TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቃዎች ታግተዋል " የተባሉት 3 የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ሜይሊ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚገኝ እስር ቤት እንደሚገኙ የትግራይ ቴሌቪዥን ከደቂቃዎች በፊት ማረጋገጡ ይታወሳል። አሁን ከስፍራው በተገኘው መረጃ ሦስቱ ጋዜጠኞች ከእስር ተለቀዋል። የጋዜጠኞቹ መፈታት በማስመልከት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ጋዜጠኞቹ መረጃ…
#Tigray
የትግራይ የፀጥታና የሰላም ቢሮ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ይቅርታ ይጠይቅ አለ።
ቢሮው ይህን ያለድ ለአንድ ቀን ያህል በእገታና አስር ቆይተው ተለቀቁ በተባሉት ሦስት የትግራይ ቴሌቪዥን ባለሙያዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ነው።
የቢሮው መግለጫ የሚድያ ባለሙያዎቹ እገታ እና እስር አስመልክቶ የተሰራጨውን መረጃ የሚቃወም እንድምታ አለው።
ተስፋዝጊ ዓስበይ ፣ ኢሳያስ በየነ እና ኣታኽልቲ የተባሉ የትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ታግተውበታል ወደ ተባለው ቦታ መሄዳቸው የወረዳ ፣ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ አልነበራቸውም ብሏል።
ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ' ታግተናል ታስረናል ' ማለታቸው ልክ እንዳልሆነ አመላክቷል።
" ጋዜጠኞቹ ወደ ቦታው እንዲንቀሳቀሱ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ እንዲኖራቸው የግድ ነው ወይ ? " የሚል ጥያቄን ግን የቢሮው መግለጫ አለመለሰም።
" ሊበሉዋት የፈለጓትን አሞራ ቆቅ ናት ይሉዋታል " ብሎ የተረተው የሰላምና የፀጥታ ቢሮ መግለጫ ፤ ተገቢ ማጣራት ሳይደረግ የሚድያ ባለሙያዎቹ ' ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ታግተዋል ፤ ታፍነዋል ' ተብሎ የተሰራጨው መረጃ መስተካከል እና የትግራይ ቴሌቪዥን ይቅርታ ሊጠየቅበት እንደሚገባ አስገንዝቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጋዜጠኞች እና የሚድያ ባለሙያዎች የሙያ ነፃነታቸው ተከብሮ በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ቦታ ተዘዋውረው መረጃ በማሰባሰብ ለህዝብ የማድረስ መብት እንዳላቸው የገለጸው የትግራይ ጋዜጠኞች ማህበር ፤ በትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የተደረገው ወከባ አፈና ፣ እስር እና እንግልት በፅኑ ኮንነዋል።
ጋዜጠኞቹ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር ለህዝብ እና ለአገር መረጃ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ተገቢ የፀጥታ ጥብቃ ሊድረግላቸው እንደሚገባ ያሳሰበው የማህበሩ መግለጫ ፤ ህግ እና ስርዓት አክብረው ተገቢ የሙያ ተግባራቸው በሚከውኑ የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የሚድረግ ማንኛውም ዓይነት አፈና ፣ በደል ፣ ክልከላ እና ወከባ በጥብቅ እንቃወማለን ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ የፀጥታና የሰላም ቢሮ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ይቅርታ ይጠይቅ አለ።
ቢሮው ይህን ያለድ ለአንድ ቀን ያህል በእገታና አስር ቆይተው ተለቀቁ በተባሉት ሦስት የትግራይ ቴሌቪዥን ባለሙያዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ነው።
የቢሮው መግለጫ የሚድያ ባለሙያዎቹ እገታ እና እስር አስመልክቶ የተሰራጨውን መረጃ የሚቃወም እንድምታ አለው።
ተስፋዝጊ ዓስበይ ፣ ኢሳያስ በየነ እና ኣታኽልቲ የተባሉ የትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ታግተውበታል ወደ ተባለው ቦታ መሄዳቸው የወረዳ ፣ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ አልነበራቸውም ብሏል።
ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ' ታግተናል ታስረናል ' ማለታቸው ልክ እንዳልሆነ አመላክቷል።
" ጋዜጠኞቹ ወደ ቦታው እንዲንቀሳቀሱ የቀበሌ እና የመንደር አመራሮች መረጃ እንዲኖራቸው የግድ ነው ወይ ? " የሚል ጥያቄን ግን የቢሮው መግለጫ አለመለሰም።
" ሊበሉዋት የፈለጓትን አሞራ ቆቅ ናት ይሉዋታል " ብሎ የተረተው የሰላምና የፀጥታ ቢሮ መግለጫ ፤ ተገቢ ማጣራት ሳይደረግ የሚድያ ባለሙያዎቹ ' ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ታግተዋል ፤ ታፍነዋል ' ተብሎ የተሰራጨው መረጃ መስተካከል እና የትግራይ ቴሌቪዥን ይቅርታ ሊጠየቅበት እንደሚገባ አስገንዝቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጋዜጠኞች እና የሚድያ ባለሙያዎች የሙያ ነፃነታቸው ተከብሮ በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ቦታ ተዘዋውረው መረጃ በማሰባሰብ ለህዝብ የማድረስ መብት እንዳላቸው የገለጸው የትግራይ ጋዜጠኞች ማህበር ፤ በትግራይ ቴሌቪዥን የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የተደረገው ወከባ አፈና ፣ እስር እና እንግልት በፅኑ ኮንነዋል።
ጋዜጠኞቹ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር ለህዝብ እና ለአገር መረጃ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ተገቢ የፀጥታ ጥብቃ ሊድረግላቸው እንደሚገባ ያሳሰበው የማህበሩ መግለጫ ፤ ህግ እና ስርዓት አክብረው ተገቢ የሙያ ተግባራቸው በሚከውኑ የሚድያ ባለሙያዎች ላይ የሚድረግ ማንኛውም ዓይነት አፈና ፣ በደል ፣ ክልከላ እና ወከባ በጥብቅ እንቃወማለን ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ወቅታዊ ጥያቄያችሁን ሰምተናል ፤ ከሚመለከተው አካል ምላሽ ይሰጥበታል " - የትግራይ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ አመራሮች
ከመቐለ እና አከባቢዋ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተሰባሰቡ በሺህ የሚሆኑ ወጣቶች የሚበዙባቸው ሰልፈኞች ዛሬ ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ ወደ ከተማዋ የከንቲባ አስተዳደር ፅህፈት ቤት ተሰባስበው ነበር።
የአስተዳደሩ ዋና በሮችና ዙሪያው የሚጠብቁ በርካታ ቁጥር ያላቸው ፓሊሶች በአከባቢው የነበሩ ሲሆን በባነር የተፃፉ መፈክሮች በመያዝና ድምፅ በማሰማት ወደ አስተዳደሩ ህንፃ በተለያዩ አቅጣጫ የተመሙ ሰልፈኞች አንድ ላይ አንዳይሰባሰቡ አድርገዋቸዋል።
በአንዱ አቅጣጫ የመጡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰልፈኞች ከከንቲባው ህንፃ ዋና በር በቅርብ ርቀት በመሆን ፦
- ጊዚያዊ አስተዳደሩ አይፈርስም !
- በመንግስት ላይ እምቢታ ያወጁ ሃይሎች ላይ እርምጃ ይወሰድ !
- መንደርተኝነት እና ኋላቀርነት ይወገድ !
- ከፓርቲ መንግስት ይቀድማል !
- መንግስት ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- የህዝቦች አንድነት ለማፍረስ የሚደረገው እንቅስቃሴ በጥብቅ እንቃወማለን !
- እምባገነንነት ፣ጭቆናና አፈና አንቀበልም !
- መቐለ የልማት እንጂ የአመፅ መነሃሪያ አይደለችም !
- የጊዚያዊ አስተዳደሩ ውሳኔዎች በድማፃችን ይከበራሉ !
- የአመፅ መሪዎች ወደ ህግ ይቅረቡ !
- እውነተኛ የህዝብ ትግል አይቀለበስም !
- ህዝብ እና እውነት የያዘ ያሸንፋል !
- እናሸንፋለን ! ... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ከፍ ባለ ድምፅ አሰምተዋል።
የሰልፈኞቹ ጥያቄ ያዳመጡ በቦታው የተገኙ የክልሉ ከፍተኛ የፀጥታ አመራሮች " ወቅታዊ የሰልፈኞቹ ጥያቄ ከሚመለከተው አካል ምላሽ እንደሚሰጠው " በመንገር ሰልፈኞቹ ወደ መጠቡበት አከባቢ በሰላም እንዲመለሱ አድርገዋል።
በሰልፈኞቹ መካከል ይሁን ከፀጥታ አካላት ጋር የተፈጠረ ግርግር እና ግጭት እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ቦታው ደረስ በአካል በመገኘት አረጋግጧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾሙ አዲሱ የመቐለ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፃቸው " የትግራይ ትንሳኤ እውን እንዲሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሳ " የሚል ይዘት ያለው ፅሁፍ አጋርተዋል።
በተመሳሳይ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ እየመከረ ሲሆን ፤ በምክክሩ የዞን እና የክልሉ የፀጥታ አመራሮች ተሳታፊ እንደሆኑ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ያወጣው መረጃ ያመለክታል።
ይህ መረጃ ተዘጋጅቶ የተላከው በቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ወቅታዊ ጥያቄያችሁን ሰምተናል ፤ ከሚመለከተው አካል ምላሽ ይሰጥበታል " - የትግራይ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ አመራሮች
ከመቐለ እና አከባቢዋ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተሰባሰቡ በሺህ የሚሆኑ ወጣቶች የሚበዙባቸው ሰልፈኞች ዛሬ ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ ወደ ከተማዋ የከንቲባ አስተዳደር ፅህፈት ቤት ተሰባስበው ነበር።
የአስተዳደሩ ዋና በሮችና ዙሪያው የሚጠብቁ በርካታ ቁጥር ያላቸው ፓሊሶች በአከባቢው የነበሩ ሲሆን በባነር የተፃፉ መፈክሮች በመያዝና ድምፅ በማሰማት ወደ አስተዳደሩ ህንፃ በተለያዩ አቅጣጫ የተመሙ ሰልፈኞች አንድ ላይ አንዳይሰባሰቡ አድርገዋቸዋል።
በአንዱ አቅጣጫ የመጡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰልፈኞች ከከንቲባው ህንፃ ዋና በር በቅርብ ርቀት በመሆን ፦
- ጊዚያዊ አስተዳደሩ አይፈርስም !
- በመንግስት ላይ እምቢታ ያወጁ ሃይሎች ላይ እርምጃ ይወሰድ !
- መንደርተኝነት እና ኋላቀርነት ይወገድ !
- ከፓርቲ መንግስት ይቀድማል !
- መንግስት ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- የህዝቦች አንድነት ለማፍረስ የሚደረገው እንቅስቃሴ በጥብቅ እንቃወማለን !
- እምባገነንነት ፣ጭቆናና አፈና አንቀበልም !
- መቐለ የልማት እንጂ የአመፅ መነሃሪያ አይደለችም !
- የጊዚያዊ አስተዳደሩ ውሳኔዎች በድማፃችን ይከበራሉ !
- የአመፅ መሪዎች ወደ ህግ ይቅረቡ !
- እውነተኛ የህዝብ ትግል አይቀለበስም !
- ህዝብ እና እውነት የያዘ ያሸንፋል !
- እናሸንፋለን ! ... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ከፍ ባለ ድምፅ አሰምተዋል።
የሰልፈኞቹ ጥያቄ ያዳመጡ በቦታው የተገኙ የክልሉ ከፍተኛ የፀጥታ አመራሮች " ወቅታዊ የሰልፈኞቹ ጥያቄ ከሚመለከተው አካል ምላሽ እንደሚሰጠው " በመንገር ሰልፈኞቹ ወደ መጠቡበት አከባቢ በሰላም እንዲመለሱ አድርገዋል።
በሰልፈኞቹ መካከል ይሁን ከፀጥታ አካላት ጋር የተፈጠረ ግርግር እና ግጭት እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ቦታው ደረስ በአካል በመገኘት አረጋግጧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾሙ አዲሱ የመቐለ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፃቸው " የትግራይ ትንሳኤ እውን እንዲሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሳ " የሚል ይዘት ያለው ፅሁፍ አጋርተዋል።
በተመሳሳይ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ እየመከረ ሲሆን ፤ በምክክሩ የዞን እና የክልሉ የፀጥታ አመራሮች ተሳታፊ እንደሆኑ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ያወጣው መረጃ ያመለክታል።
ይህ መረጃ ተዘጋጅቶ የተላከው በቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Axum
" በአሁኑ ሰዓት የተለየ አዲስ መመሪያና ክልከላ ባልወጣበት ፤ የነበረውን የአለባበስ ስርዓት የሚቀይር አዲስ ጥያቄ ባልቀረበበት ሁኔታ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም " ሲል የትግራይ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮ ለአክሱም የትምህርት ፅህፈት ቤት በፃፈው ደብዳቤ ፤ " ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ምን ዓይነት አለባበስ መከተል እንዳለባቸው የሚያዝ የቆየ መመሪያ እና አሰራር አለን " ብሏል።
" ነባሩ የአለባበስ መመሪያ እና አሰራር እያለ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም በከተማው በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ተለይቶ ያልነበረ የአለባበስ ህግ እንዲተገበር ያቀረበው ጥያቄ ልክ አይደለም " ሲል ገልጿል።
" ከመ/ቤታችን የተላኩ ባለሙያዎች ለተነሳው ጥያቄ መፍትሄ ለማምጣት መግባባት ላይ ቢደርሱም ምክር ቤቱ ጥያቄውን እልባት እንዳላገኘ አድርጎ ቅሬታ ማቅረቡ ትክክል አይደለም " ሲል አመልክቷል።
በአሁኑ ሰዓት የተለየ አዲስ መመሪያና ክልከላ ስለሌለ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንደሌለው የአለባበስ ስርዓቱ በነበረው እንዲቀጥል ቢሮው አሳስቧል።
በሌላ በኩል ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ " ሙስሊም ተማሪዎች ከተፈቀወድ አለባበስ ውጭ ለብሰው (ሂጃብ አድርገው) መግባት ተከልክለዋል ፤ ከትምህርታቸውም ተሰተጓጉለዋል " ከተባለባቸው ትምህርት ቤቶች የአንዱን ትምህርት ቤት ዳይሬክተር ለማነጋገር ስልክ ቢደውልም በጉዳዩ ላይ ለሚድያ መረጃ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ገልፀዋል።
ትናንት የትግራይ አስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለሚዲያ መግለጫ ሊሰጥ ዝግጅት አድርጎ የነበረ ሲሆን ከላይ ያለውን የትምህርት ቢሮን መገለጫ ተስፋ በማድረግ ሊሰጠው ያሰበውን መግለጫ ለሌላ ጊዜ አስተላልፏል።
ይሁን እንጂ ዛሬም ተማሪዎች " ከተፈቀደው አለባበስ ውጪ ለብሳችኋል " በሚል ምክንያት ወደ ትምህርት መአድ እንዳይገቡ ተደርገዋል።
ጉዳዩ ብዙዎችን እንዳስቆጣ የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" በአሁኑ ሰዓት የተለየ አዲስ መመሪያና ክልከላ ባልወጣበት ፤ የነበረውን የአለባበስ ስርዓት የሚቀይር አዲስ ጥያቄ ባልቀረበበት ሁኔታ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም " ሲል የትግራይ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮ ለአክሱም የትምህርት ፅህፈት ቤት በፃፈው ደብዳቤ ፤ " ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ምን ዓይነት አለባበስ መከተል እንዳለባቸው የሚያዝ የቆየ መመሪያ እና አሰራር አለን " ብሏል።
" ነባሩ የአለባበስ መመሪያ እና አሰራር እያለ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም በከተማው በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ተለይቶ ያልነበረ የአለባበስ ህግ እንዲተገበር ያቀረበው ጥያቄ ልክ አይደለም " ሲል ገልጿል።
" ከመ/ቤታችን የተላኩ ባለሙያዎች ለተነሳው ጥያቄ መፍትሄ ለማምጣት መግባባት ላይ ቢደርሱም ምክር ቤቱ ጥያቄውን እልባት እንዳላገኘ አድርጎ ቅሬታ ማቅረቡ ትክክል አይደለም " ሲል አመልክቷል።
በአሁኑ ሰዓት የተለየ አዲስ መመሪያና ክልከላ ስለሌለ የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንደሌለው የአለባበስ ስርዓቱ በነበረው እንዲቀጥል ቢሮው አሳስቧል።
በሌላ በኩል ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ " ሙስሊም ተማሪዎች ከተፈቀወድ አለባበስ ውጭ ለብሰው (ሂጃብ አድርገው) መግባት ተከልክለዋል ፤ ከትምህርታቸውም ተሰተጓጉለዋል " ከተባለባቸው ትምህርት ቤቶች የአንዱን ትምህርት ቤት ዳይሬክተር ለማነጋገር ስልክ ቢደውልም በጉዳዩ ላይ ለሚድያ መረጃ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ገልፀዋል።
ትናንት የትግራይ አስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለሚዲያ መግለጫ ሊሰጥ ዝግጅት አድርጎ የነበረ ሲሆን ከላይ ያለውን የትምህርት ቢሮን መገለጫ ተስፋ በማድረግ ሊሰጠው ያሰበውን መግለጫ ለሌላ ጊዜ አስተላልፏል።
ይሁን እንጂ ዛሬም ተማሪዎች " ከተፈቀደው አለባበስ ውጪ ለብሳችኋል " በሚል ምክንያት ወደ ትምህርት መአድ እንዳይገቡ ተደርገዋል።
ጉዳዩ ብዙዎችን እንዳስቆጣ የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ እርምጃ እንወሰወዳለን " - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሴት ሙስሊም ተማሪዎች #ሒጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላና የመብት ጥሰት አስመልክቶ ዛሬ ዓርብ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል። በዚሁ መግለጫ " የፌደራል…
#Update
" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃዎችን እንስወዳለን " - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት
የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ከሃይማኖታዊ ስርዓት ውጪ በሆነ ሁኔታ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላ እና የመብት ጥሰት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ የተከለከሉ 160 የያዝነው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዲፈታ ካለፈው ጥቅምት 2017 ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች እንዳደረገ ምክር ቤቱ ጠቅሷል።
ትምህርት ቤቱ በያዝነው ሳምንት የትግራይ ትምህርት ቢሮ አዲስ ህግ እና ደንብ ባልወጣበት ሁኔታ ተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸው እንዳይማሩ መደረጉ ልክ እንዳልሆነ አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ባለመቀበል ተማሪዎቹ በማስፈራራት እና በማሰር ከእውቀት ገበታ ውጭ እንዲሆኑ ማድረጉ ምክር ቤቱ በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤት ባወጣው የ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ፦
1. የሂጃብ ክልከላው በህገ-መንግስት የተቀመጡ የጋራ እና የግል መብቶች የሚፃረር ፣ በትምህርት ሚንስቴር እና በክልሉ መከበር ያለባቸው ደንቦች የጣሰ ነው።
2. የትምህርት ቤቶች ህግ በህገ-መንግስቱ የተቀመጡ መብቶች የሚፃረር መሆን የለበትም። በትምህርት ሚንስቴር ደንብ ቁጥር -6 ንኡስ ቁጥር -3 ሂጃብ መልበስ እንደሚፈቅድ በግልፅ ተደንግጓል ስለሆነም ጥያቄያችን በዚሁ ደንብ በአስቸኳይ እንዲመለስ እንጠይቃለን።
3. ትግራይ አሁን ባለችበት ፓለቲካዊ ቀውስ በሃይማኖት ምክንያት ሌላ ቀውስ መጨመር ተገቢ ስላልሆነ ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስልን።
4. በጦርነቱ ምክንያት ከእውቀት መአድ ርቀው የነበሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንዲበረታቱ የሚገባቸው ሙስሊም ሴቶች ማበረታታት ሲገባ ሂጃብ በመልበሳቸው ብቻ ከትምህርት ገበታ መከልከል ፍፁም ኢ-ህጋዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንጠይቃለን።
5. ጉዳዩ በማንኛውም መልኩ ለፓለቲካ ፍጆታ መጠቀምያ ማዋል ስለማይገባ ጉዳዩ እንዳይፈታ የሚያወሳስቡት ግለሰቦች ወይም አካላት መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርጋቸው ጥሪ እናቀርባለን።
6. ኢ-ህገመንግስታዊ ተግባሩን የሌሎች እምነት ተከታዮች እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች እንዲያወግዙት ጥሪ እናቀርባለን።
7. ከትምህርት ገበታ የተስተጓጎሉት ተማሪዎች የትምህርት ሚንስቴር ያወጣው ሁሉም ትምህርት ቤቶች መፈፀም የሚገባቸው የአለባበስ ሁኔታ የሚመለከት ህግና ደንብ ያልጣሱ ስለሆነ ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ እንዲደረግ በአፅንኦት እንጠይቃለን።
8. ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ እየተደረገ ያለው ተግባር ሰብአዊ መብቶች ፣ ክልላዊ ፣ አገራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ህጎች የሚፃረር በመሆኑ በጥብቅ እንኮንነዋለን።
9. ከትምህርት ሚንስቴር መመሪያ እና ደንብ ባፈነገጠ መልኩ በግል ፍላጎት ብቻ በመመራት በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ህገ-ወጥ ተግባር የፈፀሙት ግለሰቦች እና አካላት በህግ እንዲጠየቁ ጥሪ እናቀርባለን።
10. የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ህገ-ወጥ ተግባር እንዲወገዝ ድጋፍ የቸራችሁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል።
11. ፍትሃዊ ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የክልላችን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር በመምከር በቀጣይ የምንወስዳቸው ሰላማዊ የትግል እርምጃዎች ለህዝባችን እናሳውቃለን።
... ብሏል።
መረጃውን የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃዎችን እንስወዳለን " - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት
የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ከሃይማኖታዊ ስርዓት ውጪ በሆነ ሁኔታ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላ እና የመብት ጥሰት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ የተከለከሉ 160 የያዝነው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዲፈታ ካለፈው ጥቅምት 2017 ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች እንዳደረገ ምክር ቤቱ ጠቅሷል።
ትምህርት ቤቱ በያዝነው ሳምንት የትግራይ ትምህርት ቢሮ አዲስ ህግ እና ደንብ ባልወጣበት ሁኔታ ተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸው እንዳይማሩ መደረጉ ልክ እንዳልሆነ አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ባለመቀበል ተማሪዎቹ በማስፈራራት እና በማሰር ከእውቀት ገበታ ውጭ እንዲሆኑ ማድረጉ ምክር ቤቱ በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤት ባወጣው የ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ፦
1. የሂጃብ ክልከላው በህገ-መንግስት የተቀመጡ የጋራ እና የግል መብቶች የሚፃረር ፣ በትምህርት ሚንስቴር እና በክልሉ መከበር ያለባቸው ደንቦች የጣሰ ነው።
2. የትምህርት ቤቶች ህግ በህገ-መንግስቱ የተቀመጡ መብቶች የሚፃረር መሆን የለበትም። በትምህርት ሚንስቴር ደንብ ቁጥር -6 ንኡስ ቁጥር -3 ሂጃብ መልበስ እንደሚፈቅድ በግልፅ ተደንግጓል ስለሆነም ጥያቄያችን በዚሁ ደንብ በአስቸኳይ እንዲመለስ እንጠይቃለን።
3. ትግራይ አሁን ባለችበት ፓለቲካዊ ቀውስ በሃይማኖት ምክንያት ሌላ ቀውስ መጨመር ተገቢ ስላልሆነ ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስልን።
4. በጦርነቱ ምክንያት ከእውቀት መአድ ርቀው የነበሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንዲበረታቱ የሚገባቸው ሙስሊም ሴቶች ማበረታታት ሲገባ ሂጃብ በመልበሳቸው ብቻ ከትምህርት ገበታ መከልከል ፍፁም ኢ-ህጋዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንጠይቃለን።
5. ጉዳዩ በማንኛውም መልኩ ለፓለቲካ ፍጆታ መጠቀምያ ማዋል ስለማይገባ ጉዳዩ እንዳይፈታ የሚያወሳስቡት ግለሰቦች ወይም አካላት መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርጋቸው ጥሪ እናቀርባለን።
6. ኢ-ህገመንግስታዊ ተግባሩን የሌሎች እምነት ተከታዮች እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች እንዲያወግዙት ጥሪ እናቀርባለን።
7. ከትምህርት ገበታ የተስተጓጎሉት ተማሪዎች የትምህርት ሚንስቴር ያወጣው ሁሉም ትምህርት ቤቶች መፈፀም የሚገባቸው የአለባበስ ሁኔታ የሚመለከት ህግና ደንብ ያልጣሱ ስለሆነ ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ እንዲደረግ በአፅንኦት እንጠይቃለን።
8. ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ እየተደረገ ያለው ተግባር ሰብአዊ መብቶች ፣ ክልላዊ ፣ አገራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ህጎች የሚፃረር በመሆኑ በጥብቅ እንኮንነዋለን።
9. ከትምህርት ሚንስቴር መመሪያ እና ደንብ ባፈነገጠ መልኩ በግል ፍላጎት ብቻ በመመራት በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ህገ-ወጥ ተግባር የፈፀሙት ግለሰቦች እና አካላት በህግ እንዲጠየቁ ጥሪ እናቀርባለን።
10. የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ህገ-ወጥ ተግባር እንዲወገዝ ድጋፍ የቸራችሁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል።
11. ፍትሃዊ ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የክልላችን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር በመምከር በቀጣይ የምንወስዳቸው ሰላማዊ የትግል እርምጃዎች ለህዝባችን እናሳውቃለን።
... ብሏል።
መረጃውን የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል። ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ…
#TPLF #Tigray
ለሁለት ቡድን የተከፈሉት የህወሓት አመራሮች አሸናፊ እና ተሸናፊ በሌለበት የፓለቲካ ችግሮቻቸውን ለመፍታት የተደረገው ተደጋጋሚ ድርድር አልተሳካም አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር።
ሁለቱ ቡድኖች ፓለቲካዊ ልዩነታቸው እንዲፈታ ከመጣር ይልቅ ፤ አንዱ ሌላውን ጠርጎ ለማጥፋት በሚል እሳቤ መጠመዳቸው ለድርድሩ አለማሳካት አንዱ እና ዋነኛ ምክንያት ነው ተብሏል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ ለክልሉ መገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?
- የፓለቲካ ልዩነቱ ዋና መነሻ ከፍተኛ አመራሩ በመሆኑ ችግሩ በድርድር እንዲፈታ ጥረት የተደረገው በከፍተኛ አመራሩ ነው ብለዋል።
- የክልሉ የፀጥታ ሃይል ጨምሮ ሌሎች አካላት " ሁለቱ የህወሓት ቡድኖች ችግሮቻቸው ፓለቲካዊ ነው መፈታት ያለበትም በፓለቲካዊ መግባባት ነው " በሚል ለማደራደር በርካታ ጥረት ተደርጓል።
- በሁለቱ ቡድኖች መካከል የተፈጠረ የፓለቲካ ልዩነት አሁን የተፈጠረ ሳይሆን በወቅቱ ሳይፈታ ለዓመታት እየተከማቸ የመጣ መሆኑ ቡድኖቹ ለማቀራረብ አዳጋች አድርጎታል።
- በሁለቱን ቡድኖች ያለው ፓለቲካዊ መሳሳብ አሁንም ፓለቲካዊ መፍትሄ ያሻዋል። የፀጥታ ሃይሉ " የኛ ደጋፊ ነው " የሚል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚናገረው ተቀባይነት የለውም።
- የፀጥታ ሃይሉ የክልሉ እና የህዝቡ ፀጥታ እና ሰላም ከማስከበር ባለፈ አንዱን ቡድን በመደገፍ ሊቆም አይችልም። ህዝቡ ሁለቱ ቡድኖቹ ችግራቸው በጠረጴዛ ውይይት እንዲፈቱ ጫናውን ማሳደር ይጠበቅበታል።
- የፀጥታ ሃይሉ የአንዱ ደጋፊ ለማሰመሰል የሚደረግ ጥላሸት የመቀባት ተግባር ልክ አይደለም። ይህን መሰል በሬ ወለደ ውሸት የሚያራግቡ አካላትም ሆነ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባቸዋለን።
መረጃውን የትግራይ የመገናኛ ብዙሃንን ጠቅሶ የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ለሁለት ቡድን የተከፈሉት የህወሓት አመራሮች አሸናፊ እና ተሸናፊ በሌለበት የፓለቲካ ችግሮቻቸውን ለመፍታት የተደረገው ተደጋጋሚ ድርድር አልተሳካም አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር።
ሁለቱ ቡድኖች ፓለቲካዊ ልዩነታቸው እንዲፈታ ከመጣር ይልቅ ፤ አንዱ ሌላውን ጠርጎ ለማጥፋት በሚል እሳቤ መጠመዳቸው ለድርድሩ አለማሳካት አንዱ እና ዋነኛ ምክንያት ነው ተብሏል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ ለክልሉ መገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?
- የፓለቲካ ልዩነቱ ዋና መነሻ ከፍተኛ አመራሩ በመሆኑ ችግሩ በድርድር እንዲፈታ ጥረት የተደረገው በከፍተኛ አመራሩ ነው ብለዋል።
- የክልሉ የፀጥታ ሃይል ጨምሮ ሌሎች አካላት " ሁለቱ የህወሓት ቡድኖች ችግሮቻቸው ፓለቲካዊ ነው መፈታት ያለበትም በፓለቲካዊ መግባባት ነው " በሚል ለማደራደር በርካታ ጥረት ተደርጓል።
- በሁለቱ ቡድኖች መካከል የተፈጠረ የፓለቲካ ልዩነት አሁን የተፈጠረ ሳይሆን በወቅቱ ሳይፈታ ለዓመታት እየተከማቸ የመጣ መሆኑ ቡድኖቹ ለማቀራረብ አዳጋች አድርጎታል።
- በሁለቱን ቡድኖች ያለው ፓለቲካዊ መሳሳብ አሁንም ፓለቲካዊ መፍትሄ ያሻዋል። የፀጥታ ሃይሉ " የኛ ደጋፊ ነው " የሚል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚናገረው ተቀባይነት የለውም።
- የፀጥታ ሃይሉ የክልሉ እና የህዝቡ ፀጥታ እና ሰላም ከማስከበር ባለፈ አንዱን ቡድን በመደገፍ ሊቆም አይችልም። ህዝቡ ሁለቱ ቡድኖቹ ችግራቸው በጠረጴዛ ውይይት እንዲፈቱ ጫናውን ማሳደር ይጠበቅበታል።
- የፀጥታ ሃይሉ የአንዱ ደጋፊ ለማሰመሰል የሚደረግ ጥላሸት የመቀባት ተግባር ልክ አይደለም። ይህን መሰል በሬ ወለደ ውሸት የሚያራግቡ አካላትም ሆነ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባቸዋለን።
መረጃውን የትግራይ የመገናኛ ብዙሃንን ጠቅሶ የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
በትግራይ ክልል ፤ አክሱም ከተማ በሚገኘው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ መልበስ መከልከል ጋር ተያይዞ የተከሰተው ውዝግብ አሁንም መቋጫ አላገኘም።
የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጉዳዩ በማስመልከት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማ በሰጠው መግለጫ " የመብት ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃ እንወሰዳለን " ብሎ ነበር።
በመግለጫው " የፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ አስመልክቶ ያወጣው ህግ እንዲከበር እንጠይቃለን " ማለቱም ይታወሳል ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዛሬ ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም ከመቐለ እና አክሱም ታማኝ የመረጃ ምንጮች እንዳረጋገጠው ፤ ከምክር ቤቱ መግለጫ በኋላ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ወደ አክሱም በማምራት ከትምህርት ቤቱ አመራሮች ፣ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎች ተወያይተዋል።
የመረጃ ምንጫችን " ውይይቱ መሬት ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አላመጣም " ብሏል።
" የቢሮ ሃላፊው የትምህርት ሚንስቴር ህግ ፣ መመሪያ እና ደንብ መሰረት ያደረገ ትእዛዝ መስጠት ሲገባቸው ፤ ጉዳዩን ለማሸማገል ያደረጉት ጥረት ተጎጂ ተማሪዎቹ መታደግ አልቻለም " ሲል አክሏል።
ስለሆነም ችግሩ በቀጣዩ ቀናት መፈታት ካልተቻለ 160 የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች እጣ ፈንታ አደጋ ላይ ይወድቃል ሲል የመረጃ ምንጩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ተናግሯል።
የመቐለ ቲክቫህ አባል ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ቅርበት ካላቸው ወገኖች ባገኘው መረጃ ደግሞ ከውዝግቡ ጋር በተያያዘ ይሁን ለሌላ ስራ ጉዳይ ነገ የፌደራል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ የሃይማኖት አመራሮች መቐለ ትግራይ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ፤ አክሱም ከተማ በሚገኘው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ መልበስ መከልከል ጋር ተያይዞ የተከሰተው ውዝግብ አሁንም መቋጫ አላገኘም።
የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጉዳዩ በማስመልከት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማ በሰጠው መግለጫ " የመብት ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃ እንወሰዳለን " ብሎ ነበር።
በመግለጫው " የፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ አስመልክቶ ያወጣው ህግ እንዲከበር እንጠይቃለን " ማለቱም ይታወሳል ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዛሬ ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም ከመቐለ እና አክሱም ታማኝ የመረጃ ምንጮች እንዳረጋገጠው ፤ ከምክር ቤቱ መግለጫ በኋላ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ወደ አክሱም በማምራት ከትምህርት ቤቱ አመራሮች ፣ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎች ተወያይተዋል።
የመረጃ ምንጫችን " ውይይቱ መሬት ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አላመጣም " ብሏል።
" የቢሮ ሃላፊው የትምህርት ሚንስቴር ህግ ፣ መመሪያ እና ደንብ መሰረት ያደረገ ትእዛዝ መስጠት ሲገባቸው ፤ ጉዳዩን ለማሸማገል ያደረጉት ጥረት ተጎጂ ተማሪዎቹ መታደግ አልቻለም " ሲል አክሏል።
ስለሆነም ችግሩ በቀጣዩ ቀናት መፈታት ካልተቻለ 160 የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች እጣ ፈንታ አደጋ ላይ ይወድቃል ሲል የመረጃ ምንጩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ተናግሯል።
የመቐለ ቲክቫህ አባል ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ቅርበት ካላቸው ወገኖች ባገኘው መረጃ ደግሞ ከውዝግቡ ጋር በተያያዘ ይሁን ለሌላ ስራ ጉዳይ ነገ የፌደራል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ የሃይማኖት አመራሮች መቐለ ትግራይ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ጥያቄያችን ግልፅ ነው ፤ አሁንም ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች !! " - የትግራይ የእሰልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት
የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፥ በአክሱም ከተማ ከሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር ተያይዞ ወቅታዊ ማብራርያ ዛሬ ምሽት ሰጥቷል።
ምክር ቤቱ በማብራርያው ፥ የአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ክልከላ ሃይማኖታዊ እና ዓለማዊ የሰው ልጆችን መብት የሚጋፋ ከመሆኑ አኳያ ችግሩን ለመፍታት በብዙ አማራጮች ተሞኩረዋል ብሏል።
ከሙከራዎቹ አንዱ በክልሉ ትምህርቲ ቢሮ የተደረገው እንደሆነ ጠቁሟል።
ህግ የጣሰው ክልከላ እንዲነሳ " ትምህርት ቢሮ ያልተሳካ ሽምግልና እና መተግበር የማይችል ደብዳቤ ከመፃፍ የዘለለ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ የለም " ሲል ገልጿል።
የትምህርት ቤቱ አንዳንድ አመራሮች ከራሳቸው የሃይማኖት ፍላጎት ፤ የትምህርት መብት አተያይ በመነሳት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳይገቡ ተደርገዋል ብሏል ም/ቤቱ።
" የተማሪዎች የትምህርት ገበታ ክልከላ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውንና በሂጃብ ክልከላ ምክንያት ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያዘልቃቸው ዕድል እንዲዘጋ መደረጉ ነው " ሲል ገልጿል።
ምክር ቤቱ " ከቀናት በፊት በአቋም መግለጫችን እንደጠቀስነው ክልከው በአፈጣኝ ካልተፈታ በህግ ክስ እንጠይቃለን ባልነው መሰረት ጉዳዩ ወደ ህግ ወስደነዋል " ብሏል።
በዚህም በቀጣይ " እወስደዋለሁ " ያለውን እርምጃ መተግበር መጀመሩ አስታውቋል።
" ጉዳዩ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጋር ብቻ ሳይሆን ከሴቶች መብትና የሰው ልጆች የመማር መብት ጥሰት አኳያ መታየት አለበት " ያለው ምክር ቤቱ " ጉዳዩ ሁሉም ትግራዋይ እንዲያወግዘው " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው ማጠቃለያ " ጥያቄያችን ግልፅ ነው ፤ አሁንም ሂጃብዋ ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፥ በአክሱም ከተማ ከሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር ተያይዞ ወቅታዊ ማብራርያ ዛሬ ምሽት ሰጥቷል።
ምክር ቤቱ በማብራርያው ፥ የአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ክልከላ ሃይማኖታዊ እና ዓለማዊ የሰው ልጆችን መብት የሚጋፋ ከመሆኑ አኳያ ችግሩን ለመፍታት በብዙ አማራጮች ተሞኩረዋል ብሏል።
ከሙከራዎቹ አንዱ በክልሉ ትምህርቲ ቢሮ የተደረገው እንደሆነ ጠቁሟል።
ህግ የጣሰው ክልከላ እንዲነሳ " ትምህርት ቢሮ ያልተሳካ ሽምግልና እና መተግበር የማይችል ደብዳቤ ከመፃፍ የዘለለ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ የለም " ሲል ገልጿል።
የትምህርት ቤቱ አንዳንድ አመራሮች ከራሳቸው የሃይማኖት ፍላጎት ፤ የትምህርት መብት አተያይ በመነሳት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳይገቡ ተደርገዋል ብሏል ም/ቤቱ።
" የተማሪዎች የትምህርት ገበታ ክልከላ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውንና በሂጃብ ክልከላ ምክንያት ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያዘልቃቸው ዕድል እንዲዘጋ መደረጉ ነው " ሲል ገልጿል።
ምክር ቤቱ " ከቀናት በፊት በአቋም መግለጫችን እንደጠቀስነው ክልከው በአፈጣኝ ካልተፈታ በህግ ክስ እንጠይቃለን ባልነው መሰረት ጉዳዩ ወደ ህግ ወስደነዋል " ብሏል።
በዚህም በቀጣይ " እወስደዋለሁ " ያለውን እርምጃ መተግበር መጀመሩ አስታውቋል።
" ጉዳዩ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጋር ብቻ ሳይሆን ከሴቶች መብትና የሰው ልጆች የመማር መብት ጥሰት አኳያ መታየት አለበት " ያለው ምክር ቤቱ " ጉዳዩ ሁሉም ትግራዋይ እንዲያወግዘው " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው ማጠቃለያ " ጥያቄያችን ግልፅ ነው ፤ አሁንም ሂጃብዋ ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ለ1,523 ቀናት ያህል በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን " - ተፈናቃይ ወገኖች
ዛሬ ጥዋት በመቐለ ሰላማዊ ስልፍ ተካሂዷል።
ሰላማዊ ሰልፉ " በቃን ወደ ቄያችን መልሱን " ባሉ የተፈናቃይ መጠለያዎች ውስጥ በሚገኙ ወገኖች አማካኝነት ነው የተደረገው።
የመቐለ ሮማናት አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ፓሊስ ከተሸከርካሪ እና ከእግረኞች እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ተደርገው ነበር።
በመቐለ እና ከመቐለ ውጪ ባሉት የተፈናቃይ መጠለያዎች የሚገኙ ወገኖች " ይበቃል !! " በሚል በሦስት አቅጣጫ ወደ ሮማናት አደባባይ ተሰባስበው ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ሰልፈኞች በሮማናት አደባባይ እንደደረሱ ፦
- ለ1523 ቀናት በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን !
- የፕሪቶሪያ ስምምነት በሙሉነት ይተግበር !
- ወደ ቤታችን መልሱን !
- ጦርነት እንጠየፋለን ፤ ሰላም እንሻለን !
- ዓለም ድምፃችንን ስሚ !
- በመቀጠል ያለው የተፈናቃዮች ሞት ይብቃ !
- ህገ- መንግስት ይከበር ! ... የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
ተፈናቃዮቹ በተወካያቸው በኩል ባሰሙት መግለጫ ፥ በመላ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች በረሃብ እና መድሃኒት እጦት እየሞቱ መሆናቸው ጠቅሰዋል።
ለማሳያ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ ብቻ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የተፈናቃይ ማቆያ ጣብያዎች ይኖሩ የነበሩ ከ812 በላይ ወገኖች ህይወታቸው ማጣታቸው ገልፀዋል።
መሰል ሰለማዊ ሰልፍ የዛሬን ጨምሮ ለ3 ቀናት እንደሚኖር ተነግሯል። የዛሬው የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ሰላማዊ ነበር።
የተፈናቃይ ስልፈኞቹን ጥያቄ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ምላሽ ካለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተከታትሎ ያቀርባል።
#TigraiTV #TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ዛሬ ጥዋት በመቐለ ሰላማዊ ስልፍ ተካሂዷል።
ሰላማዊ ሰልፉ " በቃን ወደ ቄያችን መልሱን " ባሉ የተፈናቃይ መጠለያዎች ውስጥ በሚገኙ ወገኖች አማካኝነት ነው የተደረገው።
የመቐለ ሮማናት አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ፓሊስ ከተሸከርካሪ እና ከእግረኞች እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ተደርገው ነበር።
በመቐለ እና ከመቐለ ውጪ ባሉት የተፈናቃይ መጠለያዎች የሚገኙ ወገኖች " ይበቃል !! " በሚል በሦስት አቅጣጫ ወደ ሮማናት አደባባይ ተሰባስበው ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ሰልፈኞች በሮማናት አደባባይ እንደደረሱ ፦
- ለ1523 ቀናት በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን !
- የፕሪቶሪያ ስምምነት በሙሉነት ይተግበር !
- ወደ ቤታችን መልሱን !
- ጦርነት እንጠየፋለን ፤ ሰላም እንሻለን !
- ዓለም ድምፃችንን ስሚ !
- በመቀጠል ያለው የተፈናቃዮች ሞት ይብቃ !
- ህገ- መንግስት ይከበር ! ... የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
ተፈናቃዮቹ በተወካያቸው በኩል ባሰሙት መግለጫ ፥ በመላ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች በረሃብ እና መድሃኒት እጦት እየሞቱ መሆናቸው ጠቅሰዋል።
ለማሳያ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ ብቻ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የተፈናቃይ ማቆያ ጣብያዎች ይኖሩ የነበሩ ከ812 በላይ ወገኖች ህይወታቸው ማጣታቸው ገልፀዋል።
መሰል ሰለማዊ ሰልፍ የዛሬን ጨምሮ ለ3 ቀናት እንደሚኖር ተነግሯል። የዛሬው የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ሰላማዊ ነበር።
የተፈናቃይ ስልፈኞቹን ጥያቄ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ምላሽ ካለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተከታትሎ ያቀርባል።
#TigraiTV #TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዛሬ ጥር 5/2017 ዓ.ም ተፈናቃዮች " ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን ! " በሚል የጀመሩትን ሰላማዊ ሰልፍ የሚደግፍ መግለጫ አውጥተዋል።
" ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን በሚል መሪ ቃል በተፈናቃዮች የተጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ቀናና የሚደገፍ " ብሎታል ጊዚያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው።
" የተፈናቃዮች መከራ ተገቢ ምላሽ አልተሰጠውም " ያለው መግለጫው " የፌደራል መንግስት የገባው ውል እና ቃል በመተግበር ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለበት " ሲል በአፅንኦት ገልጿል።
" አሁንም በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ከአገር መከላከያ ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ይውጡ " ሲልም አክሏል።
" በህገ-መንግስቱ ማእቀፍ የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለባቸው "ም ብሏል።
" የአፍሪካ ህብረት ፣ የአሜሪካ መንግስት ፣ የአውሮፓ ህብረት እና የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የህዝቡ ድምፅ በማዳመጥ የፕሪቶሪያ ውል በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆን ጫናቸው እንዲያሳድሩ " ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
" ፅላል ስቪክ ማሕበር ማሕበረሰብ ምዕራብ ትግራይ " የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ማህበር ያስተባበረውና " ይበቃል ! " በሚል መሪ ቃል ዛሬ በመቐለ ሮማናት አደባባይ መንገድ በመዝጋት የተጀመረው የተፈናቀዮች ሰላማዊ ሰልፍ እስከ ጥር 7/2017 ዓ.ም እንደሚቀጥል ታውቋል።
ዛሬ በርካታ የመቐለ ጎዳናዎች ተዘግተው በርካታ የፖሊስ አባላትም ተሰማርተው ነው የዋሉት።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዛሬ ጥር 5/2017 ዓ.ም ተፈናቃዮች " ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን ! " በሚል የጀመሩትን ሰላማዊ ሰልፍ የሚደግፍ መግለጫ አውጥተዋል።
" ይበቃል ወደ ቄያችን መልሱን በሚል መሪ ቃል በተፈናቃዮች የተጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ቀናና የሚደገፍ " ብሎታል ጊዚያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው።
" የተፈናቃዮች መከራ ተገቢ ምላሽ አልተሰጠውም " ያለው መግለጫው " የፌደራል መንግስት የገባው ውል እና ቃል በመተግበር ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለበት " ሲል በአፅንኦት ገልጿል።
" አሁንም በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ከአገር መከላከያ ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ይውጡ " ሲልም አክሏል።
" በህገ-መንግስቱ ማእቀፍ የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ አለባቸው "ም ብሏል።
" የአፍሪካ ህብረት ፣ የአሜሪካ መንግስት ፣ የአውሮፓ ህብረት እና የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የህዝቡ ድምፅ በማዳመጥ የፕሪቶሪያ ውል በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆን ጫናቸው እንዲያሳድሩ " ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
" ፅላል ስቪክ ማሕበር ማሕበረሰብ ምዕራብ ትግራይ " የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ማህበር ያስተባበረውና " ይበቃል ! " በሚል መሪ ቃል ዛሬ በመቐለ ሮማናት አደባባይ መንገድ በመዝጋት የተጀመረው የተፈናቀዮች ሰላማዊ ሰልፍ እስከ ጥር 7/2017 ዓ.ም እንደሚቀጥል ታውቋል።
ዛሬ በርካታ የመቐለ ጎዳናዎች ተዘግተው በርካታ የፖሊስ አባላትም ተሰማርተው ነው የዋሉት።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሂጃብሂጃብ #አክሱም
" ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ #እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ ታዟል " - ፍርድ ቤት
በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ክልከላ አድርገዋል በተባሉት አካላት ላይ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ህጋዊ ክስ መስርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን ከምክር ቤቱ ጠበቃ አረጋግጧል።
በተመሰረተው ክስ መሰረት ተከሳሾች ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ የመጥሪያ ትእዛዝ ተፅፎላቸዋል።
የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ለተከሳሾች የፃፈው የመጥሪያ ትእዛዝ ሙሉ ይዘት ምን ይላል ?
ከሳሽ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሲሆን ተከሳሾች ደግሞ :-
➡ የአክሱም ከተማ ትምህርት ፅህፈት ቤት
➡ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ አብራሃ ወ አፅብሃ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ ወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ ክንደያ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ናቸው።
በዚሁ ደብዳቤ ላይ ተከሳሾች በወሰኑት አስተዳደራዊ ውሳኔ መሰረት የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን በቀረበቅ ማመልከቻ መረዳት እንደተቻለ ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ፤ የተሰጠው አስተዳደራዊ ውሳኔ እግድ ካለተጣለበት በሴት ተማሪዎቹ ላይ የማይመለስ የመብት ጥሰት ሊያጋጥም ስለሚችል ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ አዟል።
ተከሳሾችም በቀረበው የእግድ ማመልከቻ መሰረት ቀርበው ቃል እንዲሰጡ በፍርድ ቤቱ ለቀን 16/05/2017 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት ተቀጥረዋል።
NB. ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደብዳቤውን ትክክለኝነት ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠበቃ ማረጋገጥ ችሏል።
159 የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከሂጃብ ክልከላ በተያያዘ ትናንት የተጠናቀቀውን 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን የሚያስችላቸውን ፎርም ሳይሞሉ መቀረታቸውን የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል መግለጹ ይታወሳል።
ጉዳዩን እስከመጨረሻውን የምንከታተለው ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ #እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ ታዟል " - ፍርድ ቤት
በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ክልከላ አድርገዋል በተባሉት አካላት ላይ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ህጋዊ ክስ መስርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን ከምክር ቤቱ ጠበቃ አረጋግጧል።
በተመሰረተው ክስ መሰረት ተከሳሾች ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ የመጥሪያ ትእዛዝ ተፅፎላቸዋል።
የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ለተከሳሾች የፃፈው የመጥሪያ ትእዛዝ ሙሉ ይዘት ምን ይላል ?
ከሳሽ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሲሆን ተከሳሾች ደግሞ :-
➡ የአክሱም ከተማ ትምህርት ፅህፈት ቤት
➡ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ አብራሃ ወ አፅብሃ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ ወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
➡ ክንደያ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ናቸው።
በዚሁ ደብዳቤ ላይ ተከሳሾች በወሰኑት አስተዳደራዊ ውሳኔ መሰረት የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን በቀረበቅ ማመልከቻ መረዳት እንደተቻለ ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ፤ የተሰጠው አስተዳደራዊ ውሳኔ እግድ ካለተጣለበት በሴት ተማሪዎቹ ላይ የማይመለስ የመብት ጥሰት ሊያጋጥም ስለሚችል ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ አዟል።
ተከሳሾችም በቀረበው የእግድ ማመልከቻ መሰረት ቀርበው ቃል እንዲሰጡ በፍርድ ቤቱ ለቀን 16/05/2017 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት ተቀጥረዋል።
NB. ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደብዳቤውን ትክክለኝነት ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠበቃ ማረጋገጥ ችሏል።
159 የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከሂጃብ ክልከላ በተያያዘ ትናንት የተጠናቀቀውን 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን የሚያስችላቸውን ፎርም ሳይሞሉ መቀረታቸውን የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል መግለጹ ይታወሳል።
ጉዳዩን እስከመጨረሻውን የምንከታተለው ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia