THIQAH
13K subscribers
2.61K photos
29 videos
1 file
23 links
ይህ ቲቃህ (ታማኝ) ኢትዮጵያ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ሥር የሚተዳደር የኢትዮጵያን ጨምሮ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ገጽ ነው።
Download Telegram
ደቡብ ሱዳን ውስጥ በተከሰተ የአውሮፕላን አደጋ 20 ሰዎች ህይታቸው አለፈ፡፡

በአደጋው 17 ደቡብ ሱዳናዊ፣ ሱዳናዊ እና አንድ ቻይናዊ ወዲያውኑ ህይወታቸው ማለፉን የደቡብ ሱዳን የመረጃ ሚኒስትር ጋትዎች ቢፓል ተናግረዋል፡፡

ከተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ ሁለቱ የበረራ አባላትና አንድ ህንዳዊ እንዲሁም አንድ የሀገሪቱ ዜጋ ከአደጋው ተርፈው ወደ ሆፒታል መላካቸውን የጁባ ዓለማቀፍ አየር መንገድ ዳይሬክተር ኢንጅነር ሳልህ አኮት ለጣቢያው ተናግረዋል፡፡

ሁሉም ተጓዦች ግሬተር ፒዎነር ኦፕሬቲንግ ካምፓኒ (GPOC) የተባለ የነዳጅ ዘይት ካምፓኒ ሠራተኞች እንደነበሩ ተነግሯል።

ሠራተኞቹ ለ28 ቀናት በሥራ ቆይተው ከዩኒቲ ግዛት እየተመለሱ በነበረበት ወቅት አደጋው እንደተፈጠረ ሚኒስትሩ ለራዲዮ ታማዙጂ አረጋግጠዋል፡፡

የሀገሪቱ ፓርላማ የትራንስፖርት ሚኒስቴር እና የአቪየሽን ባለስልጣን ስለሁኔታው ማብራሪያ እንዲሰጡ መጠየቁ ተዘግቧል፡፡ #Anadolu #Shine #Reuters

@ThiqahEth
😭12👍83🤔2
"ትራምፕ ኢራን ላይ ምንም መፍጠር ስላልቻሉ፤ የጥቃቱን ክሽፈት በግነት እየሸፋፈኑት ነው"- ኢራን

ትራምፕ ኢራን ላይ ምንም መፍጠር ስላልቻሉ፤ የጥቃቱን ክሽፈት በግነት እየሸፋፈኑት ነው ሲሉ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሚኒ ገለጹ።

የኢራኑ ጠቅላይ መሪ ትራምፕ የአሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት በኢራን ኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ ያደረሰውን ውጤት አስመልክቶ በማጋነን እየተናገሩ ነው። ሆኖም ጥቃቱ ምንም አይነት ውጤት አላስገኘም ብለዋል።

መሪው በይፋዊ የኤክስ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባልተለመደ መልኩ በተለይ ኢራን ላይ ያደረሱትን ጥቃት ማጋነናቸውን ገልፀዋል።

ኢራን ላይ ምንም ማድረግ አልቻሉም እና  ነገሮችን በማጋነን እውነቱን ለመደበቅ እየጣሩ ይገኛሉ ብለዋል።

ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ወደ ኢራን ዘልቆ በመግባት የኒውክሌር አቅማቸውን አጥፍተናል ማለታቸው ይታወሳል።

የሁለቱ ሀገራት ግጭት በአሜሪካ አመቻችነት በተደረሰ የተኩስ አቁም ስምምነት ተቋጭቷል ተብሏል።
#GazettePlus #Anadolu

@ThiqahEth
22🤔4😡4👏1🙏1