TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Coronavirus : Top-risk African nations!

- Nigeria
- Algeria
- Angola
- Ivory Coast
- DR Congo
- #Ethiopia
- Ghana
- Kenya
- Mauritius
- South Africa
- Tanzania
- Uganda
- Zambia

#WHO

[tvcnews.TV]

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ ኬዝ 769 ደርሷል!

በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የተያዙ ሰዎች ቁጥር 769 መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ አስታውቋል፡፡ በግብጽ 210 ፣ በደቡብ አፍሪካ 150፣ በአልጄሪያ 82 ፣ በሞሮኮ 61 ፣ በቡርኪና ፋሶ 40፣ በቱኒዚያ 39፣ በሴኔጋል 38 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተገልጿል፤ ቀሪዎቹ 148 ታማሚዎች በ26 የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ናቸው፡፡ በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽ ከተከሰተ በኃላ 19 ሰዎች ሲሞቱ ፣ 69 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ታውቋል፡፡

#EBC #WHO
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በአፍሪካ እስካሁን የኮሮና ቫይረስ የተከሰተባቸው አገራት አርባ ሶስት (43) መድረሳቸውን እና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 1 ሺህ 396 መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 122 ሰዎች ማገገማቸውን ድርጅቱ ጠቁሟል።

ናይጄሪያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የመጀመሪያውን ሞት ማስመዝገቧን ደግሞ ቢቢሲ የሀገሪቱን የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ጠቅሶ ዘግቧል።

በቫይረሱ ምክንያት ሕይወቱ ያለፈው እንግሊዝ ውስጥ የሕክምና ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ወደ ሀገሪቱ የተመለሰ አንድ የ67 ዓመት ግለሰብ መሆኑ ነው የተነገረው።

#BBC #WHO #ETV
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
# UPDATE

በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡

ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለት መቶ አስራ ስድስት አዲስ ታማሚዎች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡

ኮሮና ቫይረስ ጊኒ ቢሳዎ እና ማሊ ለመጀመሪያ ጊዜ መግባቱ እና እያንዳንዳቸው አንድ ታማሚ ማግኘታቸውም ተገልጿል፡፡

#WHO #AfricaCDC #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ኮቪድ-19 አየር ወለድ ወረርሽኝ አይደለም!" - WHO

የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) አየር ወለድ ወረርሽኝ እንደሆነ ተደርጎ የሚገለፀው የሀሰት መረጃ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት በድጋሚ አስታውቋል።

ኮቪድ-19 ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚስልበት፣ በሚያስነጥስበት አልያም በሚናገርበት ወቅት እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለፀው።

ከወረርሽኙ ራስን መከላከል የሚቻለው በሰዎች መካከል ርቀትን ቢያንስ በአንድ ሜትር በማስፋት፣ በተደጋጋሚ እጅን በሳሙና ቢያንስ ለ20 ሰከንዶች አሽቶ በመታጠብ፣ አልኮል ባላቸው ሳኒታይዘሮች እጅን በማፅዳት እና ፊትን በእጅ ባለመንካት ነው።

#etv #WHO
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom #WHO #DonaldTrump

ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለWHO የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በጊዜ አልተናገረም ብለዋል ፕሬዘዳንቱ።

ድርጅቱ ይህን ያደርገው በሽታው ለተጀመረባት #ቻይና ሲል ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምት አዘል አነጋገር ተናግረዋል። "በጣም ቻይና ተኮር ይመስላሉ ፣ ይህን ማጤን ይኖርብናል' ሲሉ ተደምጠዋል ዶናልድ ትራምፕ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ባለበት በዚህ አይነት ሁኔታ ለጤናው ድርጅት /WHO/ የሚዋጣ ገንዘብ መከልከ ተገቢ ነው ወይ? ተብለው ከጋዜጠኛ የተጠየቁት ትራምፕ 'እኔ አንሰጥም አላልኩም፣ እናጤነዋለን ነው ያለኩት' ሲሉ መልሰዋል።

ከፍተኛ ዘመቻ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ዛሬ በሰጡት ዕለታዊ መግለጫቸው ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው ፤ እሳቸው ግን ግድ እንዳልሰጣቸው ተናግረዋል። በማን ይህ ሊደረግ እንደቻለ ግን አልተናገሩም።

ከሁለት (2) እና ከሦስት (3) ወር በላይ #ዘረኛ ጥቃቶች ተሰንዝረውብኛል ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ 'ጥቁር ተብያለሁ። እውነቱን ለመናገር እኔ በጥቁርነቴ እኮራለሁ። የሚባለው ነገርም ግድ አይሰጠኝም' ሲሉም ተደምጠዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#WHO

የዓለም ጤና ድርጅት በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ባለፈው ሳምንት በፍጥነት ከፍ እያለ መምጣቱን ተከትሎ፣ አህጉሪቱ ቀጣይዋ የቫይረሱ ማዕከል(Epicenter) ልትሆን ትችላለች አለ።

እስካሁን ድረስ በአፍሪካ በቫይረሱ ሳቢያ ወደ 1,000 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸውን እና ከ18,000 በላይ ሰዎች በቫይረሱ እንደተያዙ የጠቀሰው ድርጅቱ፣ ቁጥሩ በአውሮፓ አንዳንድ ሀገራትና በአሜሪካ ከታየው እጅግ ያነሰ መሆኑን ጠቅሷል።

ቫይረሱ በደቡብ አፍሪካ፣ በናይጄሪያ፣ በኮትዲቯር በካሜሩን እና በጋና ከዋና ከተሞች ወደ መሃል አገር እየተሰራጨ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መታዘቡን፣ የድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር ማትሺዲሶ ሞኤቲ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ዳይሬክተሯ የአፍሪካ ሀገራት ብዙ የኮሮናቫይረስ ህሙማንን የማከም አቅም ስለሌላቸው፣ ከሕክምናው ይልቅ በመከላከል ላይ ትኩረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

የድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር አክለውም "በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት በቂ የጽኑ ህሙማን ሕክምና መስጫ መሣሪያዎች እንደሌሉ ስለምናውቅ፣ የጽኑ ህሙማን ክብካቤ ወደ መሻት ደረጃ የሚደርሱ ሰዎችን መጠን አነስተኛ ለማድረግ እንፈልጋለን" ሲሉ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#WHO

የኮሮና ቫይረስ ከዓለማችን ላይ እስከወዲያኛው ላይወደገድ እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

የዓለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ ህክምናዎች ዳይሬክተር ዶክተር ማይክ ረያን በትናንትናው እለት በሰጡት ማብራሪያ፥ ቫይረሱ የሚያበቃበትን ጊዜ መተንበይ ትክክል እይደለም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሁላችንም የኮሮናቫይረስ በዓለም ማህበረሰብ ዘንድ ሌላኛው ወረርሽኝ ሆኖ እስከወዲያኛው ሊቆይ ይችላል የሚለውን ከግምት ማስገባት አለብን ያሉት ዶክተር ረያን፥ ቫይረሱ እስከወዲያኛው አብሮን ሊኖርም ይችላል ብለዋል - #BBC

#AlJazeera
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#WHO

እንደ ዓለም ጤና ድርጅት (WHO) መረጃ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 183 ሺህ በላይ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል። ከእነዚህ መካከል ከ 50 ሺህ በላይ የሚሆኑት ከብራዚል የተገኙ ሲሆኑ ቀረዎቹ ከአሜሪካ እና ከሕንድ መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#WHO #DrTedrosAdhanom

የአስትራዜኔካ ክትባት የደም መርጋትን ስለማስከተሉ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ባለመኖሩ በዚህ ስጋት አገሮች ክትባቱን ከመስጠት መቆጠብ የለባቸውም ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

በትንሹ 5 የአውሮፓ ሀገራት አይስላንድ፣ ቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ክትባቱን መስጠት አቁመዋል ፤ ይህ የሆነ አንዲት የዳኒሽ ሴት ከደም መርጋት ጋር በተገናኘ እንደሞተች ከተነገረ በኃላ ነው።

ይህንን በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት በክትባቱ እና በደም መርጋት መካከል ምንም አይነት ግንኙነት የለም ብሏል።

እስካሁን ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጉ አውሮፓውያን የአስትራዜኔካ ክትባትን ወስደዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም በበኩላቸው ፥ እስካሁን በመላው ዓለም 335 ሚሊዮን በላይ የኮቪድ-19 ክትባት መሰራጨቱን የገለፁ ሲሆን እስካሁን ከክትባቱ ጋር በተገናኘ ምንም ሞት አለመመዝገቡን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#WHO : "አዲሱ ቫይረስ የኮቪድ-19 ክትባቶችን የመቋቋም አደጋን እያሳየ ነው፤ የበለጠ ለመረዳት ጥናቶች ያስፈልጋሉ"

"ሙ" የተባለ አዲስ ልውጥ የኮሮና ተዋህሲ መከሰቱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቀ።

ድርጅቱ «ሙ» በሚል በ12 ኛው የግሪክ ፊደል የሰየመውን የአዲሱን ልውጥ ቫይረስ ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል።

ድርጅቱ ፥ አዲሱ ልውጥ ቫይረስ በሳይንሳዊ መጠሪያው B.1.621 በመባል የሚታወቅ መሆኑን በትናንቱ የኮቪድ-19 ሳምንታዊ መግለጫ እመልክቷል።

አዲሱ ቫይረስ የኮቪድ-19 ክትባቶችን የመቋቋም አደጋን እያሳዬ መሆኑን የገለፀው ድርጅቱ፤ የበለጠ ለመረዳት ግን ጥናቶች እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥቶበታል።

ቫይረሱ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ በደቡብ አሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ተገኝቷል ተብሏል።

ከዚህ ቀደም ለልውጥ ቫይረሱ በግሪክ የመጀመሪያው እና የሁለተኛው ፊደል «አልፋ» እና «ቤታ»የሚል መጠሪያ መሰጠቱም ይታወሳል። #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia