TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Abyei #UNISFA
ተመድ ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ሳውየርን የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ሃይል አዛዥ አድርጎ ሾሟል።
ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ዜግነታቸው ናይጄሪያዊ ሲሆኑ በኢትዮጵያዊው ሜጀር ጀነራል ከፍያለው አምዴ ተሰማ ምትክ ነው በቦታ የተሾሙት።
ሜ/ጀነራል ከፍያለው አምዴ በአብዬ ግዛት የነበረውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ሲመሩ እንደነበር ይታወቃል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሜ/ጄነራል ከፍያለው አምዴ የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ኃይል አዘዥ ሆነው ከተሸሙበት ጊዜ አንስቶ ላሳዩት ትጋት፣ የሰጡት አግልግሎትና ውጤታማ አመራር ምስጋና አቅርበዋል።
ሱዳን በአብየ ግዛት ያለው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከስፍራው እንዲወጣ ጥያቄ ማቅረቧ ይታወሳል።
ከሳምንታት በፊት ተመድ በአብዬ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የመተካቱ ሂደት በየካቲት ወር እንደሚጀመር መግለፁ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
ተመድ ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ሳውየርን የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ሃይል አዛዥ አድርጎ ሾሟል።
ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ዜግነታቸው ናይጄሪያዊ ሲሆኑ በኢትዮጵያዊው ሜጀር ጀነራል ከፍያለው አምዴ ተሰማ ምትክ ነው በቦታ የተሾሙት።
ሜ/ጀነራል ከፍያለው አምዴ በአብዬ ግዛት የነበረውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ሲመሩ እንደነበር ይታወቃል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሜ/ጄነራል ከፍያለው አምዴ የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ኃይል አዘዥ ሆነው ከተሸሙበት ጊዜ አንስቶ ላሳዩት ትጋት፣ የሰጡት አግልግሎትና ውጤታማ አመራር ምስጋና አቅርበዋል።
ሱዳን በአብየ ግዛት ያለው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከስፍራው እንዲወጣ ጥያቄ ማቅረቧ ይታወሳል።
ከሳምንታት በፊት ተመድ በአብዬ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የመተካቱ ሂደት በየካቲት ወር እንደሚጀመር መግለፁ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia