሳብ ከመሰንዘር ተቆጥበዋል።
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን እናሳውቃችኃለን።
መረጃዉን አዘጋጅቶ የላከዉ የሀዋሳው ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
#ደመወዝ #የትርፍሰዓትክፍያ
➡ “ ከ9 ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈለንም ”- ከ200 በላይ የጤና ባለሙያዎች
➡ “ የትርፍ ሰዓት በየወሩ እየተከፈለ አይደለም እሱ ትክክል ነው። የከተማ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል ገብቷል ” - የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ ጋሞ ዞን ፤ በሰላምበር ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎች ከ9 ወራት በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ጊዜ ሰዓት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ፣ ደመወዝም የሚገባላቸው እየተቆራረጠ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የጤና ባለሙያዎችን ወክለው ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ አንድ የጤና ባለሙያ ተከታዩን ብለዋል።
- “ ከ9 ወራት በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈለንም። ሳይከፈለን 10ኛ ወር እየሰራን ነው ያለነው። ”
- “ በሌላ በኩል ደግሞ ዋና ደመወዝ ሁሌም እየተቆራረጠ ነው የሚገባው። ግማሹ ብቻ ያስገቡና ግማሹ ደግሞ ሳይገባ ወሩ ያልቃል። ”
- “ የደመወዝ ሆነ የትርፍ ሰዓት ክፍያ በተመለከተ ቅሬታ ያለን 113 ጤና ባለሙያዎች (የትርፍ ሰዓት ያልተከፈላቸው) ፣ 103 ድጋፍ ሰጭ ባለሙያዎች (የትርፍ ሰዓት ክፍያ የማይመለከታቸው) ናቸው። ”
- “ ያልተከፈለው የክፍያ መጠን እንደ ጤና ባለሙያው ፤ አሁን ለምሳሌ የእኔ 5,000 ነው በወር የሚሆነው። 15 ሺሕ የሚከፈለው አለ። 30 ሺሕ የሚከፈለው አለ እንደ ስፔሻሊቲ ከሆነ። ”
በጉዳዩ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* የሰላምበር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የCOA ተወካይ አቶ ደካሶ ዲቻ፣
* የሰላምበር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘነበ ወንተ
* የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንደሻው ሽብሩን አግኝቶ ምላሽ እንዲሰጡ ቢሞክርም ፈቃደኛ አልሆኑም።
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ግን ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል። የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ አቶ ሰይፉ ዋናካ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሠጥተዋል።
አቶ ሰይፉ ዋናካ ምን አሉ ?
° “ ቅሬታ ሲቀርብ ወርደን እናወያያለን። ከሁለት ወራት በፊት ወርደን አወያይተን፣ አግባብተን የትርፍ ሰዓት በየወሩ እየተከፈለ አይደለም እሱ ትክክል ነው። ግን ያው የተወዘፈም እየተከፈለ ነው ያለው። ”
° “ ችግሩ ካለ ወርደን እናስከፍላለን። የደመወዝ፣ የትርፍ ሰዓት ጉዳይ ከእኛ አቅም በላይ አይደለም። ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩ ካቅማችሁ በላይ ካልሆነ ከ9 ወራት በላይ ለምን ዘገዬ ? ሲል ጠይቋል።
ምላሽ ፦
° “ የከተማ አስተዳደሩ ችግርም ፣ አገራዊ ችግሮችም አለ። ሁሉ ወጥ አይሆንም። የከተማ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል ገብቷል። ስለዚህ የ10 ወራቱም ቢሆን ይከፈላል። ”
ጤና ባለሙያዎቹ በበኩላቸው፣ ከወራት በፊት ፒቲሽን ሰብስበው የትርፍ ሰዓት ሥራ እንደማይሰሩ አቋማቸውን ሲገልጹ ኃላፊዎች ቢያወያዩአቸውም ክፍያው እንዳልተሰጣቸው አስረድተዋል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
➡ “ ከ9 ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈለንም ”- ከ200 በላይ የጤና ባለሙያዎች
➡ “ የትርፍ ሰዓት በየወሩ እየተከፈለ አይደለም እሱ ትክክል ነው። የከተማ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል ገብቷል ” - የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ ጋሞ ዞን ፤ በሰላምበር ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎች ከ9 ወራት በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ጊዜ ሰዓት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ፣ ደመወዝም የሚገባላቸው እየተቆራረጠ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የጤና ባለሙያዎችን ወክለው ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ አንድ የጤና ባለሙያ ተከታዩን ብለዋል።
- “ ከ9 ወራት በላይ ለሚሆን ጊዜ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈለንም። ሳይከፈለን 10ኛ ወር እየሰራን ነው ያለነው። ”
- “ በሌላ በኩል ደግሞ ዋና ደመወዝ ሁሌም እየተቆራረጠ ነው የሚገባው። ግማሹ ብቻ ያስገቡና ግማሹ ደግሞ ሳይገባ ወሩ ያልቃል። ”
- “ የደመወዝ ሆነ የትርፍ ሰዓት ክፍያ በተመለከተ ቅሬታ ያለን 113 ጤና ባለሙያዎች (የትርፍ ሰዓት ያልተከፈላቸው) ፣ 103 ድጋፍ ሰጭ ባለሙያዎች (የትርፍ ሰዓት ክፍያ የማይመለከታቸው) ናቸው። ”
- “ ያልተከፈለው የክፍያ መጠን እንደ ጤና ባለሙያው ፤ አሁን ለምሳሌ የእኔ 5,000 ነው በወር የሚሆነው። 15 ሺሕ የሚከፈለው አለ። 30 ሺሕ የሚከፈለው አለ እንደ ስፔሻሊቲ ከሆነ። ”
በጉዳዩ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* የሰላምበር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የCOA ተወካይ አቶ ደካሶ ዲቻ፣
* የሰላምበር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘነበ ወንተ
* የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንደሻው ሽብሩን አግኝቶ ምላሽ እንዲሰጡ ቢሞክርም ፈቃደኛ አልሆኑም።
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ግን ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል። የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ አቶ ሰይፉ ዋናካ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሠጥተዋል።
አቶ ሰይፉ ዋናካ ምን አሉ ?
° “ ቅሬታ ሲቀርብ ወርደን እናወያያለን። ከሁለት ወራት በፊት ወርደን አወያይተን፣ አግባብተን የትርፍ ሰዓት በየወሩ እየተከፈለ አይደለም እሱ ትክክል ነው። ግን ያው የተወዘፈም እየተከፈለ ነው ያለው። ”
° “ ችግሩ ካለ ወርደን እናስከፍላለን። የደመወዝ፣ የትርፍ ሰዓት ጉዳይ ከእኛ አቅም በላይ አይደለም። ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩ ካቅማችሁ በላይ ካልሆነ ከ9 ወራት በላይ ለምን ዘገዬ ? ሲል ጠይቋል።
ምላሽ ፦
° “ የከተማ አስተዳደሩ ችግርም ፣ አገራዊ ችግሮችም አለ። ሁሉ ወጥ አይሆንም። የከተማ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል ገብቷል። ስለዚህ የ10 ወራቱም ቢሆን ይከፈላል። ”
ጤና ባለሙያዎቹ በበኩላቸው፣ ከወራት በፊት ፒቲሽን ሰብስበው የትርፍ ሰዓት ሥራ እንደማይሰሩ አቋማቸውን ሲገልጹ ኃላፊዎች ቢያወያዩአቸውም ክፍያው እንዳልተሰጣቸው አስረድተዋል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
#ስራ #ደመወዝ
° " ያለስራና ደመወዝ በመቆየታችን ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል " - የመንግስት ሰራተኞች
° " ጉዳዩን እናውቀዋለን እየተወያየንበት ነው ፥ በአጭር ቀናት መፍትሄ ይሰጣቸዋል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለስልጣን
የደቡብ ክልል መበተኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የ " ውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ሰራተኞች " ከስራ እና ከደመወዝ ውጭ ሆነው ወራት እንደተቆጠሩ ገልጸዋል።
ሰራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባቀረቡት ቅሬታ ፥ ክልሉ ከፈረሰ በኋላ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢመደቡም እስካሁን ስራ አለመጀመራቸውን በዚህም ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል።
ከ2 ወር በፊት ዘግይቶ በተሰጣቸው ደብዳቤ ሆሳዕና ከተማ መመደባቸው እንደተነገራቸው ጠቁመዋል።
ቦታው ላይ ተገኝተው ሪፖርት በማድረግ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንደሚሰጣቸውም ተገልጾላቸው ነበር።
በዚህም ግማሽ ሰራተኞች እቃቸውን በገንዘብ እጥረት ሽጠው እንዲሁም ቀሪውን በሌለ ገንዘብ ትራንስፖርት ከፍለው ቦታው ቢደርሱም አንድም የሚያስተናግዳቸው ሆነ የሚቀበላቸዉ አካል ማጣታቸውን አስረድተዋል።
በመሆኑም ያለደሞዝና ስራ በተመደቡበት ከተማ ለ2 ወራት መቆየታቸው ህይወትን ከባድ እንዳደረገባቸዉ ገልጸዋል።
በገንዘብ እጦት የምግብ መግዣ እንኳ እንስከማጣት መድረሳቸውን ከዚህም በላይ በቤት ኪራይ ችግር አብዛኛዉ ሰራተኛ ጎዳና ለመውጣት ጫፍ መድረሱን ተናግረዋል።
" ሆሳዕና የሚገኘው አዲሱ ቢሮ ስንሄድ #ጸሀፊ_ብቻ ነው የምናገኘው " የሚሉት ሰራተኞቹ " የሚመለከተው አካል ሌላዉ ቢቀር ጥያቄያችን ሊያደምጥ ይገባል " ሲሉ ቅሬታቸው ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞቹን ጥያቄ ይዞ ያናገራቸዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አማካሪ እና ልዩ ረዳት የሆኑትን አቶ ንጉሴ አስረስ ፥ ጉዳዩን እንደሚያውቁት በመግለጽ ችግሩ በቅርብ እንደሚፈታ ተናግረዋል።
ከሰሞኑ ሰራተኞችን በአካል አግኝተዋቸው ለማነጋገር እቅድ እንዳላቸውም የገለጹት አቶ ዘሪሁን " ለሁለት መቶ አስር ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል ለክልሉ ቀላል ነው " ብለዋል።
በቅርቡ ችግሩ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም ሌሎችም ተጨማሪ ጥያቄዎች ካሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያነጋግራቸው እንደሚችል ቃል ገብተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
#CentralEthiopiaRegion
@tikvahethiopia
° " ያለስራና ደመወዝ በመቆየታችን ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል " - የመንግስት ሰራተኞች
° " ጉዳዩን እናውቀዋለን እየተወያየንበት ነው ፥ በአጭር ቀናት መፍትሄ ይሰጣቸዋል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለስልጣን
የደቡብ ክልል መበተኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የ " ውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ሰራተኞች " ከስራ እና ከደመወዝ ውጭ ሆነው ወራት እንደተቆጠሩ ገልጸዋል።
ሰራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባቀረቡት ቅሬታ ፥ ክልሉ ከፈረሰ በኋላ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢመደቡም እስካሁን ስራ አለመጀመራቸውን በዚህም ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል።
ከ2 ወር በፊት ዘግይቶ በተሰጣቸው ደብዳቤ ሆሳዕና ከተማ መመደባቸው እንደተነገራቸው ጠቁመዋል።
ቦታው ላይ ተገኝተው ሪፖርት በማድረግ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንደሚሰጣቸውም ተገልጾላቸው ነበር።
በዚህም ግማሽ ሰራተኞች እቃቸውን በገንዘብ እጥረት ሽጠው እንዲሁም ቀሪውን በሌለ ገንዘብ ትራንስፖርት ከፍለው ቦታው ቢደርሱም አንድም የሚያስተናግዳቸው ሆነ የሚቀበላቸዉ አካል ማጣታቸውን አስረድተዋል።
በመሆኑም ያለደሞዝና ስራ በተመደቡበት ከተማ ለ2 ወራት መቆየታቸው ህይወትን ከባድ እንዳደረገባቸዉ ገልጸዋል።
በገንዘብ እጦት የምግብ መግዣ እንኳ እንስከማጣት መድረሳቸውን ከዚህም በላይ በቤት ኪራይ ችግር አብዛኛዉ ሰራተኛ ጎዳና ለመውጣት ጫፍ መድረሱን ተናግረዋል።
" ሆሳዕና የሚገኘው አዲሱ ቢሮ ስንሄድ #ጸሀፊ_ብቻ ነው የምናገኘው " የሚሉት ሰራተኞቹ " የሚመለከተው አካል ሌላዉ ቢቀር ጥያቄያችን ሊያደምጥ ይገባል " ሲሉ ቅሬታቸው ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞቹን ጥያቄ ይዞ ያናገራቸዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አማካሪ እና ልዩ ረዳት የሆኑትን አቶ ንጉሴ አስረስ ፥ ጉዳዩን እንደሚያውቁት በመግለጽ ችግሩ በቅርብ እንደሚፈታ ተናግረዋል።
ከሰሞኑ ሰራተኞችን በአካል አግኝተዋቸው ለማነጋገር እቅድ እንዳላቸውም የገለጹት አቶ ዘሪሁን " ለሁለት መቶ አስር ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል ለክልሉ ቀላል ነው " ብለዋል።
በቅርቡ ችግሩ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም ሌሎችም ተጨማሪ ጥያቄዎች ካሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያነጋግራቸው እንደሚችል ቃል ገብተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
#CentralEthiopiaRegion
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SouthEthiopiaRegion ➡️ " ... በረሀብ ከምንሞት መብታችን እየጠየቅን አደባባይ ላይ መሞት መርጠን ነው ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ የሄድነው " - የሶዶ ዙሪያ የመንግስት ሰራተኞች ➡️ " ማንም መብቱን በነጻነት የመጠየቅ መብት አለው " - የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃፊዉ አቶ ወገኔ ብዙነህ የ2 ወራት ደሞዛችን ይከፈለን ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች አደባባይ መውጣታቸዉን…
#ደመወዝ #ደቡብኢትዮጵያ
° " ...ድርጊቱ የደመወዝ ቅሸባ ነው ሊባል የሚችለው ፤ እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል ሰምተንም አናውቅ " - ሰራተኞች
° " ከእኛ #የሚወርደው የበጀት ሀብት እኮ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው " - የክልል ፋይናንስ ቢሮ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የመንግስት ሰራተኞች " የደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ በብርቱ ከተነሳባቸው አካባቢዎች አንዱና ዋነኛው የ #ወላይታ_ዞን እንደሆነ ይታወቃል።
ሰራተኞቹ ችግር ሲብስባቸው እና ታግሰው ሲመራቸው ሰልፍ ጭምር በመውጣት ጥያቄ አቅርበዋል።
ለ3 ወራት ያለ ደመወዝ የቆዩት የመንግስት ሰራተኞች አሁን ላይ #የ40_በመቶ እና #የ50_በመቶ ክፍያ ብቻ እየተፈጸመላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #የፋይናንስ_ቢሮ ፤ " ደመወዝ ባለመክፈል የመንግሥት ሰራተኛውን እያስራቡ ይገኛሉ " ባላቸው የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ #እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል።
ቢሮው ለወረዳዎቹ በቂ በጀት ማስተላለፉን ገልጿል።
" ለሰራተኛው #ግማሽ_ደመወዝ በመክፍል ቀሪውን ለሌላ የወጭ ርዕስ ይጠቀሙበታል " ሲል ወቅሷል።
አሁን በተለያዩ ወረዳዎች እየተከፈለ ይገኛል የተባለው ደመወዝ በዞኑ መንግሥት ሰራተኞች ዘንድ አጥጋቢ ምላሽ ተደርጎ አልተወሰደም።
ሰራተኞቹ ለ ' ዶቼ ቨለ ሬድዮ ' በሰጡት ቃል ፤ " ምላሹ አጥጋቢ ያልሆነ ፣ የሰራተኛውን ስነ ልቦናም የጎዳ ነው " ብለውታል።
የመንግስት ሰራተኞቹ ፥ ደመወዛቸው ባልተለመደ ሁኔታ ተቆራርጦ እየተከፈላቸው እንደሚገኝ ተናግረው ፤ " የሰራተኞች ጥያቄው ተመልሷል ለማለት እንቸገራለን " ብለዋል።
በአብዛኞቹ ወረዳዎች ላይ አሁን እየተከፈለ የሚገኘው የደመወዛቸውን ከ40 እስከ 50 ፐርሰት ያህል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሰራተኞቹ ፦
➡ ደሞዛችን እንደተፈለገ ተቆረጦ እየቀረ ነው፤
➡ አከፋፈሉ የፋይናንስንም ሆኖ የመንግሥት ሰራተኛ አስተዳደር መመሪያን የሚጻረር ነው፤
➡ ድርጊቱ #የደመወዝ_ቅሸባ እንጂ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም ምክንያቱም እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል በትኛውም ዓለም ሰምተን አናውቅም ብለዋል።
ሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ዎላይታ ሶዶ ላይ የፋይናንስ ባለሙያዎች ሥልጠናዊ ውይይት አካሄዶ ነበር።
በመድረኩ የደሞዝ ጉዳይ በሰራተኞች ተነስቷል፡፡
የቢሮው ሃላፊ የሆኑት አቶ ተፈሪ አባተ ፥ ፋይናንስ ቢሮ ለወረዳዎች በቂ የበጀት ሀብት እያስተላለፈ እንደሚገኝ አሳውቀዋል።
ወላይታን ጨምሮ በክልሉ አንዳንድ ወረዳዎች ውቅጥ የፋይናንስ ቁጥጥር / ኦዲት / መደረጉን ጠቅሰዋል።
" ወደ ወረዳዎች ሚወርደው የበጀት ሀብት የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው፡፡ ይሁን አንጂ አንዳንድ ወረዳዎች ከአሰራር ውጭ ደመወዝ #በፐርሰንት_እየከፈሉ ሰራተኛው እንዲራብ ፣ በክልሉ ላይም እንዲያማርር እያደረጉ ይገኛሉ " ብለዋል።
ክልሉ በቀጣይ በእነኝህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ " #ለሽብረቃ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን ለመገደብ የሚያስችል የወጭ ቅነሳ መመሪያ ተግባራዊ ይደረጋል " ሲሉ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።
Credit - #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
° " ...ድርጊቱ የደመወዝ ቅሸባ ነው ሊባል የሚችለው ፤ እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል ሰምተንም አናውቅ " - ሰራተኞች
° " ከእኛ #የሚወርደው የበጀት ሀብት እኮ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው " - የክልል ፋይናንስ ቢሮ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የመንግስት ሰራተኞች " የደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ በብርቱ ከተነሳባቸው አካባቢዎች አንዱና ዋነኛው የ #ወላይታ_ዞን እንደሆነ ይታወቃል።
ሰራተኞቹ ችግር ሲብስባቸው እና ታግሰው ሲመራቸው ሰልፍ ጭምር በመውጣት ጥያቄ አቅርበዋል።
ለ3 ወራት ያለ ደመወዝ የቆዩት የመንግስት ሰራተኞች አሁን ላይ #የ40_በመቶ እና #የ50_በመቶ ክፍያ ብቻ እየተፈጸመላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #የፋይናንስ_ቢሮ ፤ " ደመወዝ ባለመክፈል የመንግሥት ሰራተኛውን እያስራቡ ይገኛሉ " ባላቸው የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ #እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል።
ቢሮው ለወረዳዎቹ በቂ በጀት ማስተላለፉን ገልጿል።
" ለሰራተኛው #ግማሽ_ደመወዝ በመክፍል ቀሪውን ለሌላ የወጭ ርዕስ ይጠቀሙበታል " ሲል ወቅሷል።
አሁን በተለያዩ ወረዳዎች እየተከፈለ ይገኛል የተባለው ደመወዝ በዞኑ መንግሥት ሰራተኞች ዘንድ አጥጋቢ ምላሽ ተደርጎ አልተወሰደም።
ሰራተኞቹ ለ ' ዶቼ ቨለ ሬድዮ ' በሰጡት ቃል ፤ " ምላሹ አጥጋቢ ያልሆነ ፣ የሰራተኛውን ስነ ልቦናም የጎዳ ነው " ብለውታል።
የመንግስት ሰራተኞቹ ፥ ደመወዛቸው ባልተለመደ ሁኔታ ተቆራርጦ እየተከፈላቸው እንደሚገኝ ተናግረው ፤ " የሰራተኞች ጥያቄው ተመልሷል ለማለት እንቸገራለን " ብለዋል።
በአብዛኞቹ ወረዳዎች ላይ አሁን እየተከፈለ የሚገኘው የደመወዛቸውን ከ40 እስከ 50 ፐርሰት ያህል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሰራተኞቹ ፦
➡ ደሞዛችን እንደተፈለገ ተቆረጦ እየቀረ ነው፤
➡ አከፋፈሉ የፋይናንስንም ሆኖ የመንግሥት ሰራተኛ አስተዳደር መመሪያን የሚጻረር ነው፤
➡ ድርጊቱ #የደመወዝ_ቅሸባ እንጂ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም ምክንያቱም እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል በትኛውም ዓለም ሰምተን አናውቅም ብለዋል።
ሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ዎላይታ ሶዶ ላይ የፋይናንስ ባለሙያዎች ሥልጠናዊ ውይይት አካሄዶ ነበር።
በመድረኩ የደሞዝ ጉዳይ በሰራተኞች ተነስቷል፡፡
የቢሮው ሃላፊ የሆኑት አቶ ተፈሪ አባተ ፥ ፋይናንስ ቢሮ ለወረዳዎች በቂ የበጀት ሀብት እያስተላለፈ እንደሚገኝ አሳውቀዋል።
ወላይታን ጨምሮ በክልሉ አንዳንድ ወረዳዎች ውቅጥ የፋይናንስ ቁጥጥር / ኦዲት / መደረጉን ጠቅሰዋል።
" ወደ ወረዳዎች ሚወርደው የበጀት ሀብት የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው፡፡ ይሁን አንጂ አንዳንድ ወረዳዎች ከአሰራር ውጭ ደመወዝ #በፐርሰንት_እየከፈሉ ሰራተኛው እንዲራብ ፣ በክልሉ ላይም እንዲያማርር እያደረጉ ይገኛሉ " ብለዋል።
ክልሉ በቀጣይ በእነኝህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ " #ለሽብረቃ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን ለመገደብ የሚያስችል የወጭ ቅነሳ መመሪያ ተግባራዊ ይደረጋል " ሲሉ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።
Credit - #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
° " ደመወዝ በአግባቡ #እየተከፈለን_አይደለም ፤ የሚመለከተዉ አካል ካላናገረን ማስተማር አንችልም " - የከምባ ወረዳ መምህራን
° " በየሶሻል ሚዲያ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ ገጽታችንን የሚያበላሹትን በህግ እንጠይቃለን " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ
° " ያልተከፈላቸው መምህራን #ስራ_ስለማቆማቸው መረጃ አለኝ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር
ከሰሞኑ በጋሞ ዞን ከምባ ወረዳ መምህራን " ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈለን አይደለም " በማለት ቅሬታቸዉን አሰምተዋል።
" ዞኑ ውስጥ ካሉት ሀያ ክላስተሮች ተለይተን ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ መምህራን ስራ ማቆማቸውንና የሚመለከተው አካል ካላናገራቸው ስራ እንደማይገቡ በመግለጽ ቅሬታቸዉን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህንን የመምህራን ጉዳይ ሰምቶ ይመለከታቸው ያላቸውን አካላት ማለትም ፥ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበርና የዞኑን ትምህርት መምሪያ አነጋግሯል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ምን አሉ ?
አቶ አማኑኤል ፥ " በዞኑ በከምባ ወረዳ #ለመምህራን እየተከፈለ ያለው ደሞዝ የተቆራረጠና አግባብ ባልሆነ መልኩ እየተፈጸመ ነው " ብለዋል።
አክለውም ፤ " በክላስተር ተቆራርጦ ከመክፈሉ ባለፈ በአንድ ትምህርት ቤት እንኳን ለጥቂት መምህራን ተከፍሎ ለአብዛኛው ደግሞ አለመከፈሉ ያበሳጫቸው መምህራን ስራ አለመግባታቸውን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ስለመዘጋታቸው መረጃ አለን " ብለዋል።
የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊው አቶ አብርሀም አምሳሉ ምን አሉ ?
አቶ አብርሀም ፤ " ያለኝ መረጃ ለመምህራን ደመወዝ በአግባቡ እየተከፈላቸው መሆኑን እና ስራም እየተሰራ መሆኑን ነው " ብለዋል።
" ይሁንና በየሶሻል ሚዲያው ላይ የአካባቢውን ገጽታ ለማጠልሸት በማሰብ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት ወሬውን እያናፈሱት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" እነዚህ አካላት በህግ እየተጠየቁ ሲሆን ወደፊትም ይጠየቃሉ " ብለዋል።
ምን አልባት ያልተከፈላቸዉ መምህራን ካሉ የዲስፕሊን እና መሰል ችግር ያለባቸው ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ላይ ትምህርት መቋረጡን የሚመለከት መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ችግር ተከስቶ ከሆነ እንደሚስተካከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
° " ደመወዝ በአግባቡ #እየተከፈለን_አይደለም ፤ የሚመለከተዉ አካል ካላናገረን ማስተማር አንችልም " - የከምባ ወረዳ መምህራን
° " በየሶሻል ሚዲያ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ ገጽታችንን የሚያበላሹትን በህግ እንጠይቃለን " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ
° " ያልተከፈላቸው መምህራን #ስራ_ስለማቆማቸው መረጃ አለኝ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር
ከሰሞኑ በጋሞ ዞን ከምባ ወረዳ መምህራን " ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈለን አይደለም " በማለት ቅሬታቸዉን አሰምተዋል።
" ዞኑ ውስጥ ካሉት ሀያ ክላስተሮች ተለይተን ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ መምህራን ስራ ማቆማቸውንና የሚመለከተው አካል ካላናገራቸው ስራ እንደማይገቡ በመግለጽ ቅሬታቸዉን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህንን የመምህራን ጉዳይ ሰምቶ ይመለከታቸው ያላቸውን አካላት ማለትም ፥ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበርና የዞኑን ትምህርት መምሪያ አነጋግሯል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ምን አሉ ?
አቶ አማኑኤል ፥ " በዞኑ በከምባ ወረዳ #ለመምህራን እየተከፈለ ያለው ደሞዝ የተቆራረጠና አግባብ ባልሆነ መልኩ እየተፈጸመ ነው " ብለዋል።
አክለውም ፤ " በክላስተር ተቆራርጦ ከመክፈሉ ባለፈ በአንድ ትምህርት ቤት እንኳን ለጥቂት መምህራን ተከፍሎ ለአብዛኛው ደግሞ አለመከፈሉ ያበሳጫቸው መምህራን ስራ አለመግባታቸውን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ስለመዘጋታቸው መረጃ አለን " ብለዋል።
የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊው አቶ አብርሀም አምሳሉ ምን አሉ ?
አቶ አብርሀም ፤ " ያለኝ መረጃ ለመምህራን ደመወዝ በአግባቡ እየተከፈላቸው መሆኑን እና ስራም እየተሰራ መሆኑን ነው " ብለዋል።
" ይሁንና በየሶሻል ሚዲያው ላይ የአካባቢውን ገጽታ ለማጠልሸት በማሰብ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት ወሬውን እያናፈሱት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" እነዚህ አካላት በህግ እየተጠየቁ ሲሆን ወደፊትም ይጠየቃሉ " ብለዋል።
ምን አልባት ያልተከፈላቸዉ መምህራን ካሉ የዲስፕሊን እና መሰል ችግር ያለባቸው ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ላይ ትምህርት መቋረጡን የሚመለከት መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ችግር ተከስቶ ከሆነ እንደሚስተካከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
" ለግል ድርጅቶች ሠራተኞችም የደመወዝ ማስተካከያ የሚደረግበት አቅጣጫ እንዲሰጥ ለመንግስት ጥያቄ ቀርቧል " - ኢሠማኮ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መንግሥት ይፋ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ተከትሎ ለመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ይደረጋል በተባለው ልክ፣ ለግል ድርጅቶች ሠራተኞችም ማስተካከያ የሚደረግበት አቅጣጫ እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርቧል።
የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ " በመንግሥት በጀት ለሚተዳደሩት የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ የግል ድርጅቶችና ተቋማት በራሳቸው በጀትና ትርፍ የሚንቀሳቀሱ በመሆኑናቸው፣ በትርፋቸው ላይ ተመሥርተው ለሠራተኛ የደመወዝ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ከመንግሥት አቅጣጫ እየተጠበቀ ነው " ብለዋል።
" የሠራተኞችና የደመወዝ ዝቅተኛው ወለል እንዲወጣ እየወተወትን ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
የመንግሥት እና የግል ሠራተኞች አንዱ የተሻለ አንዱ የወደቀ የሚባል ክፍያ ሊኖር አይገባም ሲሉ አክለዋል።
" መንግሥት ይህን ጉዳይ ሊዘነጋው አይችልም የሚል እምነት ቢኖረንም፣ መሰል አገራዊ አጋጣሚዎችና ቀውሶች በሚኖሩበት ጊዜ ባለሀብቶችንና ተቋማትን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች በማድረግና ውይይቶች በማካሄድ አቅጣጫዎች ሊሰጡበት ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ለአገርም አይጠቅምም፣ የኢንዱስትሪ ሰላም አይኖርም፣ ሠራተኛውም ተረጋግቶ ሥራውን ማከናወን አይችልም " ብለዋል።
አቶ አያሌው፣ " ጉዳዩ እጅግ በጣም አሳሳቢ ስለሆነ መንግሥት አቅጣጫ የማይሰጥበት ከሆነ ኢሠማኮ ጥያቄውን በጽሑፍ ለመንግሥት ያቀርባል " በማለት አስረድተዋል፡፡
" ሠራተኛው በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት በልቶ ማደር አልቻለም፣ የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አልቻለም፣ ይህን ማንም ያውቀዋል ሚስጥር አይደለም፣ አሠሪዎቹ ለሚያሠሯቸው ዜጎች ተመጣጣኝ የሆነ ክፍያ መክፈል አለባቸው " ብለዋል፡፡
የሠራተኛ መብት መከበር እንዳለበት " የሚያረጋግጥ ወጥ የሆነ ሕግ ያስፈልጋል " ያሉት አቶ አያሌው፣ " የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልና ሌሎች የሠራተኞች መብቶችና ጥቅማ ጥቅሞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን መንግሥት ለምን እንዳዘገያቸው አልገባኝም " ሲሉ ገልጸዋል።
" የዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ጉዳይ ላይ አሁንም መንግሥት የዘነጋው ይመስላል " ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ኢሠማኮ ተጨማሪ ጥያቄ ሊያቀርብ እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
አክለው ፥ ከመንግሥት ተቋማት በተሻለ የሚያተርፉት የግል ተቋማት፣ ከመንግሥት የደመወዝ ጭማሪ ጋር እኩል ላለመጨመር ትልቁ ችግር የአስተሳሰብ ጉዳይ እንጂ፣ የገንዘብ እጥረት አይደለም በማለት ለዜጎች ማዘን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ለራስ ብቻ ከማግበስበስ ዕሳቤ በመውጣት ምርታማ ሠራተኛን ለማፍራት፣ አሁን ተመጣጣኝ የደመወዝ ጭማሪ ማድረግ ብዙ ነው የሚያሰኝ አለመሆኑን ገልጸዋል።
#EthiopianReporter #Salary #Ethiopia
@tikvahethiopia
" ለግል ድርጅቶች ሠራተኞችም የደመወዝ ማስተካከያ የሚደረግበት አቅጣጫ እንዲሰጥ ለመንግስት ጥያቄ ቀርቧል " - ኢሠማኮ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መንግሥት ይፋ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ተከትሎ ለመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ይደረጋል በተባለው ልክ፣ ለግል ድርጅቶች ሠራተኞችም ማስተካከያ የሚደረግበት አቅጣጫ እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርቧል።
የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ " በመንግሥት በጀት ለሚተዳደሩት የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ የግል ድርጅቶችና ተቋማት በራሳቸው በጀትና ትርፍ የሚንቀሳቀሱ በመሆኑናቸው፣ በትርፋቸው ላይ ተመሥርተው ለሠራተኛ የደመወዝ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ከመንግሥት አቅጣጫ እየተጠበቀ ነው " ብለዋል።
" የሠራተኞችና የደመወዝ ዝቅተኛው ወለል እንዲወጣ እየወተወትን ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
የመንግሥት እና የግል ሠራተኞች አንዱ የተሻለ አንዱ የወደቀ የሚባል ክፍያ ሊኖር አይገባም ሲሉ አክለዋል።
" መንግሥት ይህን ጉዳይ ሊዘነጋው አይችልም የሚል እምነት ቢኖረንም፣ መሰል አገራዊ አጋጣሚዎችና ቀውሶች በሚኖሩበት ጊዜ ባለሀብቶችንና ተቋማትን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች በማድረግና ውይይቶች በማካሄድ አቅጣጫዎች ሊሰጡበት ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ለአገርም አይጠቅምም፣ የኢንዱስትሪ ሰላም አይኖርም፣ ሠራተኛውም ተረጋግቶ ሥራውን ማከናወን አይችልም " ብለዋል።
አቶ አያሌው፣ " ጉዳዩ እጅግ በጣም አሳሳቢ ስለሆነ መንግሥት አቅጣጫ የማይሰጥበት ከሆነ ኢሠማኮ ጥያቄውን በጽሑፍ ለመንግሥት ያቀርባል " በማለት አስረድተዋል፡፡
" ሠራተኛው በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት በልቶ ማደር አልቻለም፣ የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አልቻለም፣ ይህን ማንም ያውቀዋል ሚስጥር አይደለም፣ አሠሪዎቹ ለሚያሠሯቸው ዜጎች ተመጣጣኝ የሆነ ክፍያ መክፈል አለባቸው " ብለዋል፡፡
የሠራተኛ መብት መከበር እንዳለበት " የሚያረጋግጥ ወጥ የሆነ ሕግ ያስፈልጋል " ያሉት አቶ አያሌው፣ " የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልና ሌሎች የሠራተኞች መብቶችና ጥቅማ ጥቅሞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን መንግሥት ለምን እንዳዘገያቸው አልገባኝም " ሲሉ ገልጸዋል።
" የዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ጉዳይ ላይ አሁንም መንግሥት የዘነጋው ይመስላል " ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ኢሠማኮ ተጨማሪ ጥያቄ ሊያቀርብ እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
አክለው ፥ ከመንግሥት ተቋማት በተሻለ የሚያተርፉት የግል ተቋማት፣ ከመንግሥት የደመወዝ ጭማሪ ጋር እኩል ላለመጨመር ትልቁ ችግር የአስተሳሰብ ጉዳይ እንጂ፣ የገንዘብ እጥረት አይደለም በማለት ለዜጎች ማዘን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ለራስ ብቻ ከማግበስበስ ዕሳቤ በመውጣት ምርታማ ሠራተኛን ለማፍራት፣ አሁን ተመጣጣኝ የደመወዝ ጭማሪ ማድረግ ብዙ ነው የሚያሰኝ አለመሆኑን ገልጸዋል።
#EthiopianReporter #Salary #Ethiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia " ማንኛውም ማሻሻያ ወይም የደመወዝ ስኬል ለውጥ ካለ ሕጋዊ ሰውነት ባላቸው እና በሚመለከታቸው አካላት ይፋ ይደረጋል " ሲል የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አሳውቋል። ውሳኔዎቹ ሲኖሩ በዝርዝር ጥናቶችና የበጀት አጸዳደቅ ሥርዓትን ተከትለው የሚካሄዱ እንደሆኑ ገልጿል። የትኛውንም አይነት መረጃ ሁልጊዜም በቀጥታ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ማጣራት እና ማገናዘብ ከስህተት ይታደጋልም ብሏል። የትላንትናው…
የመንግሥት_ሰራተኞች_የደመወዝ_ጭማሪ_1.pdf
14.9 MB
#ደመወዝ ፦ ይህ ስለ መንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ዶክመንት ባለፈው ዓመት ነሃሴ ወር ላይ ሲዘዋወር የነበር ነው።
ዶክመንቱ ከየትኛው አካል የወጣ እንደሆነ በግልጽ አይታወቅም።
በእርግጥም ከዚህ ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባው የመንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ ይኸው ይሁን ወይስ ሌላ ስለሚለው ጉዳይ ወይም ደግሞ ስለዚህ ዶክመንት ትክክለኝነት ወይም ትክክል አለመሆን በግልጽ ወጥቶ ምላሽ የሰጠ አንድም አካል የለም።
ይህ ዶክመንት ወጥቶ ከመሰራጨቱ በፊት አንድ ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ምስል ተሰራጭቶ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ' ሀሰት ' ነው ማለቱ አይዘነጋም።
ስለዚህ የደመወዝ ጭማሪ ዶክመንት ግን ወጥቶ ያስተባበለ ሆነ ማረጋገጫ የሰጠ አካል የለም።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ ይመለከታቸዋል የተባሉ አካላትን በማነጋገር ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም አልተሳካም።
NB. ከላይ በፋይል የተያያዘው ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትተው ዶክመት በቀጥታ ጉዳዩ በሚመላከታቸው የትኛውም አካላት ያልተረጋገጠ ነገር ግን ደግሞ በይፋ ትክክል አይደለም ተብሎ ማስተባበያ ሆነ አስተያየት ያልተሰጠበት ነው።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
ዶክመንቱ ከየትኛው አካል የወጣ እንደሆነ በግልጽ አይታወቅም።
በእርግጥም ከዚህ ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባው የመንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ ይኸው ይሁን ወይስ ሌላ ስለሚለው ጉዳይ ወይም ደግሞ ስለዚህ ዶክመንት ትክክለኝነት ወይም ትክክል አለመሆን በግልጽ ወጥቶ ምላሽ የሰጠ አንድም አካል የለም።
ይህ ዶክመንት ወጥቶ ከመሰራጨቱ በፊት አንድ ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ምስል ተሰራጭቶ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ' ሀሰት ' ነው ማለቱ አይዘነጋም።
ስለዚህ የደመወዝ ጭማሪ ዶክመንት ግን ወጥቶ ያስተባበለ ሆነ ማረጋገጫ የሰጠ አካል የለም።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ ይመለከታቸዋል የተባሉ አካላትን በማነጋገር ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም አልተሳካም።
NB. ከላይ በፋይል የተያያዘው ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትተው ዶክመት በቀጥታ ጉዳዩ በሚመላከታቸው የትኛውም አካላት ያልተረጋገጠ ነገር ግን ደግሞ በይፋ ትክክል አይደለም ተብሎ ማስተባበያ ሆነ አስተያየት ያልተሰጠበት ነው።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
" የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " - የገንዘብ ሚኒስቴር
የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ፤ ከመስከረም ወር 2017 ጀምሮ የሚጨመር ደመወዝ በካቢኔ መፅደቁን አሳውቀዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ትኩረት ያደረገ የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉን አመልክተዋል።
አቶ አህመድ " የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ ለኑሮ ድጎማ ጭምር እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ በካቢኔ ፀድቋል ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ ይደረጋል። የደመወዝ ጭማሪው ከ91 እስከ 92 ቢሊዮን ብር መካከል ተጨማሪ በጀት የሚጠይቅ ይሆናል " ብለዋል።
በነባሩ በጀት የተወሰነ መግባቱን ፤ በተጨማሪ በጀትነትም የሚታወጅ መኖሩን ጠቁመዋል።
" ሲቪል ሰርቫንቱ አጠቃላይ የመንግሥት ሰራተኛው በሁሉም መስክ በፀጥታም በሌሎችም ዘርፍ ያሉትን የኑሮ ጫና ለመቋቋም የሚያስችለውን ድጋፍ ለማድረግ መንግሥት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ተገባበት ነው " ሲሉ አቶ አህመድ ተናግረዋል።
" የባለፉት ሁለት ወራት የኢንፍሌሽን አፈጻጸም በሚታይበት ጊዜ እንደተሰጋው አይደለም። የተረጋጋ የዋጋ ሁኔታ ነው ያለው። የተወስነ ጭማሪ በአንዳንድ እቃዎች ላይ እንጂ በአብዛኛው የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። " ብለዋል።
" እንደዛም ሆኖ የደመወዝ ጭማሪው እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ የሰራተኛውን ቋሚ ደመወዝተኛ ገቢ ያለውን ዝቅተኛውን ትኩረት አድርገን የዝቅተኛውን በጣም ከፍተኛ ጭማሪ አድርገናል የላይኛውን ዝቅተኛ ጭማሪ አድርገን ነው የተሰራው ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
" የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " - የገንዘብ ሚኒስቴር
የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ፤ ከመስከረም ወር 2017 ጀምሮ የሚጨመር ደመወዝ በካቢኔ መፅደቁን አሳውቀዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ትኩረት ያደረገ የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉን አመልክተዋል።
አቶ አህመድ " የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ ለኑሮ ድጎማ ጭምር እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ በካቢኔ ፀድቋል ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ ይደረጋል። የደመወዝ ጭማሪው ከ91 እስከ 92 ቢሊዮን ብር መካከል ተጨማሪ በጀት የሚጠይቅ ይሆናል " ብለዋል።
በነባሩ በጀት የተወሰነ መግባቱን ፤ በተጨማሪ በጀትነትም የሚታወጅ መኖሩን ጠቁመዋል።
" ሲቪል ሰርቫንቱ አጠቃላይ የመንግሥት ሰራተኛው በሁሉም መስክ በፀጥታም በሌሎችም ዘርፍ ያሉትን የኑሮ ጫና ለመቋቋም የሚያስችለውን ድጋፍ ለማድረግ መንግሥት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ተገባበት ነው " ሲሉ አቶ አህመድ ተናግረዋል።
" የባለፉት ሁለት ወራት የኢንፍሌሽን አፈጻጸም በሚታይበት ጊዜ እንደተሰጋው አይደለም። የተረጋጋ የዋጋ ሁኔታ ነው ያለው። የተወስነ ጭማሪ በአንዳንድ እቃዎች ላይ እንጂ በአብዛኛው የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። " ብለዋል።
" እንደዛም ሆኖ የደመወዝ ጭማሪው እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ የሰራተኛውን ቋሚ ደመወዝተኛ ገቢ ያለውን ዝቅተኛውን ትኩረት አድርገን የዝቅተኛውን በጣም ከፍተኛ ጭማሪ አድርገናል የላይኛውን ዝቅተኛ ጭማሪ አድርገን ነው የተሰራው ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን ይጀምራል " - አቶ አህመድ ሽዴ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ፤ የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን እንደሚጀምር አሳውቀዋል። " ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ደመወዝ በካቢኔ ተወስኗል። ባለፉት ሳምንታት በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ቅድመ ዝግጅቱ አልቋል ፤ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንም በኩል ቅድመ ዝግጅት አልቋል…
#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል።
ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።
(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)
#CivilServiceCommission
#MekuriaHaile
@tikvahethiopia
ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።
(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)
#CivilServiceCommission
#MekuriaHaile
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል። ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል። (ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ…
#ደመወዝ
" በእኛ መስሪያ ቤት በኩል የተስተካከለው የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " - መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር)
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ፥ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያን በተመለከተ ባሰራጩት ፅሁፍ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " ብለዋል።
" ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። " ሲሉ ገልጸዋል።
" እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል " ሲሉ አስረድተዋል።
" የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች እየተራመዱ ነው " ያሉት ኮሚሽነሩ " በሲቪል ሰርቪስ በኩል የሚለቀቁ መረጃዎች ኦፊሴላዊና የሚተገበሩ መሆኑን መተማመን ጥሩ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ከሠራተኞች ደመወዝ ስኬል ጋር በተገናኘ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ አሳሳች ወሬዎችን እንዳታምኗቸው መልዕክት አስተላልፌ ነበር " ሲሉም አክለዋል።
ከሰሞኑን ከሠራተኞች ደመወዝ ጋር በተገናኘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች መረጃዎችን ተዘዋውረዋል።
ከነዚህም አንዱ ጭማሪው እንዳልተከፈለ የሚገልጽ ነው።
ነገር ግን በአንዳንድ መ/ቤቶች ጭማሪው መከፈሉ ታውቋል። ጭማሪው ያልተከፈለባቸውም መ/ቤቶችም ግን አሉ ፤ እነዚህ ናቸው ' እያጣሩ ናቸው " የተባሉት።
" ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ያን ያህል አይደለም " - ሠራተኞች
" የደመወዝ ጭማሪ ይደረጋል " የሚለውን መረጃ የሰሙ ሠራተኞች ከፍተኛ ጭማሪ ጠብቀው እንደነበር ነገር ግን እጃቸው ላይ የደረሰው እዚህ ግባ የማይባል እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ ሠራተኛ ፥ " ምንኑን ከምኑን ልናደርገው ይሄ ብቻ እንደተጨመረ አልገባኝም " ብለዋል።
ጭማሪው አነስተኛ እንደሆነ የገለጹ አንዲት ሠራተኛ በበኩላቸው " ከሚጨመረው ብር በላይ ወሬው በዝቶ ይበልጥ ኑሮውን እንዳያስወድደው " ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
" አይደለም ደመወዝ ተጨመረ ተብሎ ሳይባል እንኳን ነጋዴው ሁሉን ነገር አምጥቶ የሚጭነው እኛው ድሃው ዜጎች ላይ ነው አሁን ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ከኑሮው ውድነቱ አንጻር ያን ያህል አይደለም፤ ጭራሽ ነጋዴዎቹ ዋጋ ጨምረው አሁንም አልገፋ ያለውን ኑሮን እንዳያከብዱብን " ብለዋል።
ያነጋገርናቸው ሌሎችም ሠራተኞች " ደመወዝ ተጨመረ " የተባለው አነስተኛ እንደሆነ፣ የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ ፣ ሌሎች የሠራተኞችን ህይወት የሚያቀሉ መፍትሄዎች እንዲፈለጉ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" በእኛ መስሪያ ቤት በኩል የተስተካከለው የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " - መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር)
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ፥ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያን በተመለከተ ባሰራጩት ፅሁፍ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " ብለዋል።
" ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። " ሲሉ ገልጸዋል።
" እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል " ሲሉ አስረድተዋል።
" የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች እየተራመዱ ነው " ያሉት ኮሚሽነሩ " በሲቪል ሰርቪስ በኩል የሚለቀቁ መረጃዎች ኦፊሴላዊና የሚተገበሩ መሆኑን መተማመን ጥሩ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ከሠራተኞች ደመወዝ ስኬል ጋር በተገናኘ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ አሳሳች ወሬዎችን እንዳታምኗቸው መልዕክት አስተላልፌ ነበር " ሲሉም አክለዋል።
ከሰሞኑን ከሠራተኞች ደመወዝ ጋር በተገናኘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች መረጃዎችን ተዘዋውረዋል።
ከነዚህም አንዱ ጭማሪው እንዳልተከፈለ የሚገልጽ ነው።
ነገር ግን በአንዳንድ መ/ቤቶች ጭማሪው መከፈሉ ታውቋል። ጭማሪው ያልተከፈለባቸውም መ/ቤቶችም ግን አሉ ፤ እነዚህ ናቸው ' እያጣሩ ናቸው " የተባሉት።
" ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ያን ያህል አይደለም " - ሠራተኞች
" የደመወዝ ጭማሪ ይደረጋል " የሚለውን መረጃ የሰሙ ሠራተኞች ከፍተኛ ጭማሪ ጠብቀው እንደነበር ነገር ግን እጃቸው ላይ የደረሰው እዚህ ግባ የማይባል እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ ሠራተኛ ፥ " ምንኑን ከምኑን ልናደርገው ይሄ ብቻ እንደተጨመረ አልገባኝም " ብለዋል።
ጭማሪው አነስተኛ እንደሆነ የገለጹ አንዲት ሠራተኛ በበኩላቸው " ከሚጨመረው ብር በላይ ወሬው በዝቶ ይበልጥ ኑሮውን እንዳያስወድደው " ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
" አይደለም ደመወዝ ተጨመረ ተብሎ ሳይባል እንኳን ነጋዴው ሁሉን ነገር አምጥቶ የሚጭነው እኛው ድሃው ዜጎች ላይ ነው አሁን ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ከኑሮው ውድነቱ አንጻር ያን ያህል አይደለም፤ ጭራሽ ነጋዴዎቹ ዋጋ ጨምረው አሁንም አልገፋ ያለውን ኑሮን እንዳያከብዱብን " ብለዋል።
ያነጋገርናቸው ሌሎችም ሠራተኞች " ደመወዝ ተጨመረ " የተባለው አነስተኛ እንደሆነ፣ የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ ፣ ሌሎች የሠራተኞችን ህይወት የሚያቀሉ መፍትሄዎች እንዲፈለጉ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል። ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል። ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦ - ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣ - ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣ - ለካፒታል ፕሮጀክቶች…
#ኢትዮጵያ
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
🚨 " የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው " - ገቢዎች ቢሮ
🔴 " ቢሮው የፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ነው " - የህግ ምሁር
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሆቴሎች እና መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ በተመረጡ የንግድ መስኮች የሚሰሩ ሰራተኞችን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞቻቸውን ብዛት የሚተምን ተመን አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል።
ሆቴሎች፣ ስጋ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ የሰራተኞች ደመወዝን በተመለከተ አሰሪዎች ትክክለኛ መረጃ ስለማይሰጡ ግብር እያጭበረበሩ ነው ብሏል።
ይህንን ተከትሎም ነው ይህን አሰራር መዘርጋቱን ገልጻል።
ስራ ላይ በዋለው ተመን መሰረት ፦
👉 የሆቴሎች ከ32 እስከ 50 ሰራተኞች
👉 ባርና ሬስቶራን ከ20 እስከ 24 ሰራተኞች
👉 ካፍቴሪካ ከ17 እስከ 25 ሰራተኞች
👉 ምግብ ቤት ከ17 እስከ 22 ሰራተኞች
👉 ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት ከ28 እስከ 48
👉 ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ ከ20 እስከ 28 ሰራተኞች ይኖራቸዋል ተብሎ ተተምኗል።
በዚህ መሰረት የደመወዝ ግብር በተጠቀሰው የሰራተኛ ቁጥር ልክ ይጠየቃሉ።
ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።
የወር ደመወዝ ተመኑ ምን ይመስላል ?
➡ ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ5,000 እስከ 9,500
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ3,000 እስከ 3,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 7,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ / ከ6,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
➡ ካፍቴሪያ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ6,000 እስከ 7,000
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,500 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ሻይ ቡና / ጁስ አስተናጋጅ ከ5,000 እስከ 8,000
➡ ባርና ሬስቶራንት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ7,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 2,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ3,000 እስከ 3,500
➡ ሆቴል
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
ወርሃዊ ደመወዝ ተተምኗል።
ይህ ለአንድ ሰራተኛ ይከፈላል ተብሎ የተተመነ ነው።
በዚህ ተመን ባለቤቶቹ የደመወዝ ግብር ሲከፍሉ ለተጠቀሱት የስራ መደቦች " ከዚህ ያነሰ ነው የምከፍለው " ማለት አይችሉም።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ምን አሉ ?
ቢሮው ተመን ማውጣቱን አረጋግጠዋል።
ዳይሬክተሩ " በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው ውሳኔው የተቀመጠው።
ከደመወዝ ግብር ጋር በተያያዘ የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው። በጣም ትልቅ ክፍተት ነው ያለው እኛ በከተማችን ያሉ የስራ መደቦችን በዝርዝር ጥናት አድርገን አብዛኛው በትንሹ የሚከፈላቸው ከ5000 ብር በላይ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።
ለፅዳት እና የቤት ሰራተኛ እንኳን ስንት እንደሚከፈል ይታወቃል።
እነሱ እንከፍላለን ብለው የሚያቀርቡት ዋጋ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። ያንን ምንቀበልበት ሁኔታ የለም አሰራሩም አይፈቅድም። ጥናት ላይ ተመስርተን ዝቅተኛውን ተመን አስቀምጠናል " ብለዋል።
ገቢዎች ቢሮ ከተማውን የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ኃላፊነት እንደተጣለበትና በዚህም ምክንያት ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን ስራ ላይ እንዳዋለ አሳውቋል።
ጉዳዩ በሚመለከተው አካል ህግ ሆኖ ሳይወጣ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን አስቀምጦ ግብር መሰብሰብ ይቻላል ወይ ? የሚለው የህግ ጥያቄ ተነስቶበታል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድና የኢኮኖሚ ህጎች መምህር አቶ ጌዲዮን ወ/ዮሐንስ ምን ይላሉ ?
" ድርጊቱ ህገወጥ ነው።
እስካሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በገቢዎች በኩል አነስተኛ ደመወዝን መወሰን ያንን ተከትሎ ግብር መሰስበብ እስካሁን ባለው የህግ ማዕቀፍ ይህንን የሚፈቅድ ነገር ስለሌለ ህጋዊ አይደለም።
በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ ህገመንግስቱ ግብር የሚጣለው በህግ ነው ይላል። በአንድ አስፈጻሚ / በአንድ የስራ ክፍል ኃላፊ ወይም እንደ ገቢዎች ቢሮ አይነት ደብዳቤን መሰረት አድርጎ ደመወዝን መወሰን አይቻልም።
ደመወዝ ግብር የሚከፈልበት አንድ ገቢ ነው። ይሄም ታክስ ቤዝ / ግብር የሚጣልበት አንድ ገቢ እንለዋለን። እሱ በህግ ተወስኗል። ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከዚህ እስከዚህ ሲሆን ይሄን ያህል ... ከዚህ እስከዚህ ይሄን ያህል ... ብር እየተባለ በግብር አዋጃችን ላይ ተቀምጧል።
በዚህ በገቢ ግብር አዋጅ ላይ በተለያዩ የስራ ክፍሎችና አይነቶች የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛውን የደመወዝ መጠን ለመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል የሚል ህግ የለም ኢትዮጵያ ላይ።
በህግ ባልተከለከለበት / አይቻልም ባልተባለበት ሁኔታ አንድ ሰው 10,000 ብር ነው ዝቅተኛ መቅጠር የምትችለው ፣ በ8,000 ነው በ18,000 እያሉ ሰንጠረዥ ማውጣት የሰዎችን የመዋዋል ነጻነት ይጎዳል።
ድርጊቱ፦
- የመዋዋል ነጻነትን የሚገድብ
- ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የሚጥስ ተግባር ነው።
ቢሮው ' ግብር እየተጭበረበርኩ ነው ' ብሎ ካሰበ የተለያዩ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ፣ የስራ ውሉን ከአሰሪዎቹ በመቀበል ይሄም ደግሞ በህግ አነስተኛ ደወመዝን በማውጣትና በመደንገግ ነው። እንጂ የግብር ማጭበርበር ለመከላከል ተብሎ የገቢ ግብርን በዚህ መንገድ ለማስተዳደር መሞከር የታክስ ህግን፣ መርሆችን የሚጥስ ነው። "
NB. በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ መንግሥት ለግሉ ዘርፍ ለተቀጣሪዎች ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አላስቀመጠም። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲያስቀምጥ ጥረቶች እየተደረጉ እነደሆነ ይታወቃል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia
🚨 " የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው " - ገቢዎች ቢሮ
🔴 " ቢሮው የፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ነው " - የህግ ምሁር
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሆቴሎች እና መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ በተመረጡ የንግድ መስኮች የሚሰሩ ሰራተኞችን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞቻቸውን ብዛት የሚተምን ተመን አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል።
ሆቴሎች፣ ስጋ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ የሰራተኞች ደመወዝን በተመለከተ አሰሪዎች ትክክለኛ መረጃ ስለማይሰጡ ግብር እያጭበረበሩ ነው ብሏል።
ይህንን ተከትሎም ነው ይህን አሰራር መዘርጋቱን ገልጻል።
ስራ ላይ በዋለው ተመን መሰረት ፦
👉 የሆቴሎች ከ32 እስከ 50 ሰራተኞች
👉 ባርና ሬስቶራን ከ20 እስከ 24 ሰራተኞች
👉 ካፍቴሪካ ከ17 እስከ 25 ሰራተኞች
👉 ምግብ ቤት ከ17 እስከ 22 ሰራተኞች
👉 ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት ከ28 እስከ 48
👉 ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ ከ20 እስከ 28 ሰራተኞች ይኖራቸዋል ተብሎ ተተምኗል።
በዚህ መሰረት የደመወዝ ግብር በተጠቀሰው የሰራተኛ ቁጥር ልክ ይጠየቃሉ።
ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።
የወር ደመወዝ ተመኑ ምን ይመስላል ?
➡ ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ5,000 እስከ 9,500
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ3,000 እስከ 3,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 7,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ / ከ6,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
➡ ካፍቴሪያ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ6,000 እስከ 7,000
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,500 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ሻይ ቡና / ጁስ አስተናጋጅ ከ5,000 እስከ 8,000
➡ ባርና ሬስቶራንት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ7,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 2,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ3,000 እስከ 3,500
➡ ሆቴል
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
ወርሃዊ ደመወዝ ተተምኗል።
ይህ ለአንድ ሰራተኛ ይከፈላል ተብሎ የተተመነ ነው።
በዚህ ተመን ባለቤቶቹ የደመወዝ ግብር ሲከፍሉ ለተጠቀሱት የስራ መደቦች " ከዚህ ያነሰ ነው የምከፍለው " ማለት አይችሉም።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ምን አሉ ?
ቢሮው ተመን ማውጣቱን አረጋግጠዋል።
ዳይሬክተሩ " በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው ውሳኔው የተቀመጠው።
ከደመወዝ ግብር ጋር በተያያዘ የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው። በጣም ትልቅ ክፍተት ነው ያለው እኛ በከተማችን ያሉ የስራ መደቦችን በዝርዝር ጥናት አድርገን አብዛኛው በትንሹ የሚከፈላቸው ከ5000 ብር በላይ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።
ለፅዳት እና የቤት ሰራተኛ እንኳን ስንት እንደሚከፈል ይታወቃል።
እነሱ እንከፍላለን ብለው የሚያቀርቡት ዋጋ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። ያንን ምንቀበልበት ሁኔታ የለም አሰራሩም አይፈቅድም። ጥናት ላይ ተመስርተን ዝቅተኛውን ተመን አስቀምጠናል " ብለዋል።
ገቢዎች ቢሮ ከተማውን የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ኃላፊነት እንደተጣለበትና በዚህም ምክንያት ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን ስራ ላይ እንዳዋለ አሳውቋል።
ጉዳዩ በሚመለከተው አካል ህግ ሆኖ ሳይወጣ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን አስቀምጦ ግብር መሰብሰብ ይቻላል ወይ ? የሚለው የህግ ጥያቄ ተነስቶበታል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድና የኢኮኖሚ ህጎች መምህር አቶ ጌዲዮን ወ/ዮሐንስ ምን ይላሉ ?
" ድርጊቱ ህገወጥ ነው።
እስካሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በገቢዎች በኩል አነስተኛ ደመወዝን መወሰን ያንን ተከትሎ ግብር መሰስበብ እስካሁን ባለው የህግ ማዕቀፍ ይህንን የሚፈቅድ ነገር ስለሌለ ህጋዊ አይደለም።
በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ ህገመንግስቱ ግብር የሚጣለው በህግ ነው ይላል። በአንድ አስፈጻሚ / በአንድ የስራ ክፍል ኃላፊ ወይም እንደ ገቢዎች ቢሮ አይነት ደብዳቤን መሰረት አድርጎ ደመወዝን መወሰን አይቻልም።
ደመወዝ ግብር የሚከፈልበት አንድ ገቢ ነው። ይሄም ታክስ ቤዝ / ግብር የሚጣልበት አንድ ገቢ እንለዋለን። እሱ በህግ ተወስኗል። ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከዚህ እስከዚህ ሲሆን ይሄን ያህል ... ከዚህ እስከዚህ ይሄን ያህል ... ብር እየተባለ በግብር አዋጃችን ላይ ተቀምጧል።
በዚህ በገቢ ግብር አዋጅ ላይ በተለያዩ የስራ ክፍሎችና አይነቶች የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛውን የደመወዝ መጠን ለመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል የሚል ህግ የለም ኢትዮጵያ ላይ።
በህግ ባልተከለከለበት / አይቻልም ባልተባለበት ሁኔታ አንድ ሰው 10,000 ብር ነው ዝቅተኛ መቅጠር የምትችለው ፣ በ8,000 ነው በ18,000 እያሉ ሰንጠረዥ ማውጣት የሰዎችን የመዋዋል ነጻነት ይጎዳል።
ድርጊቱ፦
- የመዋዋል ነጻነትን የሚገድብ
- ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የሚጥስ ተግባር ነው።
ቢሮው ' ግብር እየተጭበረበርኩ ነው ' ብሎ ካሰበ የተለያዩ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ፣ የስራ ውሉን ከአሰሪዎቹ በመቀበል ይሄም ደግሞ በህግ አነስተኛ ደወመዝን በማውጣትና በመደንገግ ነው። እንጂ የግብር ማጭበርበር ለመከላከል ተብሎ የገቢ ግብርን በዚህ መንገድ ለማስተዳደር መሞከር የታክስ ህግን፣ መርሆችን የሚጥስ ነው። "
NB. በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ መንግሥት ለግሉ ዘርፍ ለተቀጣሪዎች ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አላስቀመጠም። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲያስቀምጥ ጥረቶች እየተደረጉ እነደሆነ ይታወቃል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia