TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ልዩ_ዘገባ - ይነበብ⬇️

ቀደም ሲል ወደ ሀገር ቤት የገቡ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ድርጅቶች አመራሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ጉዳይ አስፈፃሚዎችን በዓየር ለማጓጓዝ ለሆቴልና ትራንስፖርት መንግስት ዳጎስ ያለ ወጪ ማውጣቱ ተሰምቷል።

ለግለሰቦቹ የየዕለት የሆቴል መስተንግዶና ሌሎች ወጪዎች ከዕለት ዕለት እየናረ መምጣቱን የሚናገሩት የመንግስት የሰራ ሀላፊዎች ወጪው ለሀገር ሰላምና ዕርቅ ሲባል የሚከፈል በመሆኑ ጉዳዩን መንግስት በሆደ ሰፊነት ሲመለከተው ቆይቷል።

አሁን ግን የወጪው መናር ያሳሰባቸው ሆቴሎች መንግስት ክፍያ እንዲፈፅም መጠየቃቸውንና እየቀረበ ያለው የገንዘብ መጠን አነጋጋሪ መሆኑን ለዋዜማ ራድዮ ቅርብ የሆኑ የአዲስ አበባ ምንጮች ተናግረዋል።

የገንዘብ ወጪውንና ምን ያህን እንግዶች በመንግስት መስተንግዶ እየተደረገላቸው እንደሆነ ራድዮ ጣቢያው የጠየቃቸው ምንጮዥ ሆቴሎች ሀገራዊ ፋይዳውን በመረዳት ቅናሽ ቢሰጡንም ተሰተናጋቾቹ በርካታ እንግዶች የሚጎበኟቸው በመሆኑና የቢሮ አገልግሎት የሚጠቀሙም ስላሉ ወጪውን ከፍ ማድረጉን አስረድተዋል። የገንዘቡን መጠን መናገር ግን እንደማይደፍሩ ተናግረዋል።

አሁን ቢያንስ ሀምሳ ሁለት ያህል እንግዶች በመንግስት እየተሰተናገዱ ሲሆን ከሶስት ወር እስከ አንድ ሳምንት የቆይታ ዕድሜ አላቸው።

አንዳንዶቹ ለጊዜው ከሆቴል ውጪ ዘመዶቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ጋር ይቆዩና ተመልሰው እንደሚመጡ አንዳንዶቹ ደግሞ አዲስ አበባ ቤተሰብ ስለሌላቸው በቋሚነት የሆቴሉ እንግዶች ሆነው ቀጥለዋል። የፀጥታ ጥበቃ የሚያስፈልጋቸውም ሆቴል መሆኑን እንደሚመርጡ ተሰምቷል።

በተያያዘ ዜና ከሰሞኑ ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱት የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች መንግስት ለጉዞና ለሆቴል ወጪያቸውን ለመሸፈን ያቀረበላቸውን ግብዣ ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ተሰምቷል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ጋር በአሜሪካ በነበረው ውይይት ወቅት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በአንድ አውሮፕላን መመለስ እንደሚችሉ የተነገራቸው የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች ማናቸውንም ወጪ ራሳቸው እንደሚችሉና ለመመለስ ዝግጅት እንደሚያሰፈልጋቸው ገልፀው የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይን ግብዣ ከምስጋና ጋር ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች በቀናት ጊዜ ውስጥ ወደ አዲስ አበባ ያቀናሉ። ለአቀባበሉም ዝግጅት እየተደረገ ነው። አመራሮቹ ወደ ሀገር ቤት ሲጓዙ ለብቻቸው አይደለም፣ ከፍ ያለ ቁጥር ያለው የድርጅቱ ደጋፊና አባል ከባህር ማዶ አብሮ ይጓዛል። በመላዊ ኢትዮጵያ ያሉ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች አዲስ አበባን ያደምቋታል። በክልል ከተሞችም የአቀባበል ስነስርዓት ይካሄል።

©WazemaRadio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ልዩ_ዜና ታንዛንያ⬇️

በታንዛንያ ደቡባዊ ክፍል የምቤዬ ግዛት ፖሊስ የአንድ ሰፈር ሰዎችን በሙሉ #በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ ሰዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ለአካባቢው የውሃ አገልግሎት ለመስጠት የተዘረጋውን የቧንቧ መስመር ከጥቅም ውጪ አድርገውታል በማለት ነው።

የእስር ትእዛዙን ያስተላለፉት የግዛቲቱ ፖሊስ ዋና ኃላፊ በበኩላቸው የሃገር ሃብት የፈሰሰበትን የውሃ መስመር በማበላሸታቸው ምክንያት በቁጥጥር እንደዋሉ ገልፀዋል።

በአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት የደረሰበት የውሃ አገልግሎት መስጫ በብዙ ሺ ዶላሮች ወጪ የተሰራ ሲሆን፤ እስካሁን የአካባቢው ተመራጭን ጨምሮ ብዙ የአካባቢው ነዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ግን ሁላችንም በጉዳዩ ስላልተሳተፍን የምርመራው ሂደት ንጹህ ሰዎችን እንዳያካትት እንሰጋለን እያሉ ነው።

ፖሊስ በበኩሉ ሁሉም የአካባቢው ነዋሪዎች ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ መገልገያዎችን የመጠበቅ ግዴታ አለባቸው ብሏል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ግን ይህንን ማድረግ ስላልቻሉ ለዚህ ውሳኔ እንደደረሰ ገልጿል።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ክቡር ዶክተር ለማ መገርሳ የ2010 ዓ.ም #የበጎ ሰው ሽልማት #ልዩ ተሸላሚ ሆነ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ለፈገግታ

ክቡር ዳኛ - አቶ አብዲ #መከላከያ ማቅረብ ይችላሉ?

አቶ አብዲ - አልችልም ክቡር ፍርድ ቤት #ልዩ_ኃይል ላቅርብ??

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ የአስተዳደር መዋቅር ጥናት⬇️

የደቡብ ክልል አዳዲስ #የዞንና #የወረዳ አወቃቀር ምክረ ሐሳብ የያዘ ጥናት አጠናቅቆ ለአመራሮች ውይይት እንዳዘጋጀ ታወቀ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) ሊቀመንበርና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወ/ሮ #ሙፈርያት_ካሚል ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ክልሉ አዲስ አወቃቀር እንደሚኖረው የመንግሥት አገልግሎትን ለወረዳ ማዕከላት ቅርብ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ እንዳለ ገልጸው ነበር፡፡

አፈ ጉባዔዋ በወቅቱ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፣ ‹‹በጥናት የተለየና ሕጋዊ ሥርዓቱን ተከትሎ ወደ ተግባር የሚገባበት የመዋቅር ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዝቡን ባወያየንበት ወቅት የነበረው ዋናው ጥያቄ የአገልግሎት ጥያቄ ነው፡፡ በጥናት አገልግሎት ወደ ኅብረተሰብ ማቅረብ አቅደናል፤››  ብለው፣ ‹‹በመንግሥታዊ መዋቅሩ ይኼንን በሕግ አግባብ ዳር ለማድረግ ምላሽ መስጠት ጀምረናል፤›› ሲሉም የደረሰበትን ደረጃ ማስረዳታቸው ይታወሳል፡፡

በዚህም መሠረት ካሁን በፊት #ልዩ ወረዳ የነበረው አላባ ወደ ዞንነት ሲያድግ ዌራ ዙሪያ፣ ድጆ ዌራና ድጆ የተባሉ ወረዳዎች ይኖሩታል፡፡ የወረዳዎቹ ማዕከላት በቅደም ተከተል ቁሊቶ፣ ጉባና የቤሻኖ ከተሞች እንዲሆኑ ጥናቱ ያሳያል፡፡

በሌላ በኩል ካሁን በፊት ከነበረው ጋሞ ጎፋ ዞን፣ ጎፋ ራሱን ችሎ በመውጣት ዞን በመሆን በሥሩ ስምንት ወረዳዎች እንዲኖሩት የሚል መዋቅር ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህም መሠረት ጎፋ ዞን ዲምባ ጎፋ፣ ባዜ ጎፋ፣ ዛላ፣ ኡባ ደብረ ፀሐይ፣ አይደ ወረዱ፣ ሳውላ ከተማ፣ መለኮዛና ጋደ የተባሉ ወረዳዎች እንዲኖሩት በጥናቱ ተመልክቷል፡፡

ለብቻው እንደ አዲስ የተዋቀረው ጋሞ ዞን ደግሞ 13 ወረዳዎች እንዲኖሩት እንደሚደረግ የሚጠቁመው ጥናቱ፣ አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ፣ ዲታ፣ ካምባ፣ ምዕራብ አባያ፣ ጨንቻ፣ ደራማሎ፣ ቁጫ፣ ቦንኬ፣ ቦረዳ፣ አርባ ምንጭ ከተማ፣ ምዕራብ ቁጫ፣ ሰሜን ቦንኬና ጋርዳ ማርታ የተባሉ ወረዳዎችን ያቀፈ ሆኖ እንዲቋቋም ሐሳብ ቀርቧል፡፡

በተመሳሳይ ኮንሶ ከሰገን ሕዝቦች ዞን ወጥቶ በዞንነት እንዲደራጅ በጥናቱ የተመለከተ ሲሆን፣ በሥሩም ካራት ዙሪያ፣ ከና፣ ሰገን ዙሪያና ካራት ከተማ አስተዳደር የሚሉ የወረዳ መዋቅሮች እንደሚኖሩት ተጠቁሟል፡፡

ጥናቱ ካሁን በፊት የሰገን ሕዝቦች ዞን አስተዳደር በሚል ስያሜ ተዋቅሮ የነበረው አደረጃጀት ወደ ቀድሞው ተመልሶ የአማሮ ልዩ ወረዳ፣ የቡርጂ ልዩ ወረዳ፣ የዴራሼ ልዩ ወረዳና የአሌ ልዩ ወረዳዎች ተብለው እንዲቋቋሙ የሚል ይዘት አለው፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ የኢህአዴግ ጉባኤ⬇️

ኢህአዴግ በ11ኛው ጉባኤው #በርዕዮተ_ዓለም ለውጥ ላይም ሆነ በአርማ ለውጥ ላይ #እንደማይወያይ ተገልጿል። የጉበኤውን ውሎ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የጉባኤው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንደገለፁት ጉባኤው አጀማመሩ ያማረና ከሌላው ጊዜ በበለጠ በርካቶችን ያሳተፈ ነበር ብለዋል።

የተፎካከሪ ፓርቲዎች መሳተፍ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ ሀገራትን የወከሉ የፓርቲ አመራሮችም በመክፈቻው መገኘታቸው ጉባኤውን #ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።

ጉባኤው ከመክፈቻ ፕሮግራሙ በኋላ በጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ የቀረበለት ሪፖርት ላይ መወያየቱን እና ይህ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

ጉባኤው በቆይታው የሚመክርባቸው በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በርዕዮተ ዓለም ለውጥም ሆነ በስምና አርማ ለውጥ ላይ እንደማይመክር ግን ቃል አቀባዩ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መልካም ተግባር🔝

#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ ላይ ተጠምደዋል።


#TIKVAH_ETH ~ የመከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል አባልት እየሰራችሁ ላለው መልካም ስራ ታላቅ #ምስጋና ያቀርባል!

ፎቶ፦ ሚኪያስ (ጅግጅጋ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 17/2011 ዓ.ም.

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
.
.
ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የዱባይ ማራቶን ጌታነህ ሞላ የቦታውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል። በሴቶች ኬንያውያን እኤአ ከ2006 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
.
.

አቶ #በረከት_ስምዖንና አቶ #ታደሰ_ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
.
.
#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ አከናውነዋል።
.
.
በነጭ ሣር ፓርክ ላይ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት እሳት ተነስቶ 1 ሺ ሄክታር የሚሆን የፓርኩ ክፍል ወድሟል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ #የተቀሰቀሰው_ተቃውሞ ዛሬ ጥር 17/2011 ዓ.ም. ቀጥሎ ውሏል። የኢንተርኔት አገልግሎት ተዘግቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2 ዙር በተካሄደ ነፃ የስራ ዘመቻ 3.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ስራ መሰራቱን ተናግሯል።
.
.
የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ100 ቀናት እቅዱን በአርባምንጭ ከተማ ገምግሟል።
.
.
በሱማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት እጃቸውን በማስገባት ወንጀል ሰርተው ከሀገር የወጡ ባለስልጣናትን ወደሀገር #በመመለስ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከተሸሸጉባቸው ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታውቋል።
.
.
በሳኡዲ አረቢያ በተለያየ ምክንያት ታስረው የነበሩ 368 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ገብተዋል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የሕዝቡን አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
.
.
በኢትዮጵያ #የመጀመሪያ የሆነ የሚዲያ ኤክስፖ በኤግዚብሽን ማዕከል ዛሬ ተከፍቷል።
.
.
የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ አቶ #ጌታቸው_አሰፋን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከክልሉ መንግሥት ጋር እየሰራ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።
.
.
በጉጂ ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/አባላት ከጫካ ወጥተው #በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰናቸውን ገልፀዋል።
.
.
የሱማሌ ክልል መሪ--አቶ #ሙስጠፋ_ኡመር-የፌዴራል ገንዘብ ሚኒስትሩን አቶ #አህመድ_ሺዴን-በይፋ በክልሉ መንግስት ላይ "ዓመፃ-ክህደት በመፈፀም" እጅግ ከባድ ወንጀል #ከሰዋል

ምንጭ፦ አዲስ ስታንዳርድ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ elu፣ ቢቢሲ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

.
.
አመሰግናለሁ! ሰላም እደሩ!!
ሀገራችን ቸር ትደር!!
ጥር 17/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሚመለከተው...

በዳንጉር ወረዳ እንዲሁም ጃዊ አካባቢዎች አሁንም የፀጥታ መደፈረስ እንዳለ በአካባቢው የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል። በአካባቢዎቹ የሚስተዋለው የፀጥታ መደፍረስ #ልዩ_ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባና ጉዳት ከደረሰ በኃላ ለማረጋጋት ከመሯሯጥ ቅድሚያ የመከላከል ስራ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ወንጀለኞችም በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቴፒ ነገር... TIKVAH-ETHIOPIA ከቴፒ ከተማ ነዋሪ ቤተሰቦቹ መልዕክቶችን እያስተናገደ ነው። ከተማይቱ አይሁንም ቢሆን አስተማማኝ ደህንነት የላትም፤ መንግስት ኃይሉን አጠናክሮ ሰላምና ደህንነትን ማስጠበቅ አለበት ብለዋል። በተለይም የከተማው መግቢያና መውጫዎች ላይ ከፍተኛ ወንጀሎች እንድሚፈፁ ገልፀዋል። "ከቴፒ ነው የምጽፍላቹ! N ነኝ ቴፒ ነዋሪ ነኚ ቴፒ ላይ ከአቅም በላይ የሆነ ነገር አለ።…
#ቴፒ

"ከቴፒ የጻፍኩላቹ የናንተው ቤተሠብ ነኝ። ለ8 ቀን ተዘግቶ የነበረው የቴፓ መናህሪያ በመከላከያዎች ጥረትና አወያይነት ዛሬ ለመንገደኞች ክፍት ሁኖ እኛም መከላከያ ጫካውን አጅቦን ሸኚቶን ከቴፒ #ሚዛን ገብተናል መንገደኞችም ዛሬ ማንም ሣይዘረፍ ወደሚዛን ገብተናል! እድሜ ለፌደራልና ለመከላከያዋቹ ሁሉንም አመሥግኑልን የናንተው ቤተሠብ ከሚዛን ቴፒ!"

እኛ ደግሞ ይህን እንላለን...

የኢትዮጵያ መንግስት ለአካባቢው #ልዩ_ትኩረት ሰጥቶ ችግሮች በዘላቂነት የሚፈቱበትን መንገድ መፈለግ አለበት፤ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ላይ #ደህንነታቸው ተጠብቆ እንደልባቸው ወጥተው የሚገቡበትና ስራቸውን ያለእክል የሚሰሩበትን ሁኔታ መፍጠር ትልቁ የመንግስት ስራ በመሆኑ በተቻለ አቅምና ፍጥነት ይህን ማድረግ ይኖርበታል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ልዩ_ዕቃ

GRINDER Machine (የቡና እና የቅመማ ቅመም መፍጫ)
🚩እጅግ በጣም ጠንካራ
🚩ለደረቅ ቅመማ ቅመሞች የሚሆን
🚩ሙሉ ለሙሉ ብረት (Stainless steel)
🚩የራሱ መለዋወጫ ጥርስ ያለው
100 ግ = 2800 ብር
200 ግ = 3999 ብር
400 ግ = 5800 ብር
500 ግ = 6800 ብር
1000ግ= 9600 ብር

 ቴሌግራም ቻናል👉 @LeyuEka

ያሉበት ድረስ በነፃ እናደርሳለን 0944109295 @Le_Mazez
0933334444 @LeMazez_z
0946242424 @Le_Mazez
#ልዩ_ዕቃ

2 in 1 Hobby Lobby Brand የጁስ Juice እና የቡና መፍጫ የጉልበት መጠኑ አስተማማኝ የሆነ  ዕቃ ፤ ዋጋ 2600 ብር ብቻ ከነፃ ዲሊቨሪ ጋር እና ከዋስትና ጋር ቴሌግራም ቻናል @LeyuEka

👉 2 ዕቃ ከ1 ሺ ብር በላይ የሚተመኑ ዕቃዎች ሲገዙ ስጦታ🎀 አዘጋጅተናል
   0933334444 @LeMazez_z
   0944109295 @Lemaze_z
   0946242424 @Le_Mazez

አድራሻ
⭕️ቁጥር 1 ልደታ ወደ ባልቻ ሆስፒታል ገባ ብሎ  አህመድ ህንፃ ላይ 1ኛፎቅ 105B
⭕️ቁጥር 2 __ 22 ጎላጎል ህንፃ አጠገብ
የ NOAH ህንፃ ግራዉንድ የሱቅ ቁጥር  G 15 ልዩ ዕቃ የሚል ይደዉሉልን👆
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ60 በላይ የጤና ባለሙያዎች ፤ " ጤና ሚኒስቴር በሕግ የተወሰነልንን ልዩ አበል አልከፈለንም " አሉ። የጤና ባለሙያዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት፤ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ / ም መከሰቱን ተከትሎ የጤና ማኒስቴር ባወጣው ጥሪ መሠረት የኢፌደሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ግንቦት 18 ቀን 2012 ዓ / ም ባወጣው መመሪያ የሕክምና አገልግሎት ለሚሰጡ ለመላው ሀኪሞች በቀን…
#ጤና_ሚኒስቴር #ክስ

የፍርድ ቤት ውሳኔን በተደጋጋሚ ጣሰ የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " ለ70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ -19 ልዩ አበል እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ አስተላለፈበት።

70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ ወረርሽኝ #ልዩ_አበል እንዲሰጣቸው በመሰረቱበት ክስ መሠረት ገንዘቡን እንዲከፍል ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በተደጋጋሚ ጥሷል የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " አሁንም ከንግድ ባንክ አካውንቱ #እየቆረጠ_እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጤና ባለሙያዎቹ ገለጻና ከተጻፈው ደብዳቤ መረዳት ችሏል።

የጤና ባለሙያዎቹ ተወካይ የፍርድ ሂደቱ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

* ፍርድ ቤት ለባንክ ሲያዝ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

* የፋይናንስ ክፍሉ ኃላፊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ድክመት ለፍርድ ቤት #ታስረው ቀርበው እንዲያስረዱ ቢታዘዝም ጉዳዩን እንዲያስፈፅም የታዘዘው የፌደራል ፖሊስ መስሪያ ቤቱ ድርስ በመሄድ ቢጠይቅም እረፍት እንደወጡና እስከ ሰኞ (ያለፈው ሳምንት ሰኞ) እንደሚመጡ አሳውቀው ነበር። ከዚያ በኋላም ፍርድ ቤት መጥተው አያውቁም።

* ታስረው እንዲቀርቡም #ከሁለት_ጊዜ_በላይ ነው የታዘዘው።

* ፍርድ ቤት በራሳቸው እንዲፈፅሙ ግን በተደጋጋሚ (ከአምስት ጊዜ በላይ) ትዛዝ ሰቶ ነበር።

* ሰዎቹ በፍፁም ለህግ ተገዢ አለመሆናቸውን እና እምቢተኝነታቸውን በተደጋጋሚ ጊዜ አሳይተውናል።

* ለፍርድ ቤት ውሳኔ ያላቸው ንቀት በቃላት የሚገለፅ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ይሄንን የጤና ባለሞያዎች መረጃ በማደራጀት ሂደት የጤና ሚኒስቴርን ምላሽ እና ማብራሪያ ለማካከት ብዙ ቢደክምም ምላሽ ሰጪ አላገኘም።

አሁንም #በአካልም ይሁን #በስልክ ምላሽ ሰጣለሁ የሚል የሚኒስቴር መ/ቤቱን አካል ለማስተናገድ ዝግጁ ነው።

ዝርዝሩን ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-14

የመረጃው ዝግጅት በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ?

በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።

አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።

ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።

በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።

ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።

በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።

ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።

ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።

የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።

በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።

ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።

የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል  ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።

#ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ 

የብርሃን ባንክ #ልዩ_የኤቲኤም_ካርድ
👉 የካርድ አዘጋጁልኝ ጥያቄውን ባቀረቡበት ቅፅበት ማግኘት የሚችሉት
👉 ደንበኞች ለረዥም ጊዜያት ኤቲኤም ካርድ ለማግኘት የሚያባክኑትን ጊዜ ያስቀረ
👉 የሚስጥር ቁጥሩ ከወረቀት ነጻ ሆኖ በእጅ ስልክዎ ብቻ የሚደርስዎት
👉 የሚስጥር ቁጥርዎ ለሌላ ሰው እንዳይጋለጥ በማድረግ ደህንነቱ የተረጋገጠ
ወደ ቅርንጫፎቻችን ጎራ ይበሉ ፈጣኑን #ልዩ_የኤቲኤም_ካርድ ይውሰዱ!
#liyuatmcard #atmcard #berhanbank #bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia

ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook       ➡️ Telegram
➡️ Instagram      ➡️ Twitter
➡️ LinkedIn         ➡️ YouTube
#ብርሃን_ባንክ
በብርሃን ቅፅበት ካርድዎን በእጅዎ ያስገቡ!

#ልዩ_የኤቲኤም_ካርድ #liyuatmcard #atmcard #berhanbank #bank #finance
#Stressfreebanking #bankinethiopia

ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube