" ወደ ሀገሬ ድርሽ እንዳትሉ "
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ እና ሌሎች የካቢኔ አባላት ወደ ሩሲያ ምድር ድርሽ እንዳይሉ እገዳ እንደተጣለባቸው ዛሬ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ እና ሌሎች የካቢኔ አባላት ወደ ሩሲያ ምድር ድርሽ እንዳይሉ እገዳ እንደተጣለባቸው ዛሬ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ደቡብ ኦሞ ዞን " ከሰሞኑን በደቡብ ኦሞ ዞን በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ከቤታቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችን ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። ተፈናቃይ ወገኖቻችን ተፈናቅለው ከተጠለሉበት አንዱ ሜፀር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን በአሁን ወቅት አስቸጋሪ ኑሮ እየመሩ እንደሆነ ገልፀዋል ፤ መንግስት ፈጥኖ መልሶ እንዲያቋቁማቸው እና የዕለት ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። ትላንት የደቡብ ኦሞ ዞን…
" ትክክለኛ ፍትህ እንፈልጋለን "
ህይወታቸውን ሙሉ ደክመው ያፈሩት ንብረታቸው በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ዶግ አመድ ሆኖባቸው የሰው እጅ ለማየት የተገደዱ ወገኖቻችን " ፍትህ እንፈልጋለን " እያሉ ነው።
ሰሞኑን በደቡብ ክልል፤ ደቡብ ኦሞ ዞን ፤ ደቡብ አሪ ወረዳ ከዞን የመዋቅር ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተነሳው የፀጥታ ችግር በርካቶች ንብረታቸው ወድሞ ከገዛ ቤታቸው ተፈናቅለው በየትምህርት ቤቱ እና መንግስት ተቋማት ውስጥ መጠለላቸው ይታወቃል።
ለዘመናት ደክመው ያፈሩት ሀብትና ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሞባቸው በየመጠለያው የሚገኙት ወገኖቻችን መንግስት ጉዳዩን አጣርቶ ትክክለኛ ፍትህ እንዲሰጣቸው ጥይቀዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለተፈናቃዮች የተለያዩ አካላት ድጋፋቸው ማድረግ የቀጠሉ ሲሆን ከደቡብ ኦሞ ዞን ኮሚኒኬሽን ባገኘነው መረጃ ፤ ባለፉት ቀናት ቀይ መስቀል፣ የዞን ሴቶች መምሪያ፣ የዳሰነች ወረዳ ፣ የቱርሚ ከተማ ድጋፍ ካደረጉት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
@tikvahethiopia
ህይወታቸውን ሙሉ ደክመው ያፈሩት ንብረታቸው በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ዶግ አመድ ሆኖባቸው የሰው እጅ ለማየት የተገደዱ ወገኖቻችን " ፍትህ እንፈልጋለን " እያሉ ነው።
ሰሞኑን በደቡብ ክልል፤ ደቡብ ኦሞ ዞን ፤ ደቡብ አሪ ወረዳ ከዞን የመዋቅር ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተነሳው የፀጥታ ችግር በርካቶች ንብረታቸው ወድሞ ከገዛ ቤታቸው ተፈናቅለው በየትምህርት ቤቱ እና መንግስት ተቋማት ውስጥ መጠለላቸው ይታወቃል።
ለዘመናት ደክመው ያፈሩት ሀብትና ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሞባቸው በየመጠለያው የሚገኙት ወገኖቻችን መንግስት ጉዳዩን አጣርቶ ትክክለኛ ፍትህ እንዲሰጣቸው ጥይቀዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለተፈናቃዮች የተለያዩ አካላት ድጋፋቸው ማድረግ የቀጠሉ ሲሆን ከደቡብ ኦሞ ዞን ኮሚኒኬሽን ባገኘነው መረጃ ፤ ባለፉት ቀናት ቀይ መስቀል፣ የዞን ሴቶች መምሪያ፣ የዳሰነች ወረዳ ፣ የቱርሚ ከተማ ድጋፍ ካደረጉት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
@tikvahethiopia
የቀድሞው ጉምቱ ባለስልጣን ፤ አሁን ላይ በባህር ዳር ከተማ ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙት አቶ በረከት ስምኦን የረሃብ አድማ መምታታቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።
ትላንት ጀመሩት የተባለው ይህ የረሃብ አድማቸው መነሻው ለወራት ወደ አዲስ አበባ ለመዘዋወር ለማረሚያ ቤቱ ሲያቀርቡት የቆየ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ነው ተብሏል።
የአማራ ክልል የማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ግን አቶ በረከት የረሃብ አድማ ስለማድረጋቸው የማውቀው መረጃ የለም ብሏል።
አቶ በረከት መልካም በሆነ ጤንነት ላይ እንዳሉ እንጂ ረሃብ አድማ ስለማድረጋቸው አላቅም ያለው ኮሚሽኑ ጉዳዩን አጣርቼ አሳውቋለሁ ብሏል።
አቶ በረከት ከተፈረደባቸው የስድስት ዓመት እስር ውስጥ አንድ ሶስተኛውን አገባደው #በአመክሮ ከእስር ለመውጣት ጥያቄ አቅርበው ነበር።
አቶ በረከት ትላንት ጀምሮ መቱት የተባለውን የረሃብ አድማ በተመለከተ ባለቤታቸው ወ/ሮ አሲ ፈንቴ መረጃው እንዳላቸው ገልፀዋል።
ወ/ሮ ኢሲ ከአቶ በረከት ጋር አብረዋቸው ታስረው የቆዩት አቶ ታደሰ ካሳ በከፍተኛ ህመም ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ከመጡ 5 ወራት መቆጠራቸውን እና አቶ በረከት አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻቸው ታሰረው መቆየታቸው አንዱ ለረሃብ አድማው ምክንያት መሆኑ ገልፀዋል።
የረሃብ አድማው ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸውም ተናግረዋል።
ወ/ሮ አሲ ባለቤታቸው የልብ ህመም እንዳለባቸው እና በረሃቡ ምክንያት የከፋ አደጋ እንዳይደርስ ቤተሰባቸው ስጋት ውስጥ መውደቁን ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-04-16-2
@tikvahethiopia
ትላንት ጀመሩት የተባለው ይህ የረሃብ አድማቸው መነሻው ለወራት ወደ አዲስ አበባ ለመዘዋወር ለማረሚያ ቤቱ ሲያቀርቡት የቆየ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ነው ተብሏል።
የአማራ ክልል የማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ግን አቶ በረከት የረሃብ አድማ ስለማድረጋቸው የማውቀው መረጃ የለም ብሏል።
አቶ በረከት መልካም በሆነ ጤንነት ላይ እንዳሉ እንጂ ረሃብ አድማ ስለማድረጋቸው አላቅም ያለው ኮሚሽኑ ጉዳዩን አጣርቼ አሳውቋለሁ ብሏል።
አቶ በረከት ከተፈረደባቸው የስድስት ዓመት እስር ውስጥ አንድ ሶስተኛውን አገባደው #በአመክሮ ከእስር ለመውጣት ጥያቄ አቅርበው ነበር።
አቶ በረከት ትላንት ጀምሮ መቱት የተባለውን የረሃብ አድማ በተመለከተ ባለቤታቸው ወ/ሮ አሲ ፈንቴ መረጃው እንዳላቸው ገልፀዋል።
ወ/ሮ ኢሲ ከአቶ በረከት ጋር አብረዋቸው ታስረው የቆዩት አቶ ታደሰ ካሳ በከፍተኛ ህመም ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ከመጡ 5 ወራት መቆጠራቸውን እና አቶ በረከት አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻቸው ታሰረው መቆየታቸው አንዱ ለረሃብ አድማው ምክንያት መሆኑ ገልፀዋል።
የረሃብ አድማው ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸውም ተናግረዋል።
ወ/ሮ አሲ ባለቤታቸው የልብ ህመም እንዳለባቸው እና በረሃቡ ምክንያት የከፋ አደጋ እንዳይደርስ ቤተሰባቸው ስጋት ውስጥ መውደቁን ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-04-16-2
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Tigray, #Mekelle 📍 ትላንትና በጉዞ ላይ እንደነበሩ የተነገረላቸው አስፈላጊ የሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችን የጫኑት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተሸከርካሪዎች የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ደርሰዋል። ሁሉም (50ውም) ተሸከርካሪዎች በሰላም ነው መቐለ የደረሱት። ምን ይዘዋል ? ➡️ 1,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴ እና ጥራጥሬ ፤ ➡️ 700 ሜትሪክ ቶን የጤና ፣ የተመጣጠነ ምግብ…
#WFP #USA #Ethiopia #TigrayRegion
የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ ክልል #ተጨማሪ ኮንቮይዎችን ለመላክ ዝግጁ መሆኑና ፍቃድም እንዳለው ገልጿል።
ቀጣዩ የሰብዓዊ እርደታ ኮንቮይ በተቻለ ፍጥነት በሰላም እንዲሄድ በአፋር ክልል ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
በሌላ በኩል ፥ አሜሪካ ትላንት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ፤ ከ1,700 ሜትሪክ ቶን በላይ ነፍስ አድን ሰብአዊ እርዳታ ትግራይ መግባቱ መልካም ዜና ነው ብላለች።
የእርዳታው እንዲደስ ትብብር ያደረጉትን የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች እና የአፋር ክልል አስተዳዳሪዎችን እንደምታደንቅም ገልፃለች።
በተጨማሪም ፤ አሜሪካ የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ክልል ኤሬብቲ መውጣታቸውን እንደምትደግፍ ገልፃ ከሌሎችም የአፋር አካባቢዎች የትግራይ ኃይሎች ቢወጡ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብላለች።
አሜሪካ በትላንት መግለጫዋ የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ባለስልጣናት አሁን በታየው ለውጥ ቀጥለው ግጭቱን በድርድር፣ በዘላቂነት መፍታት የሚችሉበት መንገድ ማግኘት አለባቸው ብላለች።
ይህ እንዲሆንም በትግራይ ክልል መሠረታዊ አገልግሎቶች መመለስ እንዳለባቸው እና አካታች ፖለቲካዊ አካሄድ መተግበር እንዳለበት ገልጻለች።
የአሜሪካ መግለጫ : https://www.state.gov/delivery-of-humanitarian-assistance-in-tigray/
@tikvahethiopia
የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ ክልል #ተጨማሪ ኮንቮይዎችን ለመላክ ዝግጁ መሆኑና ፍቃድም እንዳለው ገልጿል።
ቀጣዩ የሰብዓዊ እርደታ ኮንቮይ በተቻለ ፍጥነት በሰላም እንዲሄድ በአፋር ክልል ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
በሌላ በኩል ፥ አሜሪካ ትላንት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ፤ ከ1,700 ሜትሪክ ቶን በላይ ነፍስ አድን ሰብአዊ እርዳታ ትግራይ መግባቱ መልካም ዜና ነው ብላለች።
የእርዳታው እንዲደስ ትብብር ያደረጉትን የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች እና የአፋር ክልል አስተዳዳሪዎችን እንደምታደንቅም ገልፃለች።
በተጨማሪም ፤ አሜሪካ የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ክልል ኤሬብቲ መውጣታቸውን እንደምትደግፍ ገልፃ ከሌሎችም የአፋር አካባቢዎች የትግራይ ኃይሎች ቢወጡ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብላለች።
አሜሪካ በትላንት መግለጫዋ የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ባለስልጣናት አሁን በታየው ለውጥ ቀጥለው ግጭቱን በድርድር፣ በዘላቂነት መፍታት የሚችሉበት መንገድ ማግኘት አለባቸው ብላለች።
ይህ እንዲሆንም በትግራይ ክልል መሠረታዊ አገልግሎቶች መመለስ እንዳለባቸው እና አካታች ፖለቲካዊ አካሄድ መተግበር እንዳለበት ገልጻለች።
የአሜሪካ መግለጫ : https://www.state.gov/delivery-of-humanitarian-assistance-in-tigray/
@tikvahethiopia
"ደህንነት ያለበት፣ ሰላማዊ የሆነ፣ የሚያስተማምን ቦታ የመጣን መስሎኝ ነበር ግን ልጄ በጥይት ተመቶ መገደሉ ከማስበው በላይ ሆኖብኛል" - ወላጅ እናት
በፖሊስ እና መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች በተደጋጋሚ ሰው በሚገደልባት ሀገረ #አሜሪካ ከሰሞኑን በርካቶችን ያስቆጣ ግድያ በፖሊስ ተፈፅሞ ነበር።
ግድያው በሚቺጋን ግዛት የተፈፀመ ሲሆን በነጭ ፖሊስ የተገደለው የ26 ዓመቱ ወጣት የኮንጎ ስደተኛ ፓትሪክ ልዮያ ነው።
ፖሊስ፤ ወጣቱ ስደተኛ የሚነዳው መኪና ታርጋው ከመኪናው አይነት ጋር ባለመገናኘቱ ትራፊክ እንዳስቆመው ገልጿል፤ በኃላም በነጭ ፖሊስ ተተኩሶ ተገድሏል።
የፓትሪክ ወላጅ አባት ፒተር ልዮያ ሁኔታው እጅጉን እንዳሳዘናቸው ገልፀው ፤ " እዚህ አሜሪካ ውስጥ ሰው ባለበት የሚገደልበት አይነት ግድያ እንዳለ ፤ጥይት በያዘ ሰው እና በፖሊስ ሰው እንደሚገደል አላውቅም ነበር ፤ እኔ የማውቀው አሜሪካ ውስጥ ፖሊስ ስታገኝ ደህንነት እንደሚሰማህ ነበር " ብለዋል።
ወላጅ እናት ዶርካስ ልዮያ በመሪር ሀዘን ውስጥ ሆነው ፤ " ኮንጎን ጥለን የወጣነው የምንኖርበት አካባቢ ደህንነቱ አስተማማኝ ስላልነበረ ነው። ጦርነት ነበር ስለዚህ ደህንነት ያለበት ሰላማዊ የሆነ የሚያስተማምን ቦታ የመጣን መስሎኝ ነበር ግን ልጄ በጥይት ተመቶ መገደሉ ከማስበው በላይ ሆኖብኛል " ብለዋል።
ወጣቱን የኮንጎ ስደተኛ የገደለው ስሙና ማንነቱ ይፋ ያልተደረገው ፖሊስ ደሞዝ እየተከፈለው እረፍት እንዲወስድ ተደርጓል።
የሚቺጋን ፖሊስ ሁኔታውን "እያጣራ" ነው የተባለ ሲሆን የፓትሪክን ቤተሰቦች የወከለ ጠበቃ ፖሊሱ ላይ ክስ እንዲመሰረትና ህግ ፊት እንዲቀርብ እንደሚፈልግ ማሳወቁን ቪኦኤ ሬድዮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በፖሊስ እና መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች በተደጋጋሚ ሰው በሚገደልባት ሀገረ #አሜሪካ ከሰሞኑን በርካቶችን ያስቆጣ ግድያ በፖሊስ ተፈፅሞ ነበር።
ግድያው በሚቺጋን ግዛት የተፈፀመ ሲሆን በነጭ ፖሊስ የተገደለው የ26 ዓመቱ ወጣት የኮንጎ ስደተኛ ፓትሪክ ልዮያ ነው።
ፖሊስ፤ ወጣቱ ስደተኛ የሚነዳው መኪና ታርጋው ከመኪናው አይነት ጋር ባለመገናኘቱ ትራፊክ እንዳስቆመው ገልጿል፤ በኃላም በነጭ ፖሊስ ተተኩሶ ተገድሏል።
የፓትሪክ ወላጅ አባት ፒተር ልዮያ ሁኔታው እጅጉን እንዳሳዘናቸው ገልፀው ፤ " እዚህ አሜሪካ ውስጥ ሰው ባለበት የሚገደልበት አይነት ግድያ እንዳለ ፤ጥይት በያዘ ሰው እና በፖሊስ ሰው እንደሚገደል አላውቅም ነበር ፤ እኔ የማውቀው አሜሪካ ውስጥ ፖሊስ ስታገኝ ደህንነት እንደሚሰማህ ነበር " ብለዋል።
ወላጅ እናት ዶርካስ ልዮያ በመሪር ሀዘን ውስጥ ሆነው ፤ " ኮንጎን ጥለን የወጣነው የምንኖርበት አካባቢ ደህንነቱ አስተማማኝ ስላልነበረ ነው። ጦርነት ነበር ስለዚህ ደህንነት ያለበት ሰላማዊ የሆነ የሚያስተማምን ቦታ የመጣን መስሎኝ ነበር ግን ልጄ በጥይት ተመቶ መገደሉ ከማስበው በላይ ሆኖብኛል " ብለዋል።
ወጣቱን የኮንጎ ስደተኛ የገደለው ስሙና ማንነቱ ይፋ ያልተደረገው ፖሊስ ደሞዝ እየተከፈለው እረፍት እንዲወስድ ተደርጓል።
የሚቺጋን ፖሊስ ሁኔታውን "እያጣራ" ነው የተባለ ሲሆን የፓትሪክን ቤተሰቦች የወከለ ጠበቃ ፖሊሱ ላይ ክስ እንዲመሰረትና ህግ ፊት እንዲቀርብ እንደሚፈልግ ማሳወቁን ቪኦኤ ሬድዮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Telegram
ቴሌግራም አጫጭር የድምፅ ፋይሎችን እና የድምፅ መልዕክቶችን ለማንኛውም ቻት/መልዕክት ልውውጥ ወደ ማንቂያ ደውል መቀየር የሚቻልበትን / የራሳችንን የማሳወቂያ ድምፆችን ማዘጋጀት የምንችልበትን ገፅታ እና ሌሎችም አዳዲስ ገፅታዎች የተካከቱበት አዲስ Update ዛሬ ይፋ አድርጓል።
➡️ አዳዲስ ስለተጨመሩ ገፅታዎች ያንብቡ 👇
telegram.org/blog/notifications-bots
➡️ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያችሁን #Update ለማድረግ ፦
▪️ለአንድሮይድ👉 play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger
▪️ለIOS 👉 https://apps.apple.com/ke/app/telegram-messenger/id686449807
ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያ (በነጭ መደብ ላይ ሰማያዊው የቴሌግራም ምልክት ያረፈበትን) እንድትተጠቀሙ እንመክራለን።
#Telegram
@tikvahethiopia
ቴሌግራም አጫጭር የድምፅ ፋይሎችን እና የድምፅ መልዕክቶችን ለማንኛውም ቻት/መልዕክት ልውውጥ ወደ ማንቂያ ደውል መቀየር የሚቻልበትን / የራሳችንን የማሳወቂያ ድምፆችን ማዘጋጀት የምንችልበትን ገፅታ እና ሌሎችም አዳዲስ ገፅታዎች የተካከቱበት አዲስ Update ዛሬ ይፋ አድርጓል።
➡️ አዳዲስ ስለተጨመሩ ገፅታዎች ያንብቡ 👇
telegram.org/blog/notifications-bots
➡️ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያችሁን #Update ለማድረግ ፦
▪️ለአንድሮይድ👉 play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger
▪️ለIOS 👉 https://apps.apple.com/ke/app/telegram-messenger/id686449807
ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያ (በነጭ መደብ ላይ ሰማያዊው የቴሌግራም ምልክት ያረፈበትን) እንድትተጠቀሙ እንመክራለን።
#Telegram
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
በአሸባሪነት የተፈረጁ አካላትና ያልተፈረጁ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት በሀገራዊ ምክክሩ ይሳተፋሉ ?
በኢፌዴሪ ህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ተብለው የተፈረጁም ሆነ ያልተፈረጁም " ትጥቅ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ " ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሀገራዊ ምክክር መድረኩ አካል ይሆናሉ ? ? የሚለው ጥያቄ የብዙሃኑ ጥያቄ ነው።
በዚህ ጉዳይ ላይ በርካቶች የገዢውን 'ብልፅግና ፓርቲ' ቁርጥ ያለ አቋም ምን እንደሆነ ለማወቅም ይፈልጋሉ።
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ አደም ፋራህ በፋና ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው በሰጡት ቃለ ምልልስ ይህንን ጥያቄ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።
አቶ አደም " ተሳታፊን መለየት እና መወሰን የብልፅግና ፓርቲ ጉዳይ አይደለም። " ብለዋል።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው የሀገራዊ ምክክር የኮሚሽኑ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ነገር ግን ኮሚሽኑ እነዚህ አካላት ለምክክሩ እና ለሀገር አቀፍ አካታች መድረክ እንዲቀርቡ ቢወስን ብልፅግና ይቀበላል ወይ ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ አቶ አደም ፋራህ ፦
" ብልፅግና ለአካታች ሀገር አቀፍ ምክክሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ የሚያበረክት ጉዳይ በሙሉ ፤ ኢትዮጵያ እንድትረጋጋ ፤ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ፤ ዴሞክራሲ እንዲዳብር ፤ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ማንኛውም ጉዳይ ኮሚሽኑ ይዞ ከመጣ ህግና ስርዓትን በጠበቀ መልኩ ለማስተናገድ፤ አስፈላጊ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ዝግጁ ነው " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ሌላው እዚህ ላይ የተነሳ ጥያቄ እንዴት ነው ኮሚሽኑ ቢፈልግ እንኳን በህግና ስርዓቱ በአሸባሪነት የተፈረጁ አካላት ተሳታፊ መሆን የሚችሉት ?
በህግ እና በስርዓቱ አሸባሪ ተብለው የተፈረጁ አካላት ትጥቃቸው እስካልፈቱ ድረስ እንዲህ ያለው ሰላማዊ መድረክ ላይ አይሳተፉም ይላል። ስለዚህ " ብልፅግና በሁለት ካርድ እየተጫወተ ነው " ፤ በሚል ለሚነሳው ክስ አቶ አደም ፋራህ ተከታዩን ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል ፦
" የህግ የበላይነት የሚባለው ለሁሉም አካል በህግ ፊት እኩል ነው። ሁሉም ከህግ በታች ነው። እንዳሻው ህግን የመጣስ መብት የሚሰጠው አካል አይደለም።
ብልፅግና ፓርቲም ህዝብ ሲመርጠው ህግና ስርዓትን አስከብር፣ በሀገሪቱ ህግ ምራኝ ፣ በህግ እና ስርዓት ምራኝ ፣ ሰላም እና ደህንነትን አስከብር፣ በማኔፌስቶው ላይ ያስቀመጥከውን በትክክል ተግብር ፣ ፈፅምልኝ ነው ያለው። ስለዚህ ብልፅግና ፓርቲ ከህግ እና ስርዓት ውጪ ወስኖ የመሄድ ስልጣን የለውም። ኮሚሽኑም በዛው ልክ ነው።
ዋናው ጉዳይ ፤ ኮሚሽኑ ለአካታች የሀገራዊ ምክክሩ ስኬትታማነት ፣ የሚለዩትን አጀንዳዎችና አጀንዳዎቹ ላይ መሳተፍ የሚገባቸው አካላት ከለየ በኃላ እነዚህ አካላት በዚህ ጉዳይ ላይ ቢሳተፉ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ይጠቅማል ብሎ ካመጣው ፤ ብልፅግና ለሀገርና ለህዝብ ነው ቅድሚያ የሚሰጠውና ይቀበላል።
የቀረበው የሀገርን እና የህዝብን ጥቅም የሚያስከብር ከሆነ ሲያስፈፅምም ህግና ስርዓትን በጠበቀ አኳኃን ነው የሚያስፈፅመው።
ስለዚህም ፤ አንድ #አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀ ድርጅት ከአሸባሪነት የሚወጣው በምን ስርዓት ነው የሚለው ህግ እና ስርዓት ያስቀመጠው አለ ፤ ስለዚህ ህግ እና ስርዓትን በጠበቀ መልኩ ነው የምናስተናግደው።
እንደብልፅግና ፓርቲ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬት በእኛ አቅም፣ በእኛ ስልጣን ማድረግ የሚገባንን ነገር በሙሉ እናደርጋለን። ይሄን ስናደርግ ህግ እየጣስን መሆን የለበትም። ስለዚህ ህግ እና ስርዓትን በጠበቀ መንገድ ሂደቱን ጠብቀን ኮሚሽኑ የሚያቀርባቸውን ነገሮች እንደመንግስት ተቀብለን የምናስተናግድበት እና ለአካታች የሀገራዊ ምክክሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፤ ሁኔታዎችን የምናመቻችበት ሁኔታ ይኖራል።
ስለዚህ ሁላችንም ከህግ በታችን ነን ፤ ብልፅግናም ሲሰራ እያንዳንዱ እንቅስቃሴው ሂደቱ በህገመንግስቱ መሰረት ፣ በሀገሪቱ ህጎች መሰረት መሆን መቻል አለበት።
መሻሻል የሚገባው ህግ ካለ ፤ ለዚህ ሂደት እንቅፋት ሊሆን ይችላል ወይም ምቹ ሁኔታ አይፈጥርም ተብሎ የሚታሰብ ካለ የህግ ማሻሻያ ሂደቱን ተከትለን ነው የምናሻሽለው እንጂ ብልፅግና መሪ ፓርቲ ስለሆነ ይሄን ጥዬዋለሁ ፣ ይሄን ፈቅጃለሁ የሚልበት ሁኔታ አይኖርም።
ግን ፥ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ኮሚሽኑ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ እንደ መንግስትም ፤ እንደ መሪ ፓርቲም እኛ ማድረግ የምንችለውን ሁሉ ፣ አቅማችን የሚፈቅደውን ሁሉ ፣ ህግ የሚፈቅድልንን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነን ፤ ቁርጠኛ ነን ፤ በትክክልም እናደርገዋለን " ሲሉ መልሰዋል።
@tikvahethiopia
በአሸባሪነት የተፈረጁ አካላትና ያልተፈረጁ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት በሀገራዊ ምክክሩ ይሳተፋሉ ?
በኢፌዴሪ ህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ተብለው የተፈረጁም ሆነ ያልተፈረጁም " ትጥቅ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ " ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሀገራዊ ምክክር መድረኩ አካል ይሆናሉ ? ? የሚለው ጥያቄ የብዙሃኑ ጥያቄ ነው።
በዚህ ጉዳይ ላይ በርካቶች የገዢውን 'ብልፅግና ፓርቲ' ቁርጥ ያለ አቋም ምን እንደሆነ ለማወቅም ይፈልጋሉ።
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ አደም ፋራህ በፋና ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው በሰጡት ቃለ ምልልስ ይህንን ጥያቄ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።
አቶ አደም " ተሳታፊን መለየት እና መወሰን የብልፅግና ፓርቲ ጉዳይ አይደለም። " ብለዋል።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው የሀገራዊ ምክክር የኮሚሽኑ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ነገር ግን ኮሚሽኑ እነዚህ አካላት ለምክክሩ እና ለሀገር አቀፍ አካታች መድረክ እንዲቀርቡ ቢወስን ብልፅግና ይቀበላል ወይ ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ አቶ አደም ፋራህ ፦
" ብልፅግና ለአካታች ሀገር አቀፍ ምክክሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ የሚያበረክት ጉዳይ በሙሉ ፤ ኢትዮጵያ እንድትረጋጋ ፤ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ፤ ዴሞክራሲ እንዲዳብር ፤ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ማንኛውም ጉዳይ ኮሚሽኑ ይዞ ከመጣ ህግና ስርዓትን በጠበቀ መልኩ ለማስተናገድ፤ አስፈላጊ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ዝግጁ ነው " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ሌላው እዚህ ላይ የተነሳ ጥያቄ እንዴት ነው ኮሚሽኑ ቢፈልግ እንኳን በህግና ስርዓቱ በአሸባሪነት የተፈረጁ አካላት ተሳታፊ መሆን የሚችሉት ?
በህግ እና በስርዓቱ አሸባሪ ተብለው የተፈረጁ አካላት ትጥቃቸው እስካልፈቱ ድረስ እንዲህ ያለው ሰላማዊ መድረክ ላይ አይሳተፉም ይላል። ስለዚህ " ብልፅግና በሁለት ካርድ እየተጫወተ ነው " ፤ በሚል ለሚነሳው ክስ አቶ አደም ፋራህ ተከታዩን ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል ፦
" የህግ የበላይነት የሚባለው ለሁሉም አካል በህግ ፊት እኩል ነው። ሁሉም ከህግ በታች ነው። እንዳሻው ህግን የመጣስ መብት የሚሰጠው አካል አይደለም።
ብልፅግና ፓርቲም ህዝብ ሲመርጠው ህግና ስርዓትን አስከብር፣ በሀገሪቱ ህግ ምራኝ ፣ በህግ እና ስርዓት ምራኝ ፣ ሰላም እና ደህንነትን አስከብር፣ በማኔፌስቶው ላይ ያስቀመጥከውን በትክክል ተግብር ፣ ፈፅምልኝ ነው ያለው። ስለዚህ ብልፅግና ፓርቲ ከህግ እና ስርዓት ውጪ ወስኖ የመሄድ ስልጣን የለውም። ኮሚሽኑም በዛው ልክ ነው።
ዋናው ጉዳይ ፤ ኮሚሽኑ ለአካታች የሀገራዊ ምክክሩ ስኬትታማነት ፣ የሚለዩትን አጀንዳዎችና አጀንዳዎቹ ላይ መሳተፍ የሚገባቸው አካላት ከለየ በኃላ እነዚህ አካላት በዚህ ጉዳይ ላይ ቢሳተፉ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ይጠቅማል ብሎ ካመጣው ፤ ብልፅግና ለሀገርና ለህዝብ ነው ቅድሚያ የሚሰጠውና ይቀበላል።
የቀረበው የሀገርን እና የህዝብን ጥቅም የሚያስከብር ከሆነ ሲያስፈፅምም ህግና ስርዓትን በጠበቀ አኳኃን ነው የሚያስፈፅመው።
ስለዚህም ፤ አንድ #አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀ ድርጅት ከአሸባሪነት የሚወጣው በምን ስርዓት ነው የሚለው ህግ እና ስርዓት ያስቀመጠው አለ ፤ ስለዚህ ህግ እና ስርዓትን በጠበቀ መልኩ ነው የምናስተናግደው።
እንደብልፅግና ፓርቲ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬት በእኛ አቅም፣ በእኛ ስልጣን ማድረግ የሚገባንን ነገር በሙሉ እናደርጋለን። ይሄን ስናደርግ ህግ እየጣስን መሆን የለበትም። ስለዚህ ህግ እና ስርዓትን በጠበቀ መንገድ ሂደቱን ጠብቀን ኮሚሽኑ የሚያቀርባቸውን ነገሮች እንደመንግስት ተቀብለን የምናስተናግድበት እና ለአካታች የሀገራዊ ምክክሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፤ ሁኔታዎችን የምናመቻችበት ሁኔታ ይኖራል።
ስለዚህ ሁላችንም ከህግ በታችን ነን ፤ ብልፅግናም ሲሰራ እያንዳንዱ እንቅስቃሴው ሂደቱ በህገመንግስቱ መሰረት ፣ በሀገሪቱ ህጎች መሰረት መሆን መቻል አለበት።
መሻሻል የሚገባው ህግ ካለ ፤ ለዚህ ሂደት እንቅፋት ሊሆን ይችላል ወይም ምቹ ሁኔታ አይፈጥርም ተብሎ የሚታሰብ ካለ የህግ ማሻሻያ ሂደቱን ተከትለን ነው የምናሻሽለው እንጂ ብልፅግና መሪ ፓርቲ ስለሆነ ይሄን ጥዬዋለሁ ፣ ይሄን ፈቅጃለሁ የሚልበት ሁኔታ አይኖርም።
ግን ፥ ለአካታች ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ኮሚሽኑ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ እንደ መንግስትም ፤ እንደ መሪ ፓርቲም እኛ ማድረግ የምንችለውን ሁሉ ፣ አቅማችን የሚፈቅደውን ሁሉ ፣ ህግ የሚፈቅድልንን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነን ፤ ቁርጠኛ ነን ፤ በትክክልም እናደርገዋለን " ሲሉ መልሰዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ "ነሲሓ" ኢፍጣር ፕሮግራም ! «ነሲሓ» የተሰኘ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት፤ በዛሬ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ በስድስት ጎዳናዎች ላይ 12 ኪ.ሜ የሸፈነ ጾመኞችን የማስፈጠር መርሃ ግብር አካሂዷል። የቦታዎቹ ዝርዝር እንደሚከተለው ነው። ①) ዓለም ባንክ ከሚገኘው ኢማሙ አሕመድ መስጂድ አደባባይ ጀምሮ እስከ ቤተል ባለው መንገድ፣ ②) ከቢላል ኮካ መስጂድ ወደ አብነት ባለው መንገድ በጭድ ተራ…
#Iftar
በነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት (NCDO) አስረባባሪነት ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ በተመረጡ 11 ጎዳናዎች ላይ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ይካሄዳል።
«ኑ አብረን በጋራ እናፍጥር!» በሚል የሚካሄደው ይህ የኢፍጣር መርሃ ግብር 35 ኪሎ ሜትር ገደማ ይሸፍናል።
የሚያካትታቸው 11 ጎዳናዎች ዝርዝር ፦
1) ከኮካ ቢላል መስጂድ - ተክለሃይማኖት
2) ከእህል በረንዳ - ቢላል መስጂድ
3) ከቢላል መስጂድ - እፎይታ
4) ከኮልፌ ቀብር - ሎሚ ሜዳ
5) ከአስኮ አዲስ ሰፈር - በድር መስጂድ
6) ከመንዲዳ - ኢማሙ አሕመድ መስጂድ
7) ከአየር ጤና - ግራር
8) ከግራር - ስልጤ ሰፈር
9) ከጀሞ 2 አደባባይ - ኖክ
10) ከረጲ ትም/ቤት - አጃምባ ማዞሪያ
11) ከአየር ጤና እስከ አለም ባንክ
አቅሙ ያለው ሰው በዕለቱ ኢፍጣር በሚካሄድባቸው ጎፋናዎች ሲያቀና እንደ ውሃና ቴምር ያሉ ቀለል ያሉ ማስፈጠሪያቸውን ለሌሎች ቢይዝ መልካም ነው ተብሏል።
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ባለፈ አመት በ6 ጎዳናዎች ላይ ደማቅ የኢፍጣር ፕሮግራም ማካሄዱ ይታወሳል።
ተቋሙ በዚህም አመት ረመዷን ከገባ ጀምሮ በየቀኑ 250 ሰዎችን በቋሚነት እያስፈጠረ ሲሆን በክልል ከተሞች በሚገኙ ቅርንጫፎቹ ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በትጋት እየሠራ እንደሚገኝ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ዛሬ በሚካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም አጋር መሆን የሚፈልጉና አቅመ ደካሞችን ማስፈጠር ለሚፈልጉ 0972747474 ላይ መደወል ይችላሉ ተብሏል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
በነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት (NCDO) አስረባባሪነት ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ በተመረጡ 11 ጎዳናዎች ላይ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ይካሄዳል።
«ኑ አብረን በጋራ እናፍጥር!» በሚል የሚካሄደው ይህ የኢፍጣር መርሃ ግብር 35 ኪሎ ሜትር ገደማ ይሸፍናል።
የሚያካትታቸው 11 ጎዳናዎች ዝርዝር ፦
1) ከኮካ ቢላል መስጂድ - ተክለሃይማኖት
2) ከእህል በረንዳ - ቢላል መስጂድ
3) ከቢላል መስጂድ - እፎይታ
4) ከኮልፌ ቀብር - ሎሚ ሜዳ
5) ከአስኮ አዲስ ሰፈር - በድር መስጂድ
6) ከመንዲዳ - ኢማሙ አሕመድ መስጂድ
7) ከአየር ጤና - ግራር
8) ከግራር - ስልጤ ሰፈር
9) ከጀሞ 2 አደባባይ - ኖክ
10) ከረጲ ትም/ቤት - አጃምባ ማዞሪያ
11) ከአየር ጤና እስከ አለም ባንክ
አቅሙ ያለው ሰው በዕለቱ ኢፍጣር በሚካሄድባቸው ጎፋናዎች ሲያቀና እንደ ውሃና ቴምር ያሉ ቀለል ያሉ ማስፈጠሪያቸውን ለሌሎች ቢይዝ መልካም ነው ተብሏል።
ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ባለፈ አመት በ6 ጎዳናዎች ላይ ደማቅ የኢፍጣር ፕሮግራም ማካሄዱ ይታወሳል።
ተቋሙ በዚህም አመት ረመዷን ከገባ ጀምሮ በየቀኑ 250 ሰዎችን በቋሚነት እያስፈጠረ ሲሆን በክልል ከተሞች በሚገኙ ቅርንጫፎቹ ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በትጋት እየሠራ እንደሚገኝ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ዛሬ በሚካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም አጋር መሆን የሚፈልጉና አቅመ ደካሞችን ማስፈጠር ለሚፈልጉ 0972747474 ላይ መደወል ይችላሉ ተብሏል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሰሜን ኮሪያ ሚሳኤል አስወነጨፈች። ትላንትና ለሊት ሰሜን ኮሪያ የተጠረጠረ ባላስቲክ ሚሳኤል ወደ ምስራቅ ባህር ማስወንጨፏን ጎረቤቶቿ እየገለፁ ይገኛሉ። የደረሰ ጉዳት የለም። ፒዮንግያንግ ይህ የሚሳኤል ማስወንጨፍ ሙከራዋ 2022 ከገባ ጊዜ አንስቶ 9ኛው መሆኑ ነው። የአሜሪካ እና የደቡብ ኮሪያ የደህንነት ባለስልጣናት የሰሜን ኮሪያን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተሉት ነው ተብሏል። @tikvahethiopia
#NorthKorea
ሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል ሙከራዋን ገፍታበታለች።
በዚህ አመት እጅግ ተደጋጋሚ የሚሳኤል ሙከራ ስታደርግ የነበረችው ሰሜን ኮሪያ በአመቱ 12ኛ ነው የተባለውን የሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን የደቡብ ኮሪያ ጦር አስታውቋል።
ሰሜን ኮሪያ ትላንት ትላንት ቅዳሜ 2 ሚሳኤሎችን በሰሜን ምስራቅ የባህር ጠረፍ ላይ ከምትገኘው ሃምሁንግ ከተማ ማስወንጨፏ እና 68 ማይል መጓዛቸው ተነግሯል።
የአሁኑ ሙከራ ከቀድሞዎቹ በኃይል ያነሰ ቢሆንም በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ውጥረት ባለበት ሁኔታ ወቅት መፈፀሙ አሳሳቢ እንዳደረገው ተነግሯል።
በሌላ በኩል አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ ዓመታዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምዳቸውን ሰኞ ይጀምራሉ። ይህን ልምምስ ሰሜን ኮሪያ በፅኑ አውግዛዋለች። ሀገሪቱ የሁለቱን አጋሮች የጋራ ልምምዶች እንደ ወረራ ልምምድ የሚቆጠር ነው ብላዋለች።
@tikvahethiopia
ሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል ሙከራዋን ገፍታበታለች።
በዚህ አመት እጅግ ተደጋጋሚ የሚሳኤል ሙከራ ስታደርግ የነበረችው ሰሜን ኮሪያ በአመቱ 12ኛ ነው የተባለውን የሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን የደቡብ ኮሪያ ጦር አስታውቋል።
ሰሜን ኮሪያ ትላንት ትላንት ቅዳሜ 2 ሚሳኤሎችን በሰሜን ምስራቅ የባህር ጠረፍ ላይ ከምትገኘው ሃምሁንግ ከተማ ማስወንጨፏ እና 68 ማይል መጓዛቸው ተነግሯል።
የአሁኑ ሙከራ ከቀድሞዎቹ በኃይል ያነሰ ቢሆንም በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ውጥረት ባለበት ሁኔታ ወቅት መፈፀሙ አሳሳቢ እንዳደረገው ተነግሯል።
በሌላ በኩል አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ ዓመታዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምዳቸውን ሰኞ ይጀምራሉ። ይህን ልምምስ ሰሜን ኮሪያ በፅኑ አውግዛዋለች። ሀገሪቱ የሁለቱን አጋሮች የጋራ ልምምዶች እንደ ወረራ ልምምድ የሚቆጠር ነው ብላዋለች።
@tikvahethiopia
" ሆሣዕና '' (የዐብይ ፆም 8ኛ ሳምንት)
እንኳን አደረሳችሁ !
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ፆም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።
ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።
ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡
ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።
በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡
በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።
@tikvahethiopia
እንኳን አደረሳችሁ !
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ፆም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።
ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።
ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡
ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።
በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡
በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።
@tikvahethiopia