TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
መቀለ⬆️በሌሎች ክልሎች የተመደቡ የትግራይ ክልል ተማሪዎች ድህንነት #ያሳስበናል በሚል ሮማናት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ሰልፍ ተደርጎ ነበር።

©Bit(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የርብ ግድብ ተመረቀ‼️

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ በዛሬው ዕለት ከምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ጋር በመሆን የርብ ግድብ #መርቀው ከፍተዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የተደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች በሰላም መጠናቀቃቸው ተሰምቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዋና አቃቤ ህግ አቶ #ብርሃኑ_ፀጋዬ፣ የቀድሞውን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የሕዝብ ግንኙነትና ኮምንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ዳይሬክተር የነበሩትን አቶ #ታዬ_ደንደአን
በመተካት የተሾሙትን አቶ #ዝናቡ_ቲኑን እንኳን ወደ ተቋማችን በደህና መጡ በሚል የመልካም ምኞት መግለጫ መቀበላቸውን ከትዊተር ገፃቸው ላይ አስተላልፈዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የርብ ግድብ ምረቃ⬆️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐብይ_አህመድ በርብ ያደረጉት ንግግር፦

• ዛሬ ጠዋት ከጣና ጀምረን ደንቢያ አካባቢና ሊቦከምከም አካባቢ እምቦጭ የሚባል ብቻየን ካልኖርኩ የሚል ጠላት ጎብኝተናል፡፡ የገባኝ ሚስጥር እንደ ጣልያን ርብ ላይ እንደሚሸነፍ ተረድቻለሁ፡፡

• ጠላቶቻችን በዚህች ቅድስት ሀገር ላይ ጦርነት ቢያውጁም አሸንፈው አያውቁም፡፡ እምቦጭንም እናሸንፈዋለን፡፡

• ኢትዮጰያ የአፍሪካ ውኃ ማማ ካስባሏት አካባቢዎች አንዱ ይህ አካባቢ ነው፡፡ ነገር ግን ውኃ፣ ጉልበትና መሬት እያለ አቀናጅተን አልተጠቀምንም፡፡

• እርሻን እንደ ቅርስ ባለማዘመን ከሚተቹ ሀገራት አንዷ ነች፡፡ እያሻሻልን መሄድ ሲገባን ዛሬም አርሶ አደሮች ብዙ ጉልበት እያፈሰሱ ትንሽ ምርት የሚያገኙ ናቸው፡፡

• ይህንን የእልህ የሆነ ዝናብ፣ ፀሐይ፣ እምቦጭ በጋራ እንደምናሸንፍ እንድንችል በጋራ እንድንቆም ይገባል፡፡ አሁን ለኢትዮጵያ የሚያዋጣው መደመር ብቻ ነው፡፡ እንደ እምቦጭ ሁሉም ለእኔ ከሆነ ተያይዞ መጥፋት ነው፡፡

• በግድቡ አገዳ፣ ፍራፍሬ ፣ አትክልት አሳ፣ እያመረቱ መጠቀም ይገባል፡፡ይህንን ግድብ እውን ለማድረግ ሕይወት ጭምር የከፈላችሁ ናችሁና በአግባቡ መጠቀም ይችላል፡፡ የጎንደርን ውብ አካባቢ ቱሪስቶች እንዲጎበኙ ለማድረግ ሁላችንም እንሥራ፡፡

• ስትፈጠርም የዳቦ ቅርጫት የሆነች ኢትዮጵያን ሀብቷን አቀናጅተን እንሥራ፡፡መስኖ ከሀገራዊ ኢኮኖሚው አራት በመቶ ብቻ ነው የሸፈነው፤ ስለዚህ ይህንን ማሻሻል አለብን፡፡ አሁን ተቋቋመው የመስኖ ኮሚሽን ግድብ ጀምረው የሚጨርሱ ተቋራጮችም ስላሉ ድርሻውን ይወጣል፡፡

• የአካባቢው አርሶ አደሮች የሚያስፈልጋችሁን የቴክኖሎጂና የሙያ ድጋፍ ያደርጋል፡፡

• በእምቦጭ ላይ በምናደርገው ዘመቻ በድጋሜ እንገናኛለን፤ እመቦጭ መሆን አያስፈልግም፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
ፎቶ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቀለ⬆️ከክልላቸው ውጭ በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት #የተመደቡ የትግራይ ክልል ተማሪዎች #ደህንነት ያሳስበናል ያሉ የመቀለ ከተማ ነዋሪዎች፣ በሮማናት አደባባይ ሰልፍ አካሂደዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የርብ መስኖ ግድብ ኘሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ ዛሬ ተመርቋል፡፡ ኘሮጀክቱ 28 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ላሊበላ⬆️

በአማራ ክላዊ መንግስት በሰሜና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገፕው: በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ የተመራውና ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ክቡር የአማራ ብ/ክ/መ ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንድአርጋቸው እና
ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች የሚገኙበት ልዑክ ከስዓት በኃላ ላይ ወደ ላሊ-በላ በማቅናት የላሊ-በላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ጥበቃና ጥገና የሚገኝበትን ሁኔታ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል፣

በቅድሚያም ቤተ-መድሃኒዓለም ሲጎበኝ በድንገት ለተሰበው የላሊ-በላ ህዝብ ንግግር ያደረጉት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ: "ላሊ-በላን የሚያክል ድንቅ የዓለምና የአፍሪካ ቅርስ: ለእኛ ደግሞ ከዚያም በላይ መኩሪያችንና መመኪያችንን ስለሆነ ደግመን መገንባት ባንችልም እንኳ መጠበቅ ግን ግዴታችን ነው" ብለዋል።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አርጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia