#AAWSA
አዲስ አበባ ከተማ ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውኃ አገልግሎት መቋረጡን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ።
በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ስራ ምክንያት 700 ሚሊሜትር ስፋት ያለው የውሃ መስመር ላይ ጉዳት በመድረሱ ነው ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት የተቋረጠው።
የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ግንባታን እያከናወነ ያለው የቻይናው #ሲሲሲሲ ስራ ተቋራጭ ለውሃ መስመሩ ጥንቃቄ ሳያደርግ የግንባታ ስራ ሲያከናውን ነው ውሃ በሚያስተላልፈው የውኃ መስመር ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡
በዚህም ጋንዲ ሆስፒታል ፣ አምባሳደር አካባቢ ፣ ቦሌ ሮድ እስከ ደንበል በአጠቃላይ ስታዲየም ዙሪያ ያሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት ተቋርጣል፡፡
መስመሩን ጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት ለማስገባት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጾ ደንበኞች በትግስት እንዲጠብቁ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
አዲስ አበባ ከተማ ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውኃ አገልግሎት መቋረጡን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ።
በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ስራ ምክንያት 700 ሚሊሜትር ስፋት ያለው የውሃ መስመር ላይ ጉዳት በመድረሱ ነው ስታዲየም ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት የተቋረጠው።
የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ግንባታን እያከናወነ ያለው የቻይናው #ሲሲሲሲ ስራ ተቋራጭ ለውሃ መስመሩ ጥንቃቄ ሳያደርግ የግንባታ ስራ ሲያከናውን ነው ውሃ በሚያስተላልፈው የውኃ መስመር ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡
በዚህም ጋንዲ ሆስፒታል ፣ አምባሳደር አካባቢ ፣ ቦሌ ሮድ እስከ ደንበል በአጠቃላይ ስታዲየም ዙሪያ ያሉ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት ተቋርጣል፡፡
መስመሩን ጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት ለማስገባት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጾ ደንበኞች በትግስት እንዲጠብቁ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT