የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከልን እና ላቦራቶሪን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
ከጤና ሚኒስትር ዴኤታዎች ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ ጋር በመሆን ማዕከሉን የጎበኙት ሚኒስትሯ ከማዕከሉ አስተባባሪዎች ጋርም ውይይት አድርገዋል፡፡
#MoH #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከጤና ሚኒስትር ዴኤታዎች ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ ጋር በመሆን ማዕከሉን የጎበኙት ሚኒስትሯ ከማዕከሉ አስተባባሪዎች ጋርም ውይይት አድርገዋል፡፡
#MoH #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል 45 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥረው ወደ ለይቶ ማቆያ ገብተዋል። ከነዚህ ውስጥ 22 ሰዎች በተደረገላቸው ምርመራ ከኮሮና ቫይረስ ነፃ መሆናቸው ተረጋግጧል። የተቀሩት ደግሞ ውጤታቸው እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኦሮሚያ ክልል አምስት መቶ ሺህ (500,000) የአፍ መሸፈኛ (ማስክ) እና 48,000 ሊትር ሳኒታይዘር እንዳዘጋጀ ገልጿል። በቅርቡ ለነዋሪዎች እንደሚያሰራጭ አሳውቋል።
በኦሮሚያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በአራት አካባቢዎች የለይቶ ማቆያዎች ተዘጋጅተዋል። ለህክምና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል ተብሏል።
በክልል የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ምልክት የታየበትን ሰው ጥቆማ ለመስጠት የ24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጥ ነፃ የስልክ መስመር 6955 ይፋ ተደርጓል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኦሮሚያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በአራት አካባቢዎች የለይቶ ማቆያዎች ተዘጋጅተዋል። ለህክምና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል ተብሏል።
በክልል የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ምልክት የታየበትን ሰው ጥቆማ ለመስጠት የ24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጥ ነፃ የስልክ መስመር 6955 ይፋ ተደርጓል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TurkishAirlines
የቱርክ አየር መንገድ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ ምክንያት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ5 አገሮች በስተቀር ዓለም አቀፍ በረራዎችን እ.ኤ.አ ከመጋቢት 27 ቀን 2020 ጀምሮ እንደሚያቆም አስታውቋል። አየር መንገዱ ወደ ሆንግ ኮንግ፣ ሞስኮ፣ አዲስ አበባ፣ ኒው ዮርክና ዋሽንግተን የሚያደርገው በረራ እንደማይቋረጥ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቢላል ኢክሲ ማስታወቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
#Reuters #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቱርክ አየር መንገድ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ ምክንያት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ5 አገሮች በስተቀር ዓለም አቀፍ በረራዎችን እ.ኤ.አ ከመጋቢት 27 ቀን 2020 ጀምሮ እንደሚያቆም አስታውቋል። አየር መንገዱ ወደ ሆንግ ኮንግ፣ ሞስኮ፣ አዲስ አበባ፣ ኒው ዮርክና ዋሽንግተን የሚያደርገው በረራ እንደማይቋረጥ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቢላል ኢክሲ ማስታወቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
#Reuters #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ድንበሮቿን ለሰዎች ዝውውር ዝግ አደረገች!
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ድንበሮች ለሰዎች ዝውውር ዝግ መደረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል።
ወረርሽኙን ለመከላከልም መንግስት አምስት ቢሊዮን ብር መበጀቱንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስታወቁት።
በአውሮፕላን ከውጭ በሚገቡ መንገደኞች ላይ ለ14 ቀናት ተለይው እንዲያቆዩ የሚያስገድደው ውሳኔም ከዛሬ ጀምሮ በመተግበር ላይ ነው።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ድንበሮች ለሰዎች ዝውውር ዝግ መደረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል።
ወረርሽኙን ለመከላከልም መንግስት አምስት ቢሊዮን ብር መበጀቱንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስታወቁት።
በአውሮፕላን ከውጭ በሚገቡ መንገደኞች ላይ ለ14 ቀናት ተለይው እንዲያቆዩ የሚያስገድደው ውሳኔም ከዛሬ ጀምሮ በመተግበር ላይ ነው።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከደህንነት ዘርፍ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። ከውይይቱ በኋላ የሚከተሉት ዐበይት እርምጃዎች የሚተገበሩ መሆኑን ይፋ አድርገዋል፦
- ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን አንስቶ፣ የደህንነት ዘርፉ በቁጥር የበዛ ሰው የሚሳተፍባቸውን ስብሰባዎችን የሚያስቆምና ማህበራዊ ርቀትን መጠበቅ የሚያስተገብር ይሆናል፡፡
- የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ የመንግስት ተቋማት ማህበራዊ ርቀትን ተፈጻሚ ማድረግና ስብሰባ ሲያካሄዱ ቫይረሱን የመከላከል ቅድመ ጥንቃቄዎችን ተፈጻሚ ማድረግ አለባቸው፡፡
- የመንግስት ተቋማት የተቀጣሪዎቻቸውን ሁኔታ በማጣራት እንደየሁኔታው አንዳንዶች በቤታቸውን ሆነው የሚሰሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤
- የሕዝብ መጓጓዠ አገልግሎት ሰጪዎች አጨናንቆ ተሳፋሪዎችን መጫን የማይችሉ ሲሆን፣ ይህን ማድረጋቸው በትራፊክ ፖሊስና በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት ቁጥጥር የሚደረግበት ይሆናል፡፡
- ብሔራዊ የመከላከያ ሰራዊትና ፖሊስ ውስጣዊ ቅደመ ዝግጅት በማድረግ በአገር ደረጃ የቫይረሱ ስርጭት የመከላከል ስራን ለማስፈጸም ማዘጋጀት፣
- በተጠቃሚው ማህበረሰብ ላይ ሕገ ወጥ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ተቋማት ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡
- መገናኛ ብዙሃን በትኩረት በየደረጃው ግንዛቤን የማሳደግ ሚናን መጫወት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ብሔራዊ የመከላከያ ሰራዊት በድንበር አከባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ይገታሉ፡፡ ይህ እርምጃ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ሸቀጦችና አስፈላጊ መገልገያዎችን አይጨምርም፡፡
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን አንስቶ፣ የደህንነት ዘርፉ በቁጥር የበዛ ሰው የሚሳተፍባቸውን ስብሰባዎችን የሚያስቆምና ማህበራዊ ርቀትን መጠበቅ የሚያስተገብር ይሆናል፡፡
- የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ የመንግስት ተቋማት ማህበራዊ ርቀትን ተፈጻሚ ማድረግና ስብሰባ ሲያካሄዱ ቫይረሱን የመከላከል ቅድመ ጥንቃቄዎችን ተፈጻሚ ማድረግ አለባቸው፡፡
- የመንግስት ተቋማት የተቀጣሪዎቻቸውን ሁኔታ በማጣራት እንደየሁኔታው አንዳንዶች በቤታቸውን ሆነው የሚሰሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤
- የሕዝብ መጓጓዠ አገልግሎት ሰጪዎች አጨናንቆ ተሳፋሪዎችን መጫን የማይችሉ ሲሆን፣ ይህን ማድረጋቸው በትራፊክ ፖሊስና በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት ቁጥጥር የሚደረግበት ይሆናል፡፡
- ብሔራዊ የመከላከያ ሰራዊትና ፖሊስ ውስጣዊ ቅደመ ዝግጅት በማድረግ በአገር ደረጃ የቫይረሱ ስርጭት የመከላከል ስራን ለማስፈጸም ማዘጋጀት፣
- በተጠቃሚው ማህበረሰብ ላይ ሕገ ወጥ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ተቋማት ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡
- መገናኛ ብዙሃን በትኩረት በየደረጃው ግንዛቤን የማሳደግ ሚናን መጫወት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ብሔራዊ የመከላከያ ሰራዊት በድንበር አከባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ይገታሉ፡፡ ይህ እርምጃ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ሸቀጦችና አስፈላጊ መገልገያዎችን አይጨምርም፡፡
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
በአፍሪካ እስካሁን የኮሮና ቫይረስ የተከሰተባቸው አገራት አርባ ሶስት (43) መድረሳቸውን እና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 1 ሺህ 396 መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 122 ሰዎች ማገገማቸውን ድርጅቱ ጠቁሟል።
ናይጄሪያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የመጀመሪያውን ሞት ማስመዝገቧን ደግሞ ቢቢሲ የሀገሪቱን የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ጠቅሶ ዘግቧል።
በቫይረሱ ምክንያት ሕይወቱ ያለፈው እንግሊዝ ውስጥ የሕክምና ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ወደ ሀገሪቱ የተመለሰ አንድ የ67 ዓመት ግለሰብ መሆኑ ነው የተነገረው።
#BBC #WHO #ETV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ እስካሁን የኮሮና ቫይረስ የተከሰተባቸው አገራት አርባ ሶስት (43) መድረሳቸውን እና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 1 ሺህ 396 መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 122 ሰዎች ማገገማቸውን ድርጅቱ ጠቁሟል።
ናይጄሪያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የመጀመሪያውን ሞት ማስመዝገቧን ደግሞ ቢቢሲ የሀገሪቱን የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ጠቅሶ ዘግቧል።
በቫይረሱ ምክንያት ሕይወቱ ያለፈው እንግሊዝ ውስጥ የሕክምና ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ወደ ሀገሪቱ የተመለሰ አንድ የ67 ዓመት ግለሰብ መሆኑ ነው የተነገረው።
#BBC #WHO #ETV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮቪድ-19 ህይወቱ ያለፈው የ30 ዓመቱ ጋዜጠኛ!
ዚምባቡዌ ውስጥ ሕይወቱን ያጣው የሰላሳ (30) ዓመቱ የብሮድካስት ጋዜጠኛ ዞሮሮ ማካምባ ይባላል። በኮሮና ቫይረስ ወጣት ሊሞት አይችልም ተብሎ የሚነገረውን ሐሰት ያደረገው ይኸው ሞት ዚምባቡዌያውያንን አስደንግጧል።
ጋዜጠኛው በአገሩ የታወቀ እንደነበር እና የሀብታም ቤተሰብ ልጅም እንደሆነ ተዘግቧል። ቅዳሜ በቫይረሱ እንደተጠቃ በምርመራ የተረጋገጠው ዞሮሮ የጤናው ሁኔታ በፍጥነት ስላሽቆለቆለ በአገሪቱ መዲና ሀራሬ በጽኑ ሕሙማን ማቆያ ገብቶ ነበር።
#BBC #ETV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዚምባቡዌ ውስጥ ሕይወቱን ያጣው የሰላሳ (30) ዓመቱ የብሮድካስት ጋዜጠኛ ዞሮሮ ማካምባ ይባላል። በኮሮና ቫይረስ ወጣት ሊሞት አይችልም ተብሎ የሚነገረውን ሐሰት ያደረገው ይኸው ሞት ዚምባቡዌያውያንን አስደንግጧል።
ጋዜጠኛው በአገሩ የታወቀ እንደነበር እና የሀብታም ቤተሰብ ልጅም እንደሆነ ተዘግቧል። ቅዳሜ በቫይረሱ እንደተጠቃ በምርመራ የተረጋገጠው ዞሮሮ የጤናው ሁኔታ በፍጥነት ስላሽቆለቆለ በአገሪቱ መዲና ሀራሬ በጽኑ ሕሙማን ማቆያ ገብቶ ነበር።
#BBC #ETV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮሮና ቫይረስ የተያዘ 1 ተጨማሪ ሰው መገኘቱ ተገለፀ!
መጋቢት 3/2012 ዓ.ም የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ በሀገራችን ከተገኘ ወዲህ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ (1) ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ በአጠቃላይ ቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 12 ደርሷል።
ታማሚው የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ሲሆን ከዱባይ ወደ ሀገር ውስጥ መጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም የገባ ነው።
ግለሰቡ የሕመም ምልክት የነበረው በመሆኑ በመጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄደ ሲሆን ተቋሙም ለኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖረት በማደረግ በተደረገለት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል።
ታማሚውም በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ሲሆን ጤንነቱ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ግንኙነት የነበራቸው 15 ሰዎች በክትትል ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መጋቢት 3/2012 ዓ.ም የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ በሀገራችን ከተገኘ ወዲህ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ (1) ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ በአጠቃላይ ቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 12 ደርሷል።
ታማሚው የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ሲሆን ከዱባይ ወደ ሀገር ውስጥ መጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም የገባ ነው።
ግለሰቡ የሕመም ምልክት የነበረው በመሆኑ በመጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄደ ሲሆን ተቋሙም ለኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖረት በማደረግ በተደረገለት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል።
ታማሚውም በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ሲሆን ጤንነቱ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ግንኙነት የነበራቸው 15 ሰዎች በክትትል ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቦሌ ቡልቡላ አካባቢ አርሶ አደሮች የአ/አ ከተማ አስተዳደር ለ14 ቀን በማቆያ እንዲገቡ ላደረጋቸው ሰዎች የሚውል የሰብል ምርቶችን በስጦታነት አበርክተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የተለያዩ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን አበረከቷል፡፡
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ከአየር መንገድ ጠፍተው ወደ ኅብረተሰቡ ተቀላቅዋል የተባሉ ግለሰቦች የገቡት የግዴታ ለይቶ ማቆየት ከመተግበሩ በፊት ነው" - የጤና ሚኒስቴር
መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ/ም ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ የመጡ አንድ መንገደኛ ወደ ሀገር ከገቡ በኋላ ከአየር መንገድ በመጥፋት ወደ ኅብረተሰቡ ተቀላቅለዋል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ላይ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ማጣራት ማካሔዱን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ግለሰቧ ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ መጋቢት 08 ቀን 2012 ዓ.ም ከባለቤታቸው መምጣታቸውንና ወደ ሀገር ሲገቡ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር መንገድ የሚደረገውን የልየታ ሂደት ውስጥ ማለፋቸውን ገልጿል።
ግለሰቦቹ የገቡት የግዴታ ለይቶ ማቆየት ከመተግበሩ በፊት መሆኑንም አመልክቷል። በቀጣይም ከኅብረተሰቡ የሚመጡ ጥቆማዎችን በመቀበል እና በማጣራት ተግባራዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አመልክቷል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ/ም ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ የመጡ አንድ መንገደኛ ወደ ሀገር ከገቡ በኋላ ከአየር መንገድ በመጥፋት ወደ ኅብረተሰቡ ተቀላቅለዋል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ላይ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ማጣራት ማካሔዱን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ግለሰቧ ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ መጋቢት 08 ቀን 2012 ዓ.ም ከባለቤታቸው መምጣታቸውንና ወደ ሀገር ሲገቡ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር መንገድ የሚደረገውን የልየታ ሂደት ውስጥ ማለፋቸውን ገልጿል።
ግለሰቦቹ የገቡት የግዴታ ለይቶ ማቆየት ከመተግበሩ በፊት መሆኑንም አመልክቷል። በቀጣይም ከኅብረተሰቡ የሚመጡ ጥቆማዎችን በመቀበል እና በማጣራት ተግባራዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አመልክቷል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
# UPDATE
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡
ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለት መቶ አስራ ስድስት አዲስ ታማሚዎች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡
ኮሮና ቫይረስ ጊኒ ቢሳዎ እና ማሊ ለመጀመሪያ ጊዜ መግባቱ እና እያንዳንዳቸው አንድ ታማሚ ማግኘታቸውም ተገልጿል፡፡
#WHO #AfricaCDC #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡
ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለት መቶ አስራ ስድስት አዲስ ታማሚዎች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡
ኮሮና ቫይረስ ጊኒ ቢሳዎ እና ማሊ ለመጀመሪያ ጊዜ መግባቱ እና እያንዳንዳቸው አንድ ታማሚ ማግኘታቸውም ተገልጿል፡፡
#WHO #AfricaCDC #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
ባህላዊ ሕክምናን ከዘመናዊ ሕክምና ጋር በማቀናጀት ለኮሮና ቫይረስ መድኃኒት ለማግኘት የምርምር ሥራ እየሠራ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የምርምር ሂደቱ ተስፋ ያለው መሆኑንም ነው የጤና ሚኒስቴር የገለጸው።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባህላዊ ሕክምናን ከዘመናዊ ሕክምና ጋር በማቀናጀት ለኮሮና ቫይረስ መድኃኒት ለማግኘት የምርምር ሥራ እየሠራ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የምርምር ሂደቱ ተስፋ ያለው መሆኑንም ነው የጤና ሚኒስቴር የገለጸው።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ኮቪድ-19 አየር ወለድ ወረርሽኝ አይደለም!" - WHO
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) አየር ወለድ ወረርሽኝ እንደሆነ ተደርጎ የሚገለፀው የሀሰት መረጃ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት በድጋሚ አስታውቋል።
ኮቪድ-19 ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚስልበት፣ በሚያስነጥስበት አልያም በሚናገርበት ወቅት እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለፀው።
ከወረርሽኙ ራስን መከላከል የሚቻለው በሰዎች መካከል ርቀትን ቢያንስ በአንድ ሜትር በማስፋት፣ በተደጋጋሚ እጅን በሳሙና ቢያንስ ለ20 ሰከንዶች አሽቶ በመታጠብ፣ አልኮል ባላቸው ሳኒታይዘሮች እጅን በማፅዳት እና ፊትን በእጅ ባለመንካት ነው።
#etv #WHO
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) አየር ወለድ ወረርሽኝ እንደሆነ ተደርጎ የሚገለፀው የሀሰት መረጃ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት በድጋሚ አስታውቋል።
ኮቪድ-19 ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚስልበት፣ በሚያስነጥስበት አልያም በሚናገርበት ወቅት እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለፀው።
ከወረርሽኙ ራስን መከላከል የሚቻለው በሰዎች መካከል ርቀትን ቢያንስ በአንድ ሜትር በማስፋት፣ በተደጋጋሚ እጅን በሳሙና ቢያንስ ለ20 ሰከንዶች አሽቶ በመታጠብ፣ አልኮል ባላቸው ሳኒታይዘሮች እጅን በማፅዳት እና ፊትን በእጅ ባለመንካት ነው።
#etv #WHO
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ሀገር አቀፍ መረጃዎች፦
- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።
- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።
- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።
- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡
- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።
#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።
- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።
- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።
- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡
- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።
#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
1441ኛው የኢድ አል-ፊጥር በዓል!
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ለምእመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በዕለቱ የጀምዓ ሶላት እንደማይኖር የገለጹት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ምእመናን በዓሉን በየቤታቸው #እንዲያከብሩት አሳስበዋል፡፡
ምእመናን የኢድ አል-ፊጥር በዓል የተራቡትን በማጉረስ ፣ የተጠሙትን በማጠጣት በአጠቃላይ የተቸገሩትን በመርዳት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ለምእመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በዕለቱ የጀምዓ ሶላት እንደማይኖር የገለጹት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ምእመናን በዓሉን በየቤታቸው #እንዲያከብሩት አሳስበዋል፡፡
ምእመናን የኢድ አል-ፊጥር በዓል የተራቡትን በማጉረስ ፣ የተጠሙትን በማጠጣት በአጠቃላይ የተቸገሩትን በመርዳት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia