ዒድ ኤክስፖ ትኬትና ሸመታዎን በቴሌብር ያድርጉ!
በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ ተዘጋጀው ዒድ ኤክስፖ ጎራ ካሉ የመግቢያ ትኬቱን በቴሌብር https://onelink.to/fpgu4m ወይም *127# ሲቆርጡና ሲገበያዩ እስከ ብር 2500 ላለው የአየር ሰዓት እና ጥቅል የሚገዙበት 10% ተመላሽ ያገኛሉ።
በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ ተዘጋጀው ዒድ ኤክስፖ ጎራ ካሉ የመግቢያ ትኬቱን በቴሌብር https://onelink.to/fpgu4m ወይም *127# ሲቆርጡና ሲገበያዩ እስከ ብር 2500 ላለው የአየር ሰዓት እና ጥቅል የሚገዙበት 10% ተመላሽ ያገኛሉ።
#ደመወዝ
" ላለፉት ወራት በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ስንፈተን ቆይተናል " ያሉ የዎላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች " ስራችንን በአግባቡ ለመስራት እንችል ዘንድ መንግሥት በአግባቡ ደሞዝ ሊከፍለን ይገባል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸው ከሰጡት የመንግስት ሰራተኞች ውስጥ በተለይም #መምህራን እና #የህክምና_ባለሙያዎች ይገኙበታል።
" ጉዳዩን በተዋረድ ለሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ለወረዳ አመራሮች ካሳወቅን ቆየን " የሚሉት እነዚህ ሰራተኞች " ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ/ም ወደ ክልሉ መንግስት መቀመጫ ወደሆነችዉ ወላይታ ሶዶ ከተማ ብናቀናም ሰሚ አላገኘንም " ብለዋል።
በተለይ ይህ የደሞዝ አለመክፈል እና መቆራረጥ ችግር የተከሰተባቸው በዎላይታ ዞን ስር የሚገኙት የኪንዶ ኮይሻ ፣ የሆብቻ ፣ አባላ ፣ አባያ፣ ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ፑላሳ ፣ ዳሞት ወይዴ ፣ ኪንዶ ዲዳዬ እና አካባቢዉ ወረዳና ቀበሊያት እንደሆኑ ተገልጿል።
በሆብቻ ወረዳ የሚገኘው የሆብቻ ወረዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስራ ካቆመ መሰነባበቱንና ተማሪዎች ቤታቸዉ እየዋሉ መሆኑን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ መምህራን " መንግስት በአፋጣኝ እርምጃ ወስዶ ወደስራችን ይመልሰን " ብለዋል።
ከዚህዉ ጋር ተያይዞ የከልሉን መንግስት ሀሳብ በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወይዘሮ አዜብ ስለጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ዝርዝር ሀሳብ ከመሰንዘር ተቆጥበዋል።
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን እናሳውቃችኃለን።
መረጃዉን አዘጋጅቶ የላከዉ የሀዋሳው ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
" ላለፉት ወራት በደሞዝ መዘግየትና መቆራረጥ ስንፈተን ቆይተናል " ያሉ የዎላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች " ስራችንን በአግባቡ ለመስራት እንችል ዘንድ መንግሥት በአግባቡ ደሞዝ ሊከፍለን ይገባል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸው ከሰጡት የመንግስት ሰራተኞች ውስጥ በተለይም #መምህራን እና #የህክምና_ባለሙያዎች ይገኙበታል።
" ጉዳዩን በተዋረድ ለሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ለወረዳ አመራሮች ካሳወቅን ቆየን " የሚሉት እነዚህ ሰራተኞች " ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ/ም ወደ ክልሉ መንግስት መቀመጫ ወደሆነችዉ ወላይታ ሶዶ ከተማ ብናቀናም ሰሚ አላገኘንም " ብለዋል።
በተለይ ይህ የደሞዝ አለመክፈል እና መቆራረጥ ችግር የተከሰተባቸው በዎላይታ ዞን ስር የሚገኙት የኪንዶ ኮይሻ ፣ የሆብቻ ፣ አባላ ፣ አባያ፣ ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ፑላሳ ፣ ዳሞት ወይዴ ፣ ኪንዶ ዲዳዬ እና አካባቢዉ ወረዳና ቀበሊያት እንደሆኑ ተገልጿል።
በሆብቻ ወረዳ የሚገኘው የሆብቻ ወረዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስራ ካቆመ መሰነባበቱንና ተማሪዎች ቤታቸዉ እየዋሉ መሆኑን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ መምህራን " መንግስት በአፋጣኝ እርምጃ ወስዶ ወደስራችን ይመልሰን " ብለዋል።
ከዚህዉ ጋር ተያይዞ የከልሉን መንግስት ሀሳብ በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወይዘሮ አዜብ ስለጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ዝርዝር ሀሳብ ከመሰንዘር ተቆጥበዋል።
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን እናሳውቃችኃለን።
መረጃዉን አዘጋጅቶ የላከዉ የሀዋሳው ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው " - የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህር ዳር ከተማ የመሀል ሜዳው ተጫዋች አለልኝ አዘነ ለህልፈት መዳረጉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ " አሟሟቱ ድንገተኛና አሰቃቂ መሆኑን ተከትሎ የቅርብ ግንኙነት ያላቸዉን አካላት ይዤ ምርመራ ጀምሪያለሁ " ብሏል።
የወጣቱ ህይዎት ይቀጠፍ ዘንድ ምክኒያት የሆኑ ጉዳዮችን ለማወቅ የስልክ ልውውጦችን ከመመርመር በተጨማሪ በዙሪያው የነበሩ አካላትንም በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ እነማን ተያዙ ? የምርመራዉ አካሄድስ ምን ይመስላል ? ሲል ለአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የለሆኑት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ጥያቄ አቅርቧል።
" የተጫዋቹ መሞት በተሰማበት ወቅት አጠራጣሪ ጉዳዮች ስለነበሩ ፖሊስ የምርመራ እንቅስቃሴ ጀምሯል " ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም " በዚህ ወቅት ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው " ብለዋል።
በሶሻል ሚዲያ እየተዘዋወረ ያለዉን የእናቱ እና ባለቤቱ መያዝ በተመለከተ ላነሳንላቸዉ ጥያቄ " አሁን ላይ ከእህት እና ወንድሙ ዉጭ የተያዘ አካል የለም በማለት ወደፊት ግን ከተያዙት የሚለቀቅ ካልተያዙት ደግሞ የሚያዝ ሊኖር ይችላል " ብለዋል።
" አሁን ላይ ምርመራዉን በፍጥነትና በጥንቃቄ እያካሄድን ነው " ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ውጤቱን ለመላ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማድረስ ማሰባቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህር ዳር ከተማ የመሀል ሜዳው ተጫዋች አለልኝ አዘነ ለህልፈት መዳረጉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ " አሟሟቱ ድንገተኛና አሰቃቂ መሆኑን ተከትሎ የቅርብ ግንኙነት ያላቸዉን አካላት ይዤ ምርመራ ጀምሪያለሁ " ብሏል።
የወጣቱ ህይዎት ይቀጠፍ ዘንድ ምክኒያት የሆኑ ጉዳዮችን ለማወቅ የስልክ ልውውጦችን ከመመርመር በተጨማሪ በዙሪያው የነበሩ አካላትንም በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ እነማን ተያዙ ? የምርመራዉ አካሄድስ ምን ይመስላል ? ሲል ለአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የለሆኑት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ጥያቄ አቅርቧል።
" የተጫዋቹ መሞት በተሰማበት ወቅት አጠራጣሪ ጉዳዮች ስለነበሩ ፖሊስ የምርመራ እንቅስቃሴ ጀምሯል " ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም " በዚህ ወቅት ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው " ብለዋል።
በሶሻል ሚዲያ እየተዘዋወረ ያለዉን የእናቱ እና ባለቤቱ መያዝ በተመለከተ ላነሳንላቸዉ ጥያቄ " አሁን ላይ ከእህት እና ወንድሙ ዉጭ የተያዘ አካል የለም በማለት ወደፊት ግን ከተያዙት የሚለቀቅ ካልተያዙት ደግሞ የሚያዝ ሊኖር ይችላል " ብለዋል።
" አሁን ላይ ምርመራዉን በፍጥነትና በጥንቃቄ እያካሄድን ነው " ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ውጤቱን ለመላ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማድረስ ማሰባቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
“ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን። 2.8 ሚሊዮን ብር ተከፍሎ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ አልተለቀቁም ” - እምባ የሚተናኘቃቸው የታጋች እህት
መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ባቱ (ዝዋይ) እየተጓዙ የነበሩና በ “ ሸኔ ” ታጣቂዎች ታገቱ የተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ሁሉም እንዲለቀቁ 2.8 ሚሊዮን ብር ተዋጥቶ ቢላክም 3ቱ ተለቀው 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ የታጋች ቤተሰብ በእንባ እየተናነቃቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል “ ከአቅሜ በላይ ” ነው እንዳላቸውና በከፋ ጭንቀት ውስጥ እንደሆኑም እንባ አስረትድተዋል።
አንዲት የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ “ ከታጋቾቹ ሥም ዝርዝር የወንድሜም ስም ዝርዝር እንደነበረ ከእገታ የተለቀቁት ነግረውኛል። ብር አምጡ ብለው የመብራት ኃይል ሠራተኞች ሁሉ አዋጥተው 2.8 ሚሉዮን ብር ለ6ቱም ተብሎ ከተላከ በኃላ 3ቱ የኢሬቻ ዕለት ተለቀቁ፣ 3ቱ ግን አልተለቀቁም ” ብለዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል የስራ ኃላፊዎችን ሲጠይቁ “ ከአቅማችን በላይ ነው ” ብለው “ ለፌደራል ፓሊስ አስተላልፈናል ” እንዳሏቸው፣ የፌደራል ፓሊስም አጥጋቢ የሆነ ምላሽ እንዳልሰጣቸው ጠቁመዋል።
በቤተሰብና ወዳጀ ዘመድ በኩል ለታጋቾች ተብሎ 300 ሺህ ብር እንደተላከ፣ ወንድማቸው፣ ሹፌሩ እና አንድ ሌላ ሠራተኛን ጨምሮ ከታገቱ 6 ወራት እንዳስቆጠሩ፣ ቤተሰብም በከፋ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል።
“ ወንድሜ ሁለት ልጆች አሉት ፣ ሚስቱ የስኳር ታማሚ ናት። ሹፌሩም 2 ልጆች አሉት፣ ሚስቱ ሞታለች ” ያሉት የታገቹ እህት፣ “መለቀቅ እንኳ የማይቻል ከሆነና በሕይወት ካለ፣ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን " ሲሉ ተማጽነዋል።
ምንም እንኳን ለማስለቀቂያ 2.8 ሚሊዮን ብር ቢከፈልም ከታገቱት 6 ሰራተኞች ውስጥ 3ቱ ሲለቀቁ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ ያልተለቀቁ ያሉበት ሁኔታ የማይታወቅ ሲሆን አሁን 6 ወራት እንደሞላቸው የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በሀዘን ስሜት ሆነውም መፍትሄ የሚሰጣቸው አካል ካለ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የጠየቅን ሲሆን ምላሹን እናቀርባለን። #TikvahFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን። 2.8 ሚሊዮን ብር ተከፍሎ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ አልተለቀቁም ” - እምባ የሚተናኘቃቸው የታጋች እህት
መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ባቱ (ዝዋይ) እየተጓዙ የነበሩና በ “ ሸኔ ” ታጣቂዎች ታገቱ የተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ሁሉም እንዲለቀቁ 2.8 ሚሊዮን ብር ተዋጥቶ ቢላክም 3ቱ ተለቀው 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ የታጋች ቤተሰብ በእንባ እየተናነቃቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል “ ከአቅሜ በላይ ” ነው እንዳላቸውና በከፋ ጭንቀት ውስጥ እንደሆኑም እንባ አስረትድተዋል።
አንዲት የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ “ ከታጋቾቹ ሥም ዝርዝር የወንድሜም ስም ዝርዝር እንደነበረ ከእገታ የተለቀቁት ነግረውኛል። ብር አምጡ ብለው የመብራት ኃይል ሠራተኞች ሁሉ አዋጥተው 2.8 ሚሉዮን ብር ለ6ቱም ተብሎ ከተላከ በኃላ 3ቱ የኢሬቻ ዕለት ተለቀቁ፣ 3ቱ ግን አልተለቀቁም ” ብለዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል የስራ ኃላፊዎችን ሲጠይቁ “ ከአቅማችን በላይ ነው ” ብለው “ ለፌደራል ፓሊስ አስተላልፈናል ” እንዳሏቸው፣ የፌደራል ፓሊስም አጥጋቢ የሆነ ምላሽ እንዳልሰጣቸው ጠቁመዋል።
በቤተሰብና ወዳጀ ዘመድ በኩል ለታጋቾች ተብሎ 300 ሺህ ብር እንደተላከ፣ ወንድማቸው፣ ሹፌሩ እና አንድ ሌላ ሠራተኛን ጨምሮ ከታገቱ 6 ወራት እንዳስቆጠሩ፣ ቤተሰብም በከፋ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል።
“ ወንድሜ ሁለት ልጆች አሉት ፣ ሚስቱ የስኳር ታማሚ ናት። ሹፌሩም 2 ልጆች አሉት፣ ሚስቱ ሞታለች ” ያሉት የታገቹ እህት፣ “መለቀቅ እንኳ የማይቻል ከሆነና በሕይወት ካለ፣ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን " ሲሉ ተማጽነዋል።
ምንም እንኳን ለማስለቀቂያ 2.8 ሚሊዮን ብር ቢከፈልም ከታገቱት 6 ሰራተኞች ውስጥ 3ቱ ሲለቀቁ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ ያልተለቀቁ ያሉበት ሁኔታ የማይታወቅ ሲሆን አሁን 6 ወራት እንደሞላቸው የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በሀዘን ስሜት ሆነውም መፍትሄ የሚሰጣቸው አካል ካለ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የጠየቅን ሲሆን ምላሹን እናቀርባለን። #TikvahFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ... ሠራተኞቹ የአገር ልማት ሥራ ላይ ሲደክሙ ነው ይሄ ችግር የደረሰባቸው። ግለሰቦቹን በማገት የሚመጣ ለውጥ የለም " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
መስረከም 19/2016 ዓ/ም ለስራ በወጡበት በታጣቂዎች ከታገቱ 6 የኤሌክትሪክ ኃይል ሰራተኞች ሁሉም እንዲለቀቁ 2.8 ሚሊዮን ብር ቢከፈልም 3ቱ ተለቀው የቀሩት 3ቱ እስካሁን ያልተለቀቁ ሲሆን ያሉበት ሁኔታም አይታወቅም።
የታጋች ቤተሰቦች ዛሬም በሀዘን ውስጥ ሆነው የሚወዷቸውን ሰዎች በተስፋ እየተጠባበቁ የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል " እኔ ከአቅሜ በላይ ነው " እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይና አጠቃላይ ስላለው ሁኔታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምን ይላል ? የሚለውን ጠይቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምን ምላሽ ሰጠ ?
Q. በታጋች ቤተሰብ በኩል ተቋማችሁ ይህ ጉዳይ “ ከአቅማችን በላይ ነው ” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ነው የገለጹት እውነት ነው ? ምን ያክል ጥረት አድርጋችኋል ? ከአጋቾቹ በቅርቡ ያገኛችሁት ምላሽስ ምን ነበር ? 3ቱ ታጋቾች ሲለቀቁ 3ቱ የዘገዩበት ምክንያት ምንድን ነው ? ተስፋ አለ ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ያው እኛ ወታደር አናሰማራም ልክ ነው ከአቅም በላይ ነው።
እኛ ልናደርግ የምንችለው አካባቢው ላይ ካሉ የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመነጋገር ሰዎቹ ያለምንም ጉዳት ከቤተሰቦቻቸው መቀላቀል የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲፈጠር መስራት ነው።
ያንን ደግሞ እገታው ከተፈጸመበት ቀን የመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ ያልተቋረጠ ጥረት ሲደረግ ነበር። ይህንንም ደግሞ ቤተሰቦቻቸውም ጭምር ያውቃሉ።
እኛእንደ ተቋም ባለን አቅም በሙሉ ሠራተኞቻችን ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ ጥረት አድርገናል። ይሄ ጥረት አሁንም ቢሆን በሌላ በተሻለ መንገድ ሊፈታ የሚችል ከሆነ ያንን ከመሞከር ወደ ኋላ አንልም። ”
Q. 3ቱ ታጋቾች ለምን ሳይለቀቁ ዘገዩ ተስፋስ አለ ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ይህንን በትክክል ምክንያቱን የሚያውቁት ያገቱት ሰዎች ናቸው። ‘አጣርተን እንለቃቸዋለን’ የሚል ነበር በወቅቱ የተሰጠው ምላሽ እኛም አጣርተው ይለቃሉ የሚል እምነት ይዘን ነበር የቆየነው። ተስፋ አለው የለውም ለማለት ያስቸግራል። ”
Q. ዞሮ ዞሮ አጋቾቹ ታጋቾቹን ለመልቀቅ የጠየቁት ሁሉም ገንዘብ ተሰጥቷቸው ነው ሳይለቋቸው የቀሩት ? ያለዎት መልዕክት ምንድን ነው ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ሠራተኞቻችን ግን ‘ነግ በእኔ’ ብለው ያዋጡ አሉ። እንደ ተቋም ግን ያንን ልናደርግ የምንችልበት ከተያዘ በጀት ውስጥ ገንዘብ ልታወጣ የምትችልበት አሰራር ስሌለ ያንን አላደረግንም።
የጠየቁትን ያክል አልተሰጣቸውም። ሠራተኛው ማወመጣት የሚችለውን ያክል ነው ማዋጣት የሚችለው።
ሠራተኞቹ የአገር ልማት ሥራ ላይ ሲደክሙ ነው ይሄ ችግር የደረሰባቸው። ግለሰቦቹን በማገት የሚመጣ ለውጥ የለም። በተጀመረው መንገድ በሰላም እንዲለቋቸው የሚል ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ”
መረጃው በአ/አ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
መስረከም 19/2016 ዓ/ም ለስራ በወጡበት በታጣቂዎች ከታገቱ 6 የኤሌክትሪክ ኃይል ሰራተኞች ሁሉም እንዲለቀቁ 2.8 ሚሊዮን ብር ቢከፈልም 3ቱ ተለቀው የቀሩት 3ቱ እስካሁን ያልተለቀቁ ሲሆን ያሉበት ሁኔታም አይታወቅም።
የታጋች ቤተሰቦች ዛሬም በሀዘን ውስጥ ሆነው የሚወዷቸውን ሰዎች በተስፋ እየተጠባበቁ የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል " እኔ ከአቅሜ በላይ ነው " እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይና አጠቃላይ ስላለው ሁኔታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምን ይላል ? የሚለውን ጠይቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምን ምላሽ ሰጠ ?
Q. በታጋች ቤተሰብ በኩል ተቋማችሁ ይህ ጉዳይ “ ከአቅማችን በላይ ነው ” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ነው የገለጹት እውነት ነው ? ምን ያክል ጥረት አድርጋችኋል ? ከአጋቾቹ በቅርቡ ያገኛችሁት ምላሽስ ምን ነበር ? 3ቱ ታጋቾች ሲለቀቁ 3ቱ የዘገዩበት ምክንያት ምንድን ነው ? ተስፋ አለ ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ያው እኛ ወታደር አናሰማራም ልክ ነው ከአቅም በላይ ነው።
እኛ ልናደርግ የምንችለው አካባቢው ላይ ካሉ የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመነጋገር ሰዎቹ ያለምንም ጉዳት ከቤተሰቦቻቸው መቀላቀል የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲፈጠር መስራት ነው።
ያንን ደግሞ እገታው ከተፈጸመበት ቀን የመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ ያልተቋረጠ ጥረት ሲደረግ ነበር። ይህንንም ደግሞ ቤተሰቦቻቸውም ጭምር ያውቃሉ።
እኛእንደ ተቋም ባለን አቅም በሙሉ ሠራተኞቻችን ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ ጥረት አድርገናል። ይሄ ጥረት አሁንም ቢሆን በሌላ በተሻለ መንገድ ሊፈታ የሚችል ከሆነ ያንን ከመሞከር ወደ ኋላ አንልም። ”
Q. 3ቱ ታጋቾች ለምን ሳይለቀቁ ዘገዩ ተስፋስ አለ ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ይህንን በትክክል ምክንያቱን የሚያውቁት ያገቱት ሰዎች ናቸው። ‘አጣርተን እንለቃቸዋለን’ የሚል ነበር በወቅቱ የተሰጠው ምላሽ እኛም አጣርተው ይለቃሉ የሚል እምነት ይዘን ነበር የቆየነው። ተስፋ አለው የለውም ለማለት ያስቸግራል። ”
Q. ዞሮ ዞሮ አጋቾቹ ታጋቾቹን ለመልቀቅ የጠየቁት ሁሉም ገንዘብ ተሰጥቷቸው ነው ሳይለቋቸው የቀሩት ? ያለዎት መልዕክት ምንድን ነው ?
የተቋሙ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፦
“ ሠራተኞቻችን ግን ‘ነግ በእኔ’ ብለው ያዋጡ አሉ። እንደ ተቋም ግን ያንን ልናደርግ የምንችልበት ከተያዘ በጀት ውስጥ ገንዘብ ልታወጣ የምትችልበት አሰራር ስሌለ ያንን አላደረግንም።
የጠየቁትን ያክል አልተሰጣቸውም። ሠራተኛው ማወመጣት የሚችለውን ያክል ነው ማዋጣት የሚችለው።
ሠራተኞቹ የአገር ልማት ሥራ ላይ ሲደክሙ ነው ይሄ ችግር የደረሰባቸው። ግለሰቦቹን በማገት የሚመጣ ለውጥ የለም። በተጀመረው መንገድ በሰላም እንዲለቋቸው የሚል ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ”
መረጃው በአ/አ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
#GlobalBankEthiopia
ማንችስተር ሲቲ ወይስ አርሰናል
በመገመት የሚያሸልም ጥያቄ በኢንስታግራም ገጻችን (https://bit.ly/3NiRHOn ) ብቻ ግምትዎን ይስጡ!
በፕሪሚየር ሊጉ በጉጉት ከሚጠበቁት ጨዋታዎች መካከል አንዱ የፊታችን እሁድ መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም በማንችስተር ሲቲ እና በአርሰናል መካከል ይካሄዳል፡፡ ጨዋታውን በትክክል ለሚገምቱ 3 የኢንስታግራም (https://bit.ly/3NiRHOn) ተከታዮቻችን ለእያንዳንዳቸው የ300 ብር የካርድ ሽልማት አዘጋጅተናል፡፡
1. የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የኢንስታግራም ገጽን https://bit.ly/3NiRHOn ገፅ መከተልዎን አይዘንጉ!
2. ትክክለኛ መላሾች ከ 3 በላይ ከሆኑ አሸናፊዎቹን የምንለየው በዕጣ ይሆናል፡፡
መልካም ዕድል!!
ግሎባል ባንክ
ማንችስተር ሲቲ ወይስ አርሰናል
በመገመት የሚያሸልም ጥያቄ በኢንስታግራም ገጻችን (https://bit.ly/3NiRHOn ) ብቻ ግምትዎን ይስጡ!
በፕሪሚየር ሊጉ በጉጉት ከሚጠበቁት ጨዋታዎች መካከል አንዱ የፊታችን እሁድ መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም በማንችስተር ሲቲ እና በአርሰናል መካከል ይካሄዳል፡፡ ጨዋታውን በትክክል ለሚገምቱ 3 የኢንስታግራም (https://bit.ly/3NiRHOn) ተከታዮቻችን ለእያንዳንዳቸው የ300 ብር የካርድ ሽልማት አዘጋጅተናል፡፡
1. የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የኢንስታግራም ገጽን https://bit.ly/3NiRHOn ገፅ መከተልዎን አይዘንጉ!
2. ትክክለኛ መላሾች ከ 3 በላይ ከሆኑ አሸናፊዎቹን የምንለየው በዕጣ ይሆናል፡፡
መልካም ዕድል!!
ግሎባል ባንክ
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትክክለኛ ፍትህ እንሻለን " - የቀድሞው የሀዋሳ ከንቲባ ቤተሰቦች
ላለፉት 5 ወራት በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ ቤተሰቦች ፥ " በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
የቀድሞው ከተንቲባ ወንድም እንደሆኑ የገለጹት አቶ አስፋዉ ቱኬ ፤ " ወንድሜ በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ያሉ ሲሆን " በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ምን ያክል ህዝባዊ አመራር እንደነበርና ከሙስና የጸዳ ሰው እንደሆነ ሙሉ የሲዳማም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቃል " ብለዋል።
" በዚህ ንጽህናዉ ስለሚተማመንም ነበር ከሀገር ከወጣ በኋላ ወደሀገር ተመልሶ ለእስር የተዳረገው " ሲሉ አክለዋል።
አቶ አስፋው ፥ " ላለፉት አምስት (5) ወራት ፍትህ ተስተጓጉሎበትና የህክምና አገልግሎት አጥቶ ከፍርድ ቤት ፍርድ ቤት እየተመላለሰ ነው " ያሉ ሲሆን " አሁን ላይ የቀረበበት ክስም እሱ ከሀገር በወጣበት ወቅት በተወሰደዉ የመንግስት ቤት ውስጥ በነበሩና ጠፉ በተባሉ ተራ የምንጣፍና የመጋረጃና መሰል የቤት እቃዎች ተጠያቂ መሆኑ እሱን በእስር ለማቆየት ብቻ የታሰበ ይመስላል " ብለዋል።
" ከመምህርነት አንስቶ ሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ባገለገለበት ወቅት ያሳያቸዉ ቀና የህዝብ ፍቅር የልማት ወጤቶችና የመልካም አስተዳደር ፍሬዎች እንዲሁም በከተሞች መድረክ ያሳየዉ ከፍተኛ ውጤት በሲዳማም ሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የሚያስመሰግኑትና የሚያሸልሙት እንጅ የሚያሳስሩት አልነበሩም " ብለዋል።
አቶ አስፋው ቱኬ ፥ ወንድማቸው በጤና ችግር እየተሰቃዩ እንደሆነ በመግለጽ ቤተሰቡ ትክክለኛ ፍትህ እንደሚሻ ፤ የሚመለከተው አካል ሁሉ ይሄን ተማጽኗቸው እንዲሠማ ጥሪ አቅርበዋል።
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ፥ በስልጣን ጊዜያቸው በሙስና ወንጀል እንዲሁም በከተማው ውስጥ ብልሹ አሰራር እንዲንሰራፋ አድርገዋል በሚል ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገው መታሰራቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
ላለፉት 5 ወራት በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ ቤተሰቦች ፥ " በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
የቀድሞው ከተንቲባ ወንድም እንደሆኑ የገለጹት አቶ አስፋዉ ቱኬ ፤ " ወንድሜ በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ያሉ ሲሆን " በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ምን ያክል ህዝባዊ አመራር እንደነበርና ከሙስና የጸዳ ሰው እንደሆነ ሙሉ የሲዳማም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቃል " ብለዋል።
" በዚህ ንጽህናዉ ስለሚተማመንም ነበር ከሀገር ከወጣ በኋላ ወደሀገር ተመልሶ ለእስር የተዳረገው " ሲሉ አክለዋል።
አቶ አስፋው ፥ " ላለፉት አምስት (5) ወራት ፍትህ ተስተጓጉሎበትና የህክምና አገልግሎት አጥቶ ከፍርድ ቤት ፍርድ ቤት እየተመላለሰ ነው " ያሉ ሲሆን " አሁን ላይ የቀረበበት ክስም እሱ ከሀገር በወጣበት ወቅት በተወሰደዉ የመንግስት ቤት ውስጥ በነበሩና ጠፉ በተባሉ ተራ የምንጣፍና የመጋረጃና መሰል የቤት እቃዎች ተጠያቂ መሆኑ እሱን በእስር ለማቆየት ብቻ የታሰበ ይመስላል " ብለዋል።
" ከመምህርነት አንስቶ ሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ባገለገለበት ወቅት ያሳያቸዉ ቀና የህዝብ ፍቅር የልማት ወጤቶችና የመልካም አስተዳደር ፍሬዎች እንዲሁም በከተሞች መድረክ ያሳየዉ ከፍተኛ ውጤት በሲዳማም ሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የሚያስመሰግኑትና የሚያሸልሙት እንጅ የሚያሳስሩት አልነበሩም " ብለዋል።
አቶ አስፋው ቱኬ ፥ ወንድማቸው በጤና ችግር እየተሰቃዩ እንደሆነ በመግለጽ ቤተሰቡ ትክክለኛ ፍትህ እንደሚሻ ፤ የሚመለከተው አካል ሁሉ ይሄን ተማጽኗቸው እንዲሠማ ጥሪ አቅርበዋል።
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ፥ በስልጣን ጊዜያቸው በሙስና ወንጀል እንዲሁም በከተማው ውስጥ ብልሹ አሰራር እንዲንሰራፋ አድርገዋል በሚል ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገው መታሰራቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
#ጋምቤላ
በጋምቤላ ክልል በተለያዩ ቦታዎች ላይ በየጊዜው እየተፈፀሙ ያሉት #ጎራን_የሚለዩ ግድያዎች ፣ ጥቃቶች አሁን ካለው የከፋ ነገር ይዘው እንደይመጡ ፦
➡️ ሳይረፍድ መፍትሄ እንዲሰጣቸው
➡️ ወንጀለኞችም ለፍርድ እንዲቀርቡ
➡️ ለተበዳይ ወገኖችም ፍትህ መስጠት እንደሚገባ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች አሳስበዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ የክልሉ ነዋሪ ፥ " በየጊዜው እየተፈፀሙ ያሉት ግድያዎች የከፋ መዘዝ ይዘው ሊመጡ የሚችሉ ናቸው ስለዚህ ጠንካራ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።
ከግድያ ባለፈም የሚፈፀሙ የወንጀል ተግባራት ደህንነትን የሚነሱ ናቸው ሲሉ አክለዋል።
ነገ እርስ በእርስ ሰዎች እንዳይጠፋፉ አሁን ያለው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይደረስ መድረግ አለበት ብለዋል።
ሌላኛው ቃላቸው የሰጡ ነዋሪ ፥ በዚህ ወር ብቻ ሰዎች በተለያዩ ስፍራዎች ተገድለዋል ብለዋል።
በጋምቤላ አንድ የትራፊክ አባል " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች በጥይት ከተመታ በኃላ ችግሮች እየተባባሱ ሄደው በፍራቻ ምክንያት በከተማው እንቅስቃሴ እስከመስተጓጎል ደርሶ እንደነበር ገልጸዋል።
በአቦቦ ወረዳ ደግሞ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ቢያስን 3 ሰዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀድምም እዚሁ ወረዳ ግድያ ተፈፅሞ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከቀናት በፊት ከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን ባለው መስመር ህዝብ ጭኖ የነበረ ተሽከርካሪ ላይ በተፈፀመ ጥቃት 5 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
በኢታንግ ልዩ ወረዳም ግጭቶች እንደነበሩ ጠቁመዋል።
" እየተፈፀሙት ላሉ ግድያዎች፣ ዘረፋዎች ተጠያቂነት ሲረጋገጥ እያየን አይደለም " ብለው ችግሩ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።
ሌላው መልዕክታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ የክልሉ ነዋሪ ፥ " በቀን 18/7/2016 ከተርፋም ወደ ጋምቤላ መስመእ የህዝብ ማመላለሻ መኪናን ታጣቂዎች መትተውት እስካሁን የሰው ህይወት አልፏል ፣ የተጎዱም ሆስፒታል ገብተዋል " ብለዋል።
እኚሁ ነዋሪ ጥቃቱ የተፈፀመ ከተርፋም ወደ አቦል ሲቃረብ ቢያንስ 7 ኪ/ሜ እንደሆነ አስረድተዋል።
አቦል የምትባለው ወረዳ ላይ ዝርፊያና ግድያ በተደጋጋሚ እንደሚፈፀም ጠቁመዋል።
ነዋሪው ፥ ባለፈው ሳምንት አንድ የትራፊክ ፖሊስ መሀል አደባባይ ላይ በባጃጅ በመጡ ሰዎች በጥይት ከተመታ በኃላ ነገሮች መባባሳቸውን ጠቁመዋል።
ሌላው በክልሉ ያለው ችግር የሚያጠፉ ሰዎች በህግ አለመጠየቃቸው ነው ያሉት ነዋሪው " የህግ የበላይነት የሚባለው ነገር ጠፍቶል " ሲሉ ያለውን አሳሳቢ ሁኔታ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ጋምቤላ ክልል ያለው ሁኔታ ቸል የሚባል ስላልሆነ የፌዴራሉም መንግሥት ትኩረት እንዲሰጥበት አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ፥ ጋምቤላ ክልል እየተከሰተ ያለውን የፀጥታ ችግር ለመቅረፍ የፌደራል እና የክልሉ የፀጥታ አካላት ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኡሞድ ኡጁሉ በተገኙበት ነው የፌዴራል እና የክልል ፀጥታ አመራሮች ውይይት የተካሄደው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሸነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ፥ አንዳንድ ግለሰቦች ጎራ እየለዩ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ግድያ፣ ማፈናቀልና የተለያዩ ጉዳቶችን እያደረሱ እንዳሉ መገምገሙን ተናግረዋል።
ችግር ፈጣሪዎችም በአስቸኳይ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ መግባባት ላይ መደረሱን ገልፀዋል።
የፌደራል ፖሊስ ፣ የመከላከያ ሠራዊት እና የክልሉ የፀጥታ አካላት የፀጥታ ችግሩን ለመቅረፍ ወደ #ኦፕሬሽን_ገብተው ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በቁጥጥር ሥር እያዋሉ ይገኛሉ ብለዋል።
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል በተለያዩ ቦታዎች ላይ በየጊዜው እየተፈፀሙ ያሉት #ጎራን_የሚለዩ ግድያዎች ፣ ጥቃቶች አሁን ካለው የከፋ ነገር ይዘው እንደይመጡ ፦
➡️ ሳይረፍድ መፍትሄ እንዲሰጣቸው
➡️ ወንጀለኞችም ለፍርድ እንዲቀርቡ
➡️ ለተበዳይ ወገኖችም ፍትህ መስጠት እንደሚገባ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች አሳስበዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ የክልሉ ነዋሪ ፥ " በየጊዜው እየተፈፀሙ ያሉት ግድያዎች የከፋ መዘዝ ይዘው ሊመጡ የሚችሉ ናቸው ስለዚህ ጠንካራ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።
ከግድያ ባለፈም የሚፈፀሙ የወንጀል ተግባራት ደህንነትን የሚነሱ ናቸው ሲሉ አክለዋል።
ነገ እርስ በእርስ ሰዎች እንዳይጠፋፉ አሁን ያለው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይደረስ መድረግ አለበት ብለዋል።
ሌላኛው ቃላቸው የሰጡ ነዋሪ ፥ በዚህ ወር ብቻ ሰዎች በተለያዩ ስፍራዎች ተገድለዋል ብለዋል።
በጋምቤላ አንድ የትራፊክ አባል " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ሰዎች በጥይት ከተመታ በኃላ ችግሮች እየተባባሱ ሄደው በፍራቻ ምክንያት በከተማው እንቅስቃሴ እስከመስተጓጎል ደርሶ እንደነበር ገልጸዋል።
በአቦቦ ወረዳ ደግሞ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ቢያስን 3 ሰዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀድምም እዚሁ ወረዳ ግድያ ተፈፅሞ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከቀናት በፊት ከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን ባለው መስመር ህዝብ ጭኖ የነበረ ተሽከርካሪ ላይ በተፈፀመ ጥቃት 5 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
በኢታንግ ልዩ ወረዳም ግጭቶች እንደነበሩ ጠቁመዋል።
" እየተፈፀሙት ላሉ ግድያዎች፣ ዘረፋዎች ተጠያቂነት ሲረጋገጥ እያየን አይደለም " ብለው ችግሩ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።
ሌላው መልዕክታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ የክልሉ ነዋሪ ፥ " በቀን 18/7/2016 ከተርፋም ወደ ጋምቤላ መስመእ የህዝብ ማመላለሻ መኪናን ታጣቂዎች መትተውት እስካሁን የሰው ህይወት አልፏል ፣ የተጎዱም ሆስፒታል ገብተዋል " ብለዋል።
እኚሁ ነዋሪ ጥቃቱ የተፈፀመ ከተርፋም ወደ አቦል ሲቃረብ ቢያንስ 7 ኪ/ሜ እንደሆነ አስረድተዋል።
አቦል የምትባለው ወረዳ ላይ ዝርፊያና ግድያ በተደጋጋሚ እንደሚፈፀም ጠቁመዋል።
ነዋሪው ፥ ባለፈው ሳምንት አንድ የትራፊክ ፖሊስ መሀል አደባባይ ላይ በባጃጅ በመጡ ሰዎች በጥይት ከተመታ በኃላ ነገሮች መባባሳቸውን ጠቁመዋል።
ሌላው በክልሉ ያለው ችግር የሚያጠፉ ሰዎች በህግ አለመጠየቃቸው ነው ያሉት ነዋሪው " የህግ የበላይነት የሚባለው ነገር ጠፍቶል " ሲሉ ያለውን አሳሳቢ ሁኔታ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ጋምቤላ ክልል ያለው ሁኔታ ቸል የሚባል ስላልሆነ የፌዴራሉም መንግሥት ትኩረት እንዲሰጥበት አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ፥ ጋምቤላ ክልል እየተከሰተ ያለውን የፀጥታ ችግር ለመቅረፍ የፌደራል እና የክልሉ የፀጥታ አካላት ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኡሞድ ኡጁሉ በተገኙበት ነው የፌዴራል እና የክልል ፀጥታ አመራሮች ውይይት የተካሄደው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሸነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ፥ አንዳንድ ግለሰቦች ጎራ እየለዩ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ግድያ፣ ማፈናቀልና የተለያዩ ጉዳቶችን እያደረሱ እንዳሉ መገምገሙን ተናግረዋል።
ችግር ፈጣሪዎችም በአስቸኳይ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ መግባባት ላይ መደረሱን ገልፀዋል።
የፌደራል ፖሊስ ፣ የመከላከያ ሠራዊት እና የክልሉ የፀጥታ አካላት የፀጥታ ችግሩን ለመቅረፍ ወደ #ኦፕሬሽን_ገብተው ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በቁጥጥር ሥር እያዋሉ ይገኛሉ ብለዋል።
@tikvahethiopia