TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AAWSA

አዲስ አበባ ከተማ ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውኃ አገልግሎት መቋረጡን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ።

በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ስራ ምክንያት 700 ሚሊሜትር ስፋት ያለው የውሃ መስመር ላይ ጉዳት በመድረሱ ነው ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት የተቋረጠው።

የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ግንባታን እያከናወነ ያለው የቻይናው #ሲሲሲሲ ስራ ተቋራጭ ለውሃ መስመሩ ጥንቃቄ ሳያደርግ የግንባታ ስራ ሲያከናውን ነው ውሃ በሚያስተላልፈው የውኃ መስመር ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡

በዚህም ጋንዲ ሆስፒታል ፣ አምባሳደር አካባቢ ፣ ቦሌ ሮድ እስከ ደንበል በአጠቃላይ ስታዲየም ዙሪያ ያሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት ተቋርጣል፡፡

መስመሩን ጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት ለማስገባት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጾ ደንበኞች በትግስት እንዲጠብቁ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT