ፎቶ ፦ በአዲስ አበባ ፤ ፒያሳ የሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት (ተርሚናል) መስጠት መጀመሩ ተገልጿል።
የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ ፥ " ህብረተሰቡ ደህንነቱ ተጠብቆ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት የሚያገኝበትን የከተማ አውቶብስ #ተርሚናል አስጀምረናል " ብሏል።
ቀድሞ በፒያሳ እና አከባቢው ሲሰጡ የነበሩ አስር የከተማ አውቶብስ መስመሮች ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም ገብተው በአንድ ተርሚናል አገልግሎት መስጠት እንደጀመሩ ተጠቁሟል።
ህብረተሰቡ በሙዚየሙ በ " ምስራቅ ጀግኖች በር " በመግባት ወደ ፦
- አየር ጤና፣
- ካራ ቆሬ፣
- ቦሌ ቡልቡላ፣
- ሳሪስ፣
- ኮልፌ ቀራኒዮ፣
- አጃምባ፣
- ጀሞ 3፣
- ሃና ማርያም፣
- ቱሉዲምቱ
- ዩኒሳ የሚሄዱ የብዙሃን ትራንስፖርት (አውቶብስ) ማግኘት እንደሚችል የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ጠቁሟል።
@tikvahethiopia
የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ ፥ " ህብረተሰቡ ደህንነቱ ተጠብቆ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት የሚያገኝበትን የከተማ አውቶብስ #ተርሚናል አስጀምረናል " ብሏል።
ቀድሞ በፒያሳ እና አከባቢው ሲሰጡ የነበሩ አስር የከተማ አውቶብስ መስመሮች ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም ገብተው በአንድ ተርሚናል አገልግሎት መስጠት እንደጀመሩ ተጠቁሟል።
ህብረተሰቡ በሙዚየሙ በ " ምስራቅ ጀግኖች በር " በመግባት ወደ ፦
- አየር ጤና፣
- ካራ ቆሬ፣
- ቦሌ ቡልቡላ፣
- ሳሪስ፣
- ኮልፌ ቀራኒዮ፣
- አጃምባ፣
- ጀሞ 3፣
- ሃና ማርያም፣
- ቱሉዲምቱ
- ዩኒሳ የሚሄዱ የብዙሃን ትራንስፖርት (አውቶብስ) ማግኘት እንደሚችል የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ጠቁሟል።
@tikvahethiopia
#መቐለ
በመቐለ ቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ፥ ዘስላሴ ቀበሌ ቀጠና 14 በሚገኘ " እየሩሳሌም " በተባለ ሆቴል እፍሬም ፍትዊ ገ/ክርስቶስ የተባሉ ግለሰብ በመኝታ ክፍል ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን የክ/ከተማው ፖሊስ ገልጿል።
ግለሰቡ መጋቢት 20/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ነው በያዙት የመኝታ ክፍል ውስጥ ሞተው የተገኙት።
የአሟሟታቸው ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችል የአስክሬን ምርምራ በዓይደር ሆስፒታል በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የሟች ቤተሰቦች እስከ መጋቢት 22 /2016 ዓ.ም ባለው ጊዜ ወደ ፖሊስ ሪፓርት ካላደረጉ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ከአስከሬን ምርመራ በኃላ የቀብር ስነ-ሰርአት ለመፈፀም እንደሚገደድ ፖሊስ አመልክቷል። (104.4 የመቐለ ኤፍኤም ሬድዮ)
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በመቐለ ቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ፥ ዘስላሴ ቀበሌ ቀጠና 14 በሚገኘ " እየሩሳሌም " በተባለ ሆቴል እፍሬም ፍትዊ ገ/ክርስቶስ የተባሉ ግለሰብ በመኝታ ክፍል ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን የክ/ከተማው ፖሊስ ገልጿል።
ግለሰቡ መጋቢት 20/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ነው በያዙት የመኝታ ክፍል ውስጥ ሞተው የተገኙት።
የአሟሟታቸው ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችል የአስክሬን ምርምራ በዓይደር ሆስፒታል በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የሟች ቤተሰቦች እስከ መጋቢት 22 /2016 ዓ.ም ባለው ጊዜ ወደ ፖሊስ ሪፓርት ካላደረጉ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ከአስከሬን ምርመራ በኃላ የቀብር ስነ-ሰርአት ለመፈፀም እንደሚገደድ ፖሊስ አመልክቷል። (104.4 የመቐለ ኤፍኤም ሬድዮ)
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#CBE የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ገንዘቡን እንዲመልሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን ስም ዝርዝርም ይፋ አድርጓል። ባንኩ ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት በህገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዱ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስቦ ነበር። በዚህ መሰረት 9281 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን…
#CBE
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ #የራሳቸውን_ያልሆነውን ገንዘብ ከባንኩ ወስደው ሙሉ በሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) 5166 ግለሰቦች የሚቀረውን ብር እንዲመልሱ የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ ዛሬ ቅዳሜ 11:00 ላይ ያበቃል።
ባንኩ ፤ ገንዘቡን #የማይመልሱ ካሉ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ፦
- ሙሉ ስማቸው
- ፎቷቸው
- በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን በመግለፅ ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት እንዲሁም ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አሳስቦ ነበር።
ባንኩ ከቀናት በፊት ፤ ገንዘብ ወስደው ጭራሽ ያልመለሱ 565 ደንበኞቹንና በከፊል መልሰው የሚቀር ገንዘብ ያልመለሱ 5166 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይወሳል።
በሌላ በኩል ፤ አንዳንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የወሰዱትን እና ወደ ግል ባንኮች ያዘዋወሩትን ገንዘብ በዲጂታል መንገድ ወደ ንግድ ባንክ ቢመልሱም ገንዘብ ካልመለሱት ጋር ስማቸው መውጣቱን በመግለፅ ንግድ ባንክ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ንግድ ባንክ ዓርብ በመጋቢት 6 / 2016 ለሊት በ25,761 ደንበኞች ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ እንደተወሰደበት ከዛ ውስጥ 622 ሚሊዮን ያህሉን ማስመለሱን ከ4 ቀን በፊት መግለጹ ይወቃል።
@tikvahethiopia
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ #የራሳቸውን_ያልሆነውን ገንዘብ ከባንኩ ወስደው ሙሉ በሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) 5166 ግለሰቦች የሚቀረውን ብር እንዲመልሱ የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ ዛሬ ቅዳሜ 11:00 ላይ ያበቃል።
ባንኩ ፤ ገንዘቡን #የማይመልሱ ካሉ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ፦
- ሙሉ ስማቸው
- ፎቷቸው
- በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን በመግለፅ ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት እንዲሁም ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አሳስቦ ነበር።
ባንኩ ከቀናት በፊት ፤ ገንዘብ ወስደው ጭራሽ ያልመለሱ 565 ደንበኞቹንና በከፊል መልሰው የሚቀር ገንዘብ ያልመለሱ 5166 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይወሳል።
በሌላ በኩል ፤ አንዳንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የወሰዱትን እና ወደ ግል ባንኮች ያዘዋወሩትን ገንዘብ በዲጂታል መንገድ ወደ ንግድ ባንክ ቢመልሱም ገንዘብ ካልመለሱት ጋር ስማቸው መውጣቱን በመግለፅ ንግድ ባንክ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ንግድ ባንክ ዓርብ በመጋቢት 6 / 2016 ለሊት በ25,761 ደንበኞች ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ እንደተወሰደበት ከዛ ውስጥ 622 ሚሊዮን ያህሉን ማስመለሱን ከ4 ቀን በፊት መግለጹ ይወቃል።
@tikvahethiopia
የተረክ በM-PESA የመጨረሻው 6ኛ ዙር እድለኞች ሽልማቶቻቸውን ተረክበዋል ፤ መኪናዋን የምዕራብ አርሲ አሳሳ ደንበኛችን ፣ የጅግጅጋው ነጋዴ ፣ባጃጇን ከዲላ ፣ከሐረር አራተኛ ፣ከእንጅባራ ወስደዋታል!
ስለነበረን የተረክ በM-PESA ወራት ወሳኞቻችንን ከልብ እናመሰግናለን ፤ በዚህ አናበቃም እንቀጥላለን ፤ በአብሮነት ወደፊት!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#MPESASafaricom
#TerekBeMPESA #FurtherAheadTogether
ስለነበረን የተረክ በM-PESA ወራት ወሳኞቻችንን ከልብ እናመሰግናለን ፤ በዚህ አናበቃም እንቀጥላለን ፤ በአብሮነት ወደፊት!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#MPESASafaricom
#TerekBeMPESA #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#ትግራይ #አማራ
" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።
" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።
" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።
እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።
" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።
" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።
" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።
" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።
" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።
እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።
" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።
" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።
" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
#IOM
" እ.ኤ.አ ከ2014 እስከ 2023 ቢያንስ 63,285 ሰዎች ሞተዋል / የገቡበት አይታወቅም " - IOM
እ.ኤ.አ. ከ2014 እስከ 2023 ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ 63,285 ሰዎች በዓለም ላይ ባሉ ስደተኞች በሚጓዙበት መስመር ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ጠፍተዋል።
አብዛኞቹ ህይወታቸውን ያጡት ደግሞ በውሃ መስጠም ምክንያት ነው።
እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ሪፖርት መሰረት 28,854 ሰዎች የሞቱት እና የት እንደገቡ ያልታወቀው በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ነው።
ከተመዘገቡት የሟቾች ቁጥር ወደ 60 በመቶ የሚጠጋው ከመስጠም ጋር የተያያዘ ሲሆን ከየት እንደሆነ ከተለዩት ውስጥ ደግሞ ከአንድ ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት በግጭት ውስጥ ካሉ ሀገራት ማለትም ፦
- አፍጋኒስታን፣
- ማይንማር፣
- ሶሪያ
- #ኢትዮጵያ የሄዱ ናቸው።
ከባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለስደተኞች በጣም ገዳይ እና የከፋ የነበረው 2023 ሲሆን 8,541 ሞት ተመዝግቧል።
ዓመቱ በሜዲትራኒያን ባህር በከፍተኛ ሁኔታ ሞት የጨመረበትም ነው።
እጅግ በርካታ አፍሪካውያን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚል በህገወጥ መንገድ እጅግ አስከፊ በሆነ መንገድ ወደ #ሊቢያ ሄደው በባህር ተጉዘው አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የባህር ሲሳይ ሆነው ቀርተዋል።
እንደ ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃ ፥ አስከፊው ጉዞ አድርገው እድለኛ ሆነው በህይወት ዛሬም ድረስ መረጋጋት ወደሌላት #ሊቢያ የሚገቡ ከሆነ እገታ ፣ ስቃይ ፣ ድብደባ አለፍ ሲልም ግድያ ሊፈፀምባቸው ይችላል።
በኃላም በባህር ጉዞ ከሊቢያ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ህይወታቸውን ያጣሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
" እ.ኤ.አ ከ2014 እስከ 2023 ቢያንስ 63,285 ሰዎች ሞተዋል / የገቡበት አይታወቅም " - IOM
እ.ኤ.አ. ከ2014 እስከ 2023 ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ 63,285 ሰዎች በዓለም ላይ ባሉ ስደተኞች በሚጓዙበት መስመር ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ጠፍተዋል።
አብዛኞቹ ህይወታቸውን ያጡት ደግሞ በውሃ መስጠም ምክንያት ነው።
እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ሪፖርት መሰረት 28,854 ሰዎች የሞቱት እና የት እንደገቡ ያልታወቀው በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ነው።
ከተመዘገቡት የሟቾች ቁጥር ወደ 60 በመቶ የሚጠጋው ከመስጠም ጋር የተያያዘ ሲሆን ከየት እንደሆነ ከተለዩት ውስጥ ደግሞ ከአንድ ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት በግጭት ውስጥ ካሉ ሀገራት ማለትም ፦
- አፍጋኒስታን፣
- ማይንማር፣
- ሶሪያ
- #ኢትዮጵያ የሄዱ ናቸው።
ከባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለስደተኞች በጣም ገዳይ እና የከፋ የነበረው 2023 ሲሆን 8,541 ሞት ተመዝግቧል።
ዓመቱ በሜዲትራኒያን ባህር በከፍተኛ ሁኔታ ሞት የጨመረበትም ነው።
እጅግ በርካታ አፍሪካውያን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚል በህገወጥ መንገድ እጅግ አስከፊ በሆነ መንገድ ወደ #ሊቢያ ሄደው በባህር ተጉዘው አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የባህር ሲሳይ ሆነው ቀርተዋል።
እንደ ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃ ፥ አስከፊው ጉዞ አድርገው እድለኛ ሆነው በህይወት ዛሬም ድረስ መረጋጋት ወደሌላት #ሊቢያ የሚገቡ ከሆነ እገታ ፣ ስቃይ ፣ ድብደባ አለፍ ሲልም ግድያ ሊፈፀምባቸው ይችላል።
በኃላም በባህር ጉዞ ከሊቢያ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ህይወታቸውን ያጣሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#CBE
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ?
መጋቢት 7 / 2016 ዓ/ም ባጋጠመው የሲስተም ችግር ምክንያት ያለአግባብ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበር ፤ በዚህም በርካታ ግለሰቦች በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የወሰዱትን የገንዘብ ልክ እየመለሱ እንደሆነ ገልጿል።
ነገር ግን አንዳንድ ግለሰቦች የወሰዱትን ገንዘብ ወደ #ቤቲንግ (የስፖርት ውርርድ) ተቋማት በማዛወራቸው መመለስ እንደተቸገሩ ጥቆማ እንደሰጡት ገልጿል።
ገንዘቡን ተመላሽ ማድረግ እንዲቻል ወደ ቤቲንግ ተቋማት የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ያዘዋወሩ አቅራቢያቸው በሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመገኘት ለዚሁ የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት እንዲያመለክቱ አሳስቧል።
ባንኩ ገንዘብ ወስደው ሙሉ ሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) ቀሪ ያልመለሱትን ገንዘብ እንዲመልሱ በማለት ለ5,166 ደንበኞቹ የሰጠው የመጨረሻ ማሳስቢያ ዛሬ ቅዳሜ አብቅቷል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ?
መጋቢት 7 / 2016 ዓ/ም ባጋጠመው የሲስተም ችግር ምክንያት ያለአግባብ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበር ፤ በዚህም በርካታ ግለሰቦች በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የወሰዱትን የገንዘብ ልክ እየመለሱ እንደሆነ ገልጿል።
ነገር ግን አንዳንድ ግለሰቦች የወሰዱትን ገንዘብ ወደ #ቤቲንግ (የስፖርት ውርርድ) ተቋማት በማዛወራቸው መመለስ እንደተቸገሩ ጥቆማ እንደሰጡት ገልጿል።
ገንዘቡን ተመላሽ ማድረግ እንዲቻል ወደ ቤቲንግ ተቋማት የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ያዘዋወሩ አቅራቢያቸው በሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመገኘት ለዚሁ የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት እንዲያመለክቱ አሳስቧል።
ባንኩ ገንዘብ ወስደው ሙሉ ሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) ቀሪ ያልመለሱትን ገንዘብ እንዲመልሱ በማለት ለ5,166 ደንበኞቹ የሰጠው የመጨረሻ ማሳስቢያ ዛሬ ቅዳሜ አብቅቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አስቸኳይ “ አጋቾቹ ወደ ታች ዘቅዝቀው እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ‘1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን #ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን’ አሉኝ ” - የታጋች እናት በሊቢያ ደላሎች የታገተው የሀዋሳው ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ወጣት ጌድዮ ሳሙኤል፣ በአጋቾቹ ልዩ ልዩ ድብደባዎች እየተፈጸሙበት እንደሚገኝ ፣ አጋቾቹ ወጣቱን ለመልቀቅ 1.7 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ፣ ገንዘቡ በፍጥነት ካልገባ “ እንገድለዋለን ”…
“አጋቾቹ እያሰቃዩት ነው። ዱብ እዳ ወረደብኝ። ወደ 950 ሺሕ ጠይቀዋል። ልጄ ‘በአንድ መጋዘን ወደ 200 ሰዎች ታጎርን’ ነው የሚለው ” - የታጋች አባት
በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ካሜራ ማን ሆኖ ሲሰራ ነበር የተባለው ወጣት አብርሃም አማረ #በሊቢያ በአጋቾች #ታግቶ በየቀኑ ስቃይ እየደረሰበት መሆኑን ፣ አጋቾቹ ታጋቹን ወጣት ለመልቀቅ 950 ሺሕ ብር እንደጠየቁ፣ ይህን ገንዘብ ማሟላት እንዳልተቻለ የታጋች አባት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የታጋች አባት አቶ አማረ ዓለም ገረመው ምን አሉ ?
- “ አጋቸቹ እያሰቃዩት ነው። ዱብ እዳ ወረደብኝ። ወደ 950 ሺሕ ተጠይቀዋል። ልጄ ‘ከአንድ መጋዘን ወደ 200 ሰዎች ታጎርን’ ነው የሚለው። እኛ ኑሯችን ዝቅተኛ ነው። ፈተና ላይ ነኝ። ምን አይነት ደላላ አታሎ እንደወሰደው ፈጣሪ ይወቅ። ”
- “ ሌሎችም ታጋቾች ‘ነፍስ ውጪ የፍስ ግቢ፣ ስቃይ’ ላይ እንደሆኑ ልጄ ነግሮኛል። ”
- “ በጥቅም የተሳሰረ ምን አይነተ ጊዜ ላይ እንደደረስን ፈጣሪ ይወቅ። ልጄ በዚህ ደረጃ ላይ ይጠብቀኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። ”
- “ አጋቾቹ ገንዘቡን በፍጥነት አስተላልፉ እያሉ እያጣደፏን ነው። እስካሁን ወደ 450 ሺሕ ብር ቢገኝም ቀሪው 500 ሺሕ ብር ገና አልተሟላም እየታገልኩ ነው። ”
- “ ልጄ ለዚህ እገታ የተዳረገው፣ ሕይወቱን ለማሻሻል ወደ ሌላ አገር እየሄደ ሊቢያ ሲደርስ ነው። ”
- “ ከዚህ በፊት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ይከታተል የነበረ ቢሆንም በኮረና ወቅት እንደተቋረጠ፣ በዚህም አጋጣሚ ካሜራ ማን ሰልጥኖ በተለያዩ ተቋማት ተቀጥሮ 1,000 ብር እየተከፈለው ይሰራ ነበር። ”
- “ ዲግሪውን በግል እንዲማር እየጎተጎትኩት ነበር። ሆኖም ግን በደላሎች ተታሎ አሁን እሱም በስቃይ፣ ቤተሰብን በጭንቀት ላይ ወድቋል። ”
- “ አጋቾቹ ቀረጻውን ይልካሉ፣ የሱን ግን ድምጹን ነው የሚያሰሙኝ። ‘ስቃይ ነው እስከ 2 ወራት ታግተው የቆዩት በየቀኑ ነው የሚገረፉት ብር አምጡ እየተባሉ’ ብሏል። ”
የታጋች አባት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሁንም ፦
- የዓለም ባንክ፣
- የቄራና የሌሎች አካባቢ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ ወደ ውጪ እየሄዱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ይህ ደግሞ ለወጣቶቹም ለወላጅም፣ ለአገርም ፈተና ስለሆነ ትኩረት እንዲሰጠው መክረዋል።
“ ይሄ ነገር ይገጥመኛል ብዬ አልጠበኩም። ” ያሉት አባት አቶ አማረ “ ልጆቼ እንዳይርባቸው፣ እንዳይጠማቸው፣ ከቁም ነገር እንዲደርሱ ነበር የምጥረው። አቅም ያላችሁ ሁሉ እርዳታ አድርጉልኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።
+251911388792 የታጋቹ አባት አቶ አማረ ዓለም ገረመውን በዚህ ስልክ ማግኘት ይቻላል። መርዳት ለምትፈልጉ 1000030178638 አቶ አማረ ዓለም ገረመው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ከትላንትና በስቲያ #በሊቢያ ደላሎች የታገተ የሀዋሳ ከተማ ተወላጅ ወጣት ጌድዮ ሳሙኤል፣ በአጋቾቹ ልዩ ልዩ ድብደባዎች እየተፈጸሙበት እንደሚገኝ ፣ አጋቾቹ ወጣቱን ለመልቀቅ 1.7 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ፣ ገንዘቡ በፍጥነት ካልገባ “ #እንገድለዋለን ” በማለት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡ የታጋችን እናት በማነጋገር መረጃ እንደላከላችሁ ይታወሳል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ካሜራ ማን ሆኖ ሲሰራ ነበር የተባለው ወጣት አብርሃም አማረ #በሊቢያ በአጋቾች #ታግቶ በየቀኑ ስቃይ እየደረሰበት መሆኑን ፣ አጋቾቹ ታጋቹን ወጣት ለመልቀቅ 950 ሺሕ ብር እንደጠየቁ፣ ይህን ገንዘብ ማሟላት እንዳልተቻለ የታጋች አባት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የታጋች አባት አቶ አማረ ዓለም ገረመው ምን አሉ ?
- “ አጋቸቹ እያሰቃዩት ነው። ዱብ እዳ ወረደብኝ። ወደ 950 ሺሕ ተጠይቀዋል። ልጄ ‘ከአንድ መጋዘን ወደ 200 ሰዎች ታጎርን’ ነው የሚለው። እኛ ኑሯችን ዝቅተኛ ነው። ፈተና ላይ ነኝ። ምን አይነት ደላላ አታሎ እንደወሰደው ፈጣሪ ይወቅ። ”
- “ ሌሎችም ታጋቾች ‘ነፍስ ውጪ የፍስ ግቢ፣ ስቃይ’ ላይ እንደሆኑ ልጄ ነግሮኛል። ”
- “ በጥቅም የተሳሰረ ምን አይነተ ጊዜ ላይ እንደደረስን ፈጣሪ ይወቅ። ልጄ በዚህ ደረጃ ላይ ይጠብቀኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። ”
- “ አጋቾቹ ገንዘቡን በፍጥነት አስተላልፉ እያሉ እያጣደፏን ነው። እስካሁን ወደ 450 ሺሕ ብር ቢገኝም ቀሪው 500 ሺሕ ብር ገና አልተሟላም እየታገልኩ ነው። ”
- “ ልጄ ለዚህ እገታ የተዳረገው፣ ሕይወቱን ለማሻሻል ወደ ሌላ አገር እየሄደ ሊቢያ ሲደርስ ነው። ”
- “ ከዚህ በፊት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ይከታተል የነበረ ቢሆንም በኮረና ወቅት እንደተቋረጠ፣ በዚህም አጋጣሚ ካሜራ ማን ሰልጥኖ በተለያዩ ተቋማት ተቀጥሮ 1,000 ብር እየተከፈለው ይሰራ ነበር። ”
- “ ዲግሪውን በግል እንዲማር እየጎተጎትኩት ነበር። ሆኖም ግን በደላሎች ተታሎ አሁን እሱም በስቃይ፣ ቤተሰብን በጭንቀት ላይ ወድቋል። ”
- “ አጋቾቹ ቀረጻውን ይልካሉ፣ የሱን ግን ድምጹን ነው የሚያሰሙኝ። ‘ስቃይ ነው እስከ 2 ወራት ታግተው የቆዩት በየቀኑ ነው የሚገረፉት ብር አምጡ እየተባሉ’ ብሏል። ”
የታጋች አባት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሁንም ፦
- የዓለም ባንክ፣
- የቄራና የሌሎች አካባቢ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ ወደ ውጪ እየሄዱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ይህ ደግሞ ለወጣቶቹም ለወላጅም፣ ለአገርም ፈተና ስለሆነ ትኩረት እንዲሰጠው መክረዋል።
“ ይሄ ነገር ይገጥመኛል ብዬ አልጠበኩም። ” ያሉት አባት አቶ አማረ “ ልጆቼ እንዳይርባቸው፣ እንዳይጠማቸው፣ ከቁም ነገር እንዲደርሱ ነበር የምጥረው። አቅም ያላችሁ ሁሉ እርዳታ አድርጉልኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።
+251911388792 የታጋቹ አባት አቶ አማረ ዓለም ገረመውን በዚህ ስልክ ማግኘት ይቻላል። መርዳት ለምትፈልጉ 1000030178638 አቶ አማረ ዓለም ገረመው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ከትላንትና በስቲያ #በሊቢያ ደላሎች የታገተ የሀዋሳ ከተማ ተወላጅ ወጣት ጌድዮ ሳሙኤል፣ በአጋቾቹ ልዩ ልዩ ድብደባዎች እየተፈጸሙበት እንደሚገኝ ፣ አጋቾቹ ወጣቱን ለመልቀቅ 1.7 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ፣ ገንዘቡ በፍጥነት ካልገባ “ #እንገድለዋለን ” በማለት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡ የታጋችን እናት በማነጋገር መረጃ እንደላከላችሁ ይታወሳል።
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
#DStv
🔥ደማቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ ተመልስዋል🔥
🏆አስተማሪው ከ ተማሪው ጋርለዓመቱ የመጨረሻ ጊዜ ይገናኛሉ!
👉ዛሬ እሁድ መጋቢት 22 ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት ማን ሲቲ ከ አርሰናል በኢትሃድ ስታዲየም የሚያረጉትን እስገራሚ ፍልሚያ በቀጥታ በSSPremier League እና በSS Liyu ቻናል በቀጥታ ይከታተሉ!
👉 መድፈኞቹ 3 ነጥብይዛው የሊጉን መሪነታቸውን ይቀጥላሉ?
🎉ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!
🎉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ! https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2
#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp
🔥ደማቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ ተመልስዋል🔥
🏆አስተማሪው ከ ተማሪው ጋርለዓመቱ የመጨረሻ ጊዜ ይገናኛሉ!
👉ዛሬ እሁድ መጋቢት 22 ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት ማን ሲቲ ከ አርሰናል በኢትሃድ ስታዲየም የሚያረጉትን እስገራሚ ፍልሚያ በቀጥታ በSSPremier League እና በSS Liyu ቻናል በቀጥታ ይከታተሉ!
👉 መድፈኞቹ 3 ነጥብይዛው የሊጉን መሪነታቸውን ይቀጥላሉ?
🎉ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!
🎉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ! https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2
#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሌክልል በሶማሌ ክልል በተከሰተው የጎርፍ አደጋ እስካሁን 28 ሰዎች ሲሞቱ ከ300,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ተጠቆመ። በሶማሌ ክልል ከ33 ወረዳዎች በላይ ተከሰተ የተባለውን የጎርፍ አደጋ በተመለከተ ተጎጂዎችና ተፈናቃዮች በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው እርዳታ እያደረገ የሚገኘውን Save the Childrenን ጠይቋል። የድርጅቱ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ…
“ ከተጎጂዎች መካከል 30,427 ህፃናት ናቸው። የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ ደርሷል ” - ሴቭ ዘ ቺልድረን
በሶማሌ ክልል ከተከሰተ የወራት ያለፈው የጎርፍ አደጋ የውሃ መጠኑ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም ትንበያዎች የሚያመለክቱት በመጪው የዝናብ ወቅት ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንዲሚችል ስለሆነ፣ ህብረተሰቡም አሁንም ካለፈው የጎርፍ አደጋ ገና እያገገመ በመሆኑ፣ ትልቅ ፈተናና ስጋት መፍጠሩን በቦታው የሚገኘው የህፃና አድን አድን ድርጅት (Save the children) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የድርጅቱ ሶማሌ ክልል ምሥራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ አህመድ ምን አሉ ?
- “ ጎርፉ ከቀነሰ በኋላ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ። በሚመለሱ ጊዜ ግን ቤታቸውን ለመጠገን፣ እንደገና ለመገንባት፣ ቁሳቁሶችን ለማሟላት ድጋፍ ይፈልጋሉ። ሆኖም ይህ ድጋፍ በሚፈለገው መጠን አልተሰጠም። ”
- “ በክልሉ በጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ ደርሷል። ” (ከወራት በፊት የሟቾች ቁጥር 23 እንደነበር ይታወሳል)
- “ አደጋው በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን አፈናቅሏል። በሶማሌ ክልል ብቻ ከ1,000,000 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል። 400,000 የሚሆኑ ተፈናቅለዋል። ”
- “ በተለይ የሸበሌ ዞን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ በዞኑ የሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች ከሞላ ጎደል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ”
- “ በጎርፍ አደጋው ላይ በተደረገው የጋራ ዳሰሳ ፦ 84, 800 አባውራዎች (490, 000 ሰዎች) ተጎድተዋል። ከእነዚህም መካከል 34, 441 የሚሆኑ አባውራዎች (206, 646 ሰዎች) በሸበሌ ዞን በሚገኙ 8 ወረዳዎች ተፈናቅለዋል። ከተጎጂዎች መካከል 49, 430 ሴቶች፣ 30, 427 ህጻናት እና 25, 253 አረጋውያን ናቸው። ”
- “ ከብቶች በጎርፍ አደጋው በጣም ተጎድተዋል፣ እንደሚታወቀው ለበርካታ ተጎጂ ማህበረሰቦች ወሳኝ የገቢ ምንጭ ናቸው። በጎርፉ አደጋው ከ19, 822 በላይ እንስሳት ሞተዋል። መተዳደሪያቸው የነበረ ከ94,000 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰብልም ወድሟል። በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ሙሉና በከፊል ወድመዋል። ”
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-31
@tikvahethiopia
በሶማሌ ክልል ከተከሰተ የወራት ያለፈው የጎርፍ አደጋ የውሃ መጠኑ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም ትንበያዎች የሚያመለክቱት በመጪው የዝናብ ወቅት ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንዲሚችል ስለሆነ፣ ህብረተሰቡም አሁንም ካለፈው የጎርፍ አደጋ ገና እያገገመ በመሆኑ፣ ትልቅ ፈተናና ስጋት መፍጠሩን በቦታው የሚገኘው የህፃና አድን አድን ድርጅት (Save the children) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የድርጅቱ ሶማሌ ክልል ምሥራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ አህመድ ምን አሉ ?
- “ ጎርፉ ከቀነሰ በኋላ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ። በሚመለሱ ጊዜ ግን ቤታቸውን ለመጠገን፣ እንደገና ለመገንባት፣ ቁሳቁሶችን ለማሟላት ድጋፍ ይፈልጋሉ። ሆኖም ይህ ድጋፍ በሚፈለገው መጠን አልተሰጠም። ”
- “ በክልሉ በጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ ደርሷል። ” (ከወራት በፊት የሟቾች ቁጥር 23 እንደነበር ይታወሳል)
- “ አደጋው በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን አፈናቅሏል። በሶማሌ ክልል ብቻ ከ1,000,000 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል። 400,000 የሚሆኑ ተፈናቅለዋል። ”
- “ በተለይ የሸበሌ ዞን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ በዞኑ የሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች ከሞላ ጎደል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ”
- “ በጎርፍ አደጋው ላይ በተደረገው የጋራ ዳሰሳ ፦ 84, 800 አባውራዎች (490, 000 ሰዎች) ተጎድተዋል። ከእነዚህም መካከል 34, 441 የሚሆኑ አባውራዎች (206, 646 ሰዎች) በሸበሌ ዞን በሚገኙ 8 ወረዳዎች ተፈናቅለዋል። ከተጎጂዎች መካከል 49, 430 ሴቶች፣ 30, 427 ህጻናት እና 25, 253 አረጋውያን ናቸው። ”
- “ ከብቶች በጎርፍ አደጋው በጣም ተጎድተዋል፣ እንደሚታወቀው ለበርካታ ተጎጂ ማህበረሰቦች ወሳኝ የገቢ ምንጭ ናቸው። በጎርፉ አደጋው ከ19, 822 በላይ እንስሳት ሞተዋል። መተዳደሪያቸው የነበረ ከ94,000 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰብልም ወድሟል። በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ሙሉና በከፊል ወድመዋል። ”
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-31
@tikvahethiopia