"...የሀሰት ወሬ ነው!" አቶ ንጉሱ ጥላሁን
"በብሄራዊ ምርጫ ቦርድና በጠ/ሚር አብይ አስተዳደር መሀል ውዝግብ ተፈጠረ" ብሎ Ethio 360 Media ያወጣውን ዘገባ ከእውነት የራቀ መሆኑን ምርጫ ቦርድ እና የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ገልፀዋል።
የምርጫ ቦርድ ቃል-አቀባይ #ሶልያና_ሽመልስ በጉዳዩ ላይ ለጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ተከታዩን ብለዋል፦
"እንዲህ አይነት ንግግር ምንም የለም፣ አልነበረምም። ሁለት አመት አራዝሙ የሚል ንግግር በመሀከላችን ሊኖር አይችልም። እኛ እንደውም የቀረበ እና ቀጥተኛ ግንኙነት ያለን ከፓርላማው እና ቋሚ ኮሚቴው ጋር ነው እንጂ ከስራ አስፈፃሚው ጋር አይደለም፣ ስለዚህ ሀሳቦች ቢመጡ እንኳን ከፓርላማው ነው እንጂ ከጠ/ሚሩ አይደለም።"
በተጨማሪ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየታቸውን የሰጡት የጠ/ሚሩ ቢሬ ፕረስ ሰክረታሪ አቶ #ንጉሱ_ጥላሁን ይህን ብለዋል፦
"ይህ የሀሰት ወሬ ነው። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ትናንት የወሰነውን ሁሉም ያቀዋል። ጠ/ሚር ቢሮ ምርጫ ይካሄድ ወይም አይካሄድ ብሎ አቅጣጫ አያስቀምጥም። መንግስት ምርጫ እንዲካሄድ እየተዘጋጀ ነው እንጂ እንዲራዘም አቅጣጫ እያስቀመጠ አይደለም።"
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በብሄራዊ ምርጫ ቦርድና በጠ/ሚር አብይ አስተዳደር መሀል ውዝግብ ተፈጠረ" ብሎ Ethio 360 Media ያወጣውን ዘገባ ከእውነት የራቀ መሆኑን ምርጫ ቦርድ እና የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ገልፀዋል።
የምርጫ ቦርድ ቃል-አቀባይ #ሶልያና_ሽመልስ በጉዳዩ ላይ ለጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ተከታዩን ብለዋል፦
"እንዲህ አይነት ንግግር ምንም የለም፣ አልነበረምም። ሁለት አመት አራዝሙ የሚል ንግግር በመሀከላችን ሊኖር አይችልም። እኛ እንደውም የቀረበ እና ቀጥተኛ ግንኙነት ያለን ከፓርላማው እና ቋሚ ኮሚቴው ጋር ነው እንጂ ከስራ አስፈፃሚው ጋር አይደለም፣ ስለዚህ ሀሳቦች ቢመጡ እንኳን ከፓርላማው ነው እንጂ ከጠ/ሚሩ አይደለም።"
በተጨማሪ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየታቸውን የሰጡት የጠ/ሚሩ ቢሬ ፕረስ ሰክረታሪ አቶ #ንጉሱ_ጥላሁን ይህን ብለዋል፦
"ይህ የሀሰት ወሬ ነው። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ትናንት የወሰነውን ሁሉም ያቀዋል። ጠ/ሚር ቢሮ ምርጫ ይካሄድ ወይም አይካሄድ ብሎ አቅጣጫ አያስቀምጥም። መንግስት ምርጫ እንዲካሄድ እየተዘጋጀ ነው እንጂ እንዲራዘም አቅጣጫ እያስቀመጠ አይደለም።"
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia