TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቅዳሜ እና እሁድ ኢትዮጵያችን!
-------
🔹ነገ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት #በመቀለ_ከተማ የድጋፍ ሰልፍ አዘጋጅቷል።

🔹ኢሕአፓ የተመሰረተበትን 46ኛ አመት ነገ ከቀኑ 8 ሰዐት በአዲስ አበባ #ዋቢሸበሌ ሆቴል ያከብራል።

🔹ሕገ መንግስቱ የጸደቀበት ቀን/የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ነገ በአዲስ አበባ ከተማ ይከበራል።

🔹ዜጎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴና #የጤና ምርመራ እንዲያደርጉ ለማነቃቃት እሁድ በአዲስ አበባ የተወሰኑ መንገዶች ከትራፊክ እንቅስቃሴ ነፃ ይሆናሉ።

ምንጭ፦ elu
@tsegabwolde @tikavhethiopia
ጥብቅ ማሳሰቢያ!

#ሼር #share

#ከህሙማን ጋር ግንኙነት ባለው #የጤና የትምህርት ዘርፍ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በማታ፣ በቅዳሜና እሁድ ማስተማር እንደማይቻል የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የጤና_ሚኒስቴር_ማስጠንቀቂያ !

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ፥ የኮቪድ-19 ክትባትን ከመንግስት የጤና ተቋማት ውጪ የሚሰጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ።

በሚኒስቴሩ የብሄራዊ ክትባት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ላቀው ፥ የኮቪድ 19 ክትባትን በግል እያስከፈሉ የሚሰጡ አካላት ህገ ወጥ በመሆናቸው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ህብረተሰቡም ይሄንን ተከትሎ ራሱን ለአደጋ ማጋለጥ እንደሌለበት ተናግረዋል።

አቶ ዮሃንስ ክትባቶቹ በእርዳታ የገቡ መሆናቸውን አስታውሰው፣ ለህብረተሰቡ በመንግስታዊ ጤና ተቋማት ብቻ በነፃ የሚሰጡ ሆነው ሳለ ክፍያ እየተጠየቀ እንደሚሰጥ ሰምተን እያጣራን ነው ብለዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በህገ ወጥ መንገድ ክትባቶቹን ለመገበያየት መሞከር በአያያዙና በአወሳሰዱ ላይ እክል የሚፈጥር በመሆኑ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

እስካሁን ለየተኛውም የግል ተቋም የኮቪድ 19 ክትባትን መስጠት እንዲችል ያልተከፋፈለ መሆኑንና ፈቃድም እንዳልተሰጣቸው በማሳሰብ ለወደፊት በግል ጤና ተቋማት መሰጠት ሲጀመር ቀድመን የምናሳውቅ ይሆናል ብለዋል። እስካሁን ግን ክትባት እንዲሰጥ ፈቃድ የተሰጠዉ የግል የህክምና ተቋም የለም ሲሉ አስገንዝበዋል።

መረጃው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፈረንሳይ iPhone 12ን አገደች። ፈረንሳይ iPhone / አይፎን 12 ከልክ በላይ ጨረራ ያመነጫል በሚል የስልኩ ሽያጭ እንዲታገድ አዘዘች። ትናንት መስከረም 1/2016 ዓ.ም. የሬዲዮ ሞገዶችን የሚቆጣጠረው አካል አይፎን 12 ከሚፈቀደው የኤሌክትሮማግኔቲክ ራዲዬሽን በላይ እያመነጨ ነው ብሏል። ተቋሙ ስልክ አምራቹ አፕል ችግሩን በሚያደርጋቸው ማሻሻያዎች በአስቸኳይ የማይቀርፍ ከሆነ በመላው አገሪቷ…
#ቴክኖሎጂ #iPhone

ፈረንሳይ " አይፎን 12 " ን ከልክ በላይ ጨረራ ያመነጫል በሚል የስልኩ ሽያጭ እንዲታገድ ማዘዟን ተከትሎ የአውሮፓ ሀገራት ጉዳዩን እየተከታተሉ ነው ተብሏል።

ፈረንሳይ አይፎን 12ን ያገደችው ከሚፈቀደው የኤሌክትሮማግኔቲክ ራዲዬሽን በላይ እያመነጨ ነው በማለት ሲሆን ይህን እገዳ ተከትሎ ፦
- ቤልጂየም፣
- ኔዘርላንድስ
- ጀርመን ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ እየተከታተሉት ነው ተብሏል።

የጀርመን ባለሥልጣናት ሁኔታው ወደ አውሮፓ አቀፍ እርምጃዎች ሊመራ ይችላል ብለዋል።

የቤልጂየም መንግስት እ.ኤ.አ. በ2020 ለመጀመሪያ ጊዜ የተለቀቀው አይፎን 12 #የጤና_ጠንቅ መሆኑን እንዲገመግም ለተቆጣጣሪ አካል መመሪያ መስጠቱ ተነግሯል።

የቤልጂየም የዲጂታላይዜሽን ሚኒስትር ማቲዩ ሚሼል ፤ " ዜጎቻችን በሙሉ ደህንነታቸው የተጠበቀ እና ከማንኛውም አደጋ የተጠበቁ እንዲሆኑ ማድረግ የእኔ ኃላፊነት ነው። ጤና መቼም ቢሆን ችላ ሊባል የማይገባ ጉዳይ ነው። " ብለዋል።

ሁሉም የአፕል ሞዴሎችን እንዲመረምር ተቆጣጣሪውን አካል እንደተጠየቀ አመልክተዋል። ሌሎችም ብራንዶች ላይ ተመሳሳይ ስራ ይሰራል ብለዋል።

የኔዘርላንድ ዲጂታል መሠረተ ልማት ኤጀንሲ ፤ በፈረንሣይ ምርመራ ላይ በመመርኮዝ ከልክ በላይ የጨረር መጠን እንደሚያመነጭ ጥርጥር የለውም ያለ ሲሆን አፕልን እንደሚያነጋግር አሳውቋል።

ነገር ግን “ ምንም አጣዳፊ የደህንነት ስጋት የለም ” ብሏል።

የጀርመኑ BNetzA ኔትወርክ ኤጀንሲ ፤ የፈረንሣይ ምርመራ በሁሉም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ላይ የሚተገበሩ እርምጃዎችን ሊያስወስድ የሚችል ነው ብሏል።

አፕል የፈረንሳዩን እገዳ ከሰማ በኃላ ለቢቢሲ በሰጠው ቃል ፤ አይፎን 12 የጨረራ መጠኑ በሰዎች ላይ ጉዳት እንደማያስከትል በመላው ዓለም ባሉ ተቆጣጣሪዎች እውቅና ያለው ምርት ነው ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

በሌላ መረጃ ፤ አፕል አዲሱን " አይፎን 15 "  ከነገ ጀምሮ ማዘዝ እንደሚቻል አሳውቋል።

አዲሱ ምርት እንደየአይነቱ በተለያየ የገንዘብ መጠን ለገበያ ቀርቧል።

አይፎን 15 በስንት ዶላር ነው ለገበያ የቀረበው ?

👉 አይፎን 15 ከ$799 እስከ $1,099 (በኢትዮጵያ ብር በባንክ ቢሰላ ከ44,952 ብር እስከ 61,830 ብር ይሆናል)

👉 አይፎን 15 ፕላስ ከ$899 እስከ $1,199 (በኢትዮጵያ ብር በባንክ ቢሰላ ከ50,578 ብር እስከ 67,456 ብር ይሆናል)

👉 አይፎን 15 ፕሮ ከ$999 እስከ $1499 (በኢትዮጵያ ብር በባንክ ቢሰላ ከ56,204 ብር እስከ 84,335 ብር ይሆናል)

👉 አይፎን 15 ፕሮ ማክስ ከ$1,199 እስከ $1,599 (በኢትዮጵያ ብር በባንክ ቢሰላ ከ67,456 ብር እስከ 89,961 ብር ይሆናል)

ገንዘቡ #ዝቅተኛው እና #ከፍተኛውን ጣሪያ የሚያሳይ ሲሆን እንደ ስልኩ GB እና አይነት ይለያያል።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

" በምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል " - የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፦
° 65 በመቶ የሚሆን #ገዳይ የወባ ዝርያ እንዳለ፣
° በአንድ ዓመት ውስጥ 101 ሰዎች በወባ እንደሞቱ፣
° ማኅበረሰቡ ወደ ሕክምና ተቋማት እንዲሄድና አጎበር የመጠቀም ልምዱን እንዲያዳብር የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ተስፋፅዮን ተረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኩፍኝ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?

* ምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት 3 ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል። በክልሉ በአንድ ዓመት ውስጥ 12,700 የኩፍኝ ኬዞች ተገኝተዋል። 

* ከሌሎች ቦታዎች በተለዬ መልኩ በምዕራብ ኦሞ ዞን አሁንም ከፍተኛ ሥራ የሚጠይቅ የኩፍኝ ወረርሽኝ ስርጭት አለ። በመቀጠልም በቤንቺ ሸኮና ከፋ ዞኖች በተወሰኑ ወረዳዎች ይስተዋላል።

* አርሶ አደሮች በሚኖሩባቸው ( #በተለይም ምዕራብ ኦሞ)፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የክትባት አሰጣጡን አፌክት ያደርገዋል።

* #አርሶ_አደሮች ባሉባቸው አካባቢዎች ላይ ችግሩ እንዲቀረፍ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በአካባቢው ተንቀሳቀሰው ሕክምና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው።
 
* የኩፍኝ ኬዞች ያሉባቸው አራት ዞኖች ናቸው። ቤንቺ ሸኮ ዞን ላይ ወደ 3,000፣ ከፋ ዞን ከ1,000 በላይ ኬዞች ነበሩ ፤ አሁን መቆጣጠር ተችሏል።

* ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ለማድረግ ጤና ሚኒስቴር ፈቅዷል። ከአምስት ዓመት በታች ለሚሆኑ ሕፃናት ክትባት ይደረጋል።
 
ወባ በምን ደረጃ ይገኛል?

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃልፊ አቶ ኢብራሄም ተማሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦

- ለሁለት ዓመታት #የወባ_ወረርሽኝ በክልሉ ተከስቶ ቆይቷል። የኩፍኝ ወረርሽኝም በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ልዩ ትኩረት ይሻል። ከእስከዛሬው ጋር ሲነጻጸር ግን ኬዞቹ እየቀነሱ ነው። ግን አሁንም ሥራ ይጠይቃል።

- የወባ ወረርሽኝ ቆዬ ስንል በርካታ ሥራዎችን ሰርተናል ከወባ ጋር ተያይዞ ወደ 1.2 ሚሊዮን የአጎበር ስርጭት ተካሂዷል። ከ6,000 ኪ.ግ በላይ እርጭት ተካሂዷል።

- አሁንም ውሃ ያቆሩ ቦታዎች ላይ እርጭት እያካሄድን ነው ፤ በጣም በተለየ መንገድ ምዕራብ ኦሞ ላይ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ያለው ግብዓት አሰራጭተን የመከላከሉን ሥራ እየሰራን ነው።

አቶ ተስፋፅዮ በበኩላቸው ስለ ወባ ምን አሉ ?

* የተወሰኑ ወረዳዎችን ላያካትት ይችል ይሆናል እንጂ ሁሉም  ዞኖች በጣም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው ናቸው።

* በአመት ውስጥ #በ6_ዞኖች በወባ ወደ 101 ሞት ተመዝግቧል። አሁን ግን ማኅበረሰቡ  በአቅራቢያቸው ህክምና እያገኙ ስለሆነ የህመም (የኬዝ)፣ የሞት መጠኑ በዛው ልክ ቀንሷል።

* ላለፉት ሁለት ዓመት ለዚህ መንስኤ የሆኑ ጥናቶች ለማድረግ ሞክረናል፣ የምላሽ ሥራው ተሰርቷል።

* እስካሁን ባለው በአጠቃላይ ወደ 400,054 ሰዎች በአንድ ዓመት የወባ አይነቶች ተለይተው ህክምና ያገኙ ናቸው።

* በተሰሩ ሥራዎች በተለይ ከአራት ወራት በፊት እስከ 15,000 ሰዎች በወባ ይጠቁ ነበር። አሁን ባለንበት በሳምንት በወባ የመጠቃቱ ሁኔታ ከ7,000 እስከ 6,000 ሰዎች ዝቅ ለማድረግ ተችላል።

* በመከላከል ላይ ያለ ክፍተት ነው የወባ ቁጥር ከፍ ብሎ እዲታይ እያደረገ ያለው። ምዕራብ ኦሞ ፣ ካፋ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች ላይ አርብቶ አደሮች ናቸው በተለይ ተጋላጭ የሆኑት።

* ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሆስፒታል ድረስ የወባ ህክምና አለ።

* ሞት እያስከተለ ያለው ቆይተው ስለሚመጡ ነው። ቆይተው ሲመጡ ደግሞ በክልላችን #ከ65 ፐርሰት በላይ ፋልሲፋረም የሚባል በባህሪው #ገዳይ የሆነ ዝርያ ነው ያለው።

* በእኛ ክልል ላይ የሚበዛው ያ " ፋልሲፋረም " ነው። ሰዎች ወዳውኑ ምልክቱን እንዳዩ የመወሳሰብ ደረጃ ላይ ሳይደርስ ወደ ጤና ተቋማት ሂደው መታከም አለባቸው። ችግሩ ሲወሳሰብ ደም ሊፈልግ ይችላል፣ #ነፍሰ ጡሮችን በተለይ ወዲያው የመግደል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

ለ2ቱም ወረርሽኞች ለሞት አደጋው መከሰት ምክንያቱ ፦

° የሕሙማን ወደ ሕክምና #ዘግይቶ መምጣት፣

° #የጤና_ኤክስቴንሽኖች ወረርሽኝ አካባቢዎች ላይ አክቲቭ አለመሆንና በወቅቱ ለይቶ አለመላክ ነበር።

* በዘላቂነት ችግሮቹን ለማስወገድ ክልሉ የንቅናቄ መድረክ እንያዘጋጀ ነው። አሁንም ዝናብ ወጣ እየገባ እያለ ስለሆነ ለወባ መራባት እጅግ በጣም ምቹ አጋጣሚ ስለሚፈጥር ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደግ ይገባል።

ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EMA ከ600 በላይ የሕክምና ባለሙያዎችና ውሳኔ ሰጪዎች ውይይት ሊያደርጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕክምና ማኀበር ገለጸ። የማኀበሩ ራዕይ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ማግኘት የሚችል ጤናማና የበለጸገ ማህበረሰብ እውን ለማድረግ ይረዳ ዘንድ ከሚመለከታቸው የመንግሥት መ/ቤቶች የጤና ሚኒስትርን ጨምሮ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ ከስፔሻሊቲ ሶሳይቲዎች፣ ከማኀበሩ አባላት ጋር በመሆን ምክክር የሚያደርግበት ዓመታዊ…
#EMA

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ አባል ፤ ከኢትዮጵያ ሕክምና ማኀበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ትዕግስት መኮንንን ጋር ቆይታ  አድርጎ ነበር።

በዚህም ወቅት መሰረታዊ የሚባሉ ጥያቄዎችን አንስቷል።

1ኛ. በጤና ተቋማት እየታዩ ያሉና ትኩረት የሚሹ ችግሮች ምንድን ናቸው ?

ወ/ሮ ትዕግስት መኮንን ፦

" አሁን በስፋት በዋነኝነት እንደተግዳሮት ሆኖ የሚታየው የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት መኖር ነው።

የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት በሚፈለገው ልክ ተቋማት  የሚጠበቅባቸውን ሥራ ለመስራት ትልቅ ተግዳሮት እየሆነ ነው። "

2ኛ. ማህበሩ #የጤና_ባለሙያዎችን ጉዳዮች ተደራሽ ማድረግ አንዱ ዓላማው እንደመሆኑ መጠን በደመወዝ እጥረት የጤና ባለሙያዎች ወደ ውስጥም ሆነ ውጪ አገራት እየፈለሱ (የትግራይ ክልል) መሆኑን በተመለከተ ማኅበሩ እንደማኀበር ምን እየሰራ ነው ?

ወ/ሮ ትዕግስት መኮንን ፦

" እርግጥ ነው ይሄ ነገር ማኀበሩ እውቅና የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከሥራ ማጣት ጋርም ተያይዞ፣ ከተለያዩ ችግሮች አንፃር የባለሙያዎች ፍልሰት እንዳለ እሙን ነው። ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ እንደዚህ ነው የሚል ጥናታዊ ፅሑፍ አልሰራንም።

ግን ችግሩ እንዳለ፣ በጥልቀት አትኩሮት መሰጠት እንዳለበትም ለተለያዩ አካላት ግብዓት ስንሰጥ ቆይተናል።

ይሄ አገሪቱም ካለችበት የኢኮኖሚ ጉዳይ፣ ለጤና ሴክተሩ ከሚሰጠው ትኩረት አንፃር እጥረት አለ፣ መድረስ ያለብን ደረጃ ላይ አልደረሰንም። ይህ ባለበት ሁኔታ የመፍለሱ፣ ሥራ የማጣቱ ጉዳይ እየታዬ ስለሆነ እንደ አገር ያለው ችግር ነው ለዚህ የዳረገው። "

3ኛ. የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ጤና ተቋማት የሚሄዱ ሕሙማን መጉላላት፣ የቀጠሮ መንዛዛት ስለሚገጥማቸው በወቅቱ መታከም ሲገባቸው ከሕመማቸው ጋር ለመቆየት እንደሚገደዱ ሕሙማን በተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያነሱ ይደመጣል። ይህን ጉዳይ በተመለከተ ማኀበሩ ምን እየሰራ ነው ?

ወ/ሮ ትዕግስት መኮንን ፦

" የታካሚዎች መጉላላት፣ በወቅቱ የሚፈለገውን የሕክምና አገልግሎት አለማግኘት አጠቃላይ የሥርዓት ችግር ቢሆንም፣ ችግሩን ምን አመጣው ? በሚለው ጉዳይ ብዙ ነገሮች ሊጠቀሱ ይችላሉ።

ለምሳሌ፦ የሕክምና መሣሪያዎች ግብዓት እጥረት መኖር፣ ለጤና ሴክተር የሚሰጠው የበጀት እጥረት፣ ከዶላር ጋር ተያይዞ ያለው ችግር በቀጥታ ለዚህ ችግር አስተዋጽኦ ያደርጋል።

ቁጥሩን ለመግለጽ ለጊዜው ባላስታውሰውም ማህበረሰቡ የጤና አገልግሎት ፍላጎቱ እየጨመረ መጥቷል።

እንደ አጠቃላይ በታካሚዎች፣ በሐኪሞች፣ በዘርፉ ያለውን ክፍተት ለመሙላት የሚያስችል ውይይት የማኀበሩ 60ኛ ዓመታዊ ጉባኤ በዚህ ወር ሲደረግ ይነሳል። ይበልጥ ትኩረት ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። "

#TikvahEthiopiaAA

@tikvahethiopia
#ጎጆብሪጅ #ጤናባለሙያዎች

➡️ " ውላችን ይቋረጥ ፣ #ገንዘባችንም_ይመለስልን ብለው የፈረሙ 4,000 ቆጣቢዎች አሉ " - የቤት እጣ ቆጣቢዎች

➡️ " ከጤና ሚኒስቴር፣ ከዳሽን ባንክ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስላለን ተመካክረን መልስ እንሰጣለን " - ጎጆ ብሪጂ

ከ7 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ #የጤና_ባለሙያዎች ቤት ገንብቶ ለማስረከብ ከጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከዳሽን ባንክ የሦስትዮሽ ውል የፈረመው ጎጆ ብሪጂ ሀውሲንግ ፦
➡️እጣውን በወቅቱ እያወጣ ባለመሆኑ፣
➡️እጣ የወጣላቸውም ግንባታ ባለመጀመሩ፣ 4,000 ቆጣቢዎች ገንዘባቸው እንዲመለስ ቢጠይቁም እንዳልተመለሰላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አሁንም ቢሆን ገንዘቡ እንዲመለስላቸው ጠይቀዋል።

የቆጣቢዎቹ ኮሚቴ በጉዳዩ ዙሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ " በየሶስት ወሩ ለማውጣት እጣው ሳይሰጥ 2 ዙር አልፏል። ለምን ? ተብለው ሲጠየቁ ' #የመሬት_አስተዳደር_ችግር_ስላለብን_ነው ' እያሉ እስካሁን ቆዩ " ብሏል።

" ውላችን ይቋረጥ ፤ ገንዘባችንም ይመለስልን ብለው የፈረሙ 4,000 የቤት ቆጣቢዎች አሉ " ሲል የገለጸው ኮሚቴው በደብዳቤ ጭምር ቢጠይቅም መፍትሄ እንዳልተሰጠው አስረድቷል።

ለተነሳው የቤቶች እጣ መዘግየት ቅሬታ በ ' ጎጆ ብሪጅ ሃውሲንግ ' በኩል ምላሽ እንዲሰጡን የተጠየቁት አቶ አልማው ጋሪ ፤ " የገጠመን ችግር በአደረጃጀት ላይ #መዘግየቶች ስለነበሩ ነው " ብለዋል።

" የሚያደራጀው የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን የሚባለው ነው " ያሉት አቶ አልማው፣ " ሌላ ሳይት ላይ በተፈጠረ ክስ ትንሽ ሥራው ስለቆመ እስኪ ውጤቱን እንየው የሚል ሀሳብ ተነስቶ ስለነበረ የመዘግየት ጉዳይ አጋጥሟል " ነው ያሉት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ የቤት ቆጣቢዎቹ ከጠየቁ ለምን ገንዘባቸውን አልመለሳችሁም ? ሲል ላቀረበው ጥያቄ ፣ " ውሉ የሚያስቀምጣቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ይህን ደግሞ ለብቻችን ሳይሆን ከጤና ሚኒስቴርም ከዳሽን ባንክም ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስላለን ተመካክረን መልስ እንሰጣለን " ብለዋል።

" የመጀመሪያው እጣ ማውጣት ተደርሶ ወደ 300 ሰዎች እጣ የደረሳቸው አሉ። እነርሱን ለማደራጀት በሂደት ላይ ነው ያለነው " ያሉት አቶ አልማው " አንዳንዶች ደግሞ ቅሬታ አላቸው እየመጡ ይጠይቃሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

" የቅሬታ አቅራቢዎቹን ጉዳይም ባለፈው ሳምንት ጤና ሚኒስቴር የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ተደርጎ አቀረቡ አቅጣጫ ተቀምጧል። ምናልባት በዚህ ሳምንት አንድ ደረጃ ላይ ይደርሳል " ብለዋል።

#TikvahEthinpiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት እነ ቀሲስ በላይ መኮንን ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ አዟል። በዋስ ጥያቄያቸው ዛሬም ውድቅ ተደርጓል። ቀሲስ በላይ መኮንን በችሎቱ ፥ " ፖሊስ ይዞኝ ሳይሆን እራሴ ነው የሄድኩት " ብለዋል፡፡ " #ብዙ_የሀገር_ጉዳይ በእጄ ስላሉ ጥፋ ብባል እንኳ የምጠፋ ስላልሆንኩ ፤ በጤናዬ ላይ በደረሰው እክልና በቤተሰቦቼ ላይ በደረሰው…
#Update

ከ 'አፍሪካ ህብረት' የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ በ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር የምዝበራ ሙከራ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ የጠየቁት ዋስትና ውድቅ ተደርጓል።

ጥያቄውን ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ከምዝበራ መኩራው ጋር በተያያዘ የተከሰሱት ፦

1ኛ. ቀሲስ በላይ መኮንን፣
2ኛ. በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ ወ/መስቀል፣
3ኛ. በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ ጃፋር፣
4ኛ. አለምገና ሳሙኤል ዲንሳ
5ኛ. የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ ተስፋዬ ናቸው።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያሉ ተከሳሾች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር።

ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ውድቅ ተደርጎ በማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ታይዟል።

ፍርድ ቤት ለግንቦት 29/2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በዛሬ ችሎት ተጠርጣሪዎች የተከሰሱበት አዋጅ ከ10 ዓመት በላይ የሚያሳስርና ከባድ ፍርድ የሚያስከትል በመሆኑ ማረሚያ ወርደው ፍርዳቸውን ይከታተሉ ተብሏል።

ቀሲስ በላይ #የጤና_እክል እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። በፌደራል ፖሊስ ጊዜያዊ ማቆያ ለመቆየት እንዲችሉ እንዲፈቀድላቸውም ጠይቀዋል።

ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተወከለ መርማሪ የጊዜያዊ ማቆያው ቦታ ጥበት መኖሩን ጠቅሶ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ እንዲደረግ ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ እስከ ቀጣይ ቀጠሮ ግንቦት 29 ቀን ድረስ ባሉበት የፖሊስ ማረፊያ እንዲቆዩ ፈቅዷል።

4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የፌደራል ፖሊስ ተገቢ ጥረት አድርጎ አፈላልጎ እንዲያቀርባቸው ታዟል።

መረጃው ከኤፍቢሲና ዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ የተወሰደ ነው።

https://telegra.ph/fbc-05-27-2

@tikvahethiopia