"....ይቅርታ ወንዝ ነው፡፡ ድንበርም የለውም፡፡ ወደ ሁሉ ይፈሳል፤ ሁሉን ያጠጣል፤ ሁሉን ደግሞ ያለመልማል፡፡ ይቅርታ ርቀውም ቀርበውም የነበሩትን በአንድነት የሚሰበሰብ የምስራች ድምፅ ነው፡፡ ወንዝ ለሁሉ ይፈሳል፡፡ ለምሳሌ አባይ ለኢትዮጵያ ይፈሳል፤ ለሱዳንም እንዲሁ ግብፅንም ያጠጣል፡፡ ወንዝ ንፁህ ነው "በቃ እንደውም ኢትዮጲያ ትሻለኛለች እና ኢትዮጲያ ጋር ብቻ ልፍሰስ" አይልም!! ምክንያቱም ወንዝ ተሻጋሪ ነውና ፡፡ ይቅርታም ልክ እንደዚሁ ነው፡፡ ይዞ ይሻገራል፡፡ ይቅርታ "ወንድሞቼ" ብሎ ለመጥራት ጉልበታም ያደርጋል፡፡ ይቅርታ ድልድይ ነው ሰውን ከራሱ፣ ሰውን ከሰው እና ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር ያገናኛል፡፡ በአጠቃላይ ይቅርታ የድል አድራጊዎች ምልክት የአሽናፊዎችም ሰንደቅ ነው፡፡ የሰው ልጅ ያለ ይቅርታ:ተንቀሳቃሽ ስልክም ያለ "ኔትወርክ" ባዶ ቀፎዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ የሰው ልጅ ኖረ ሚባለው አንድም ሲያፈቅር : አንድም ደሞ ይቅር ሲል ነው፡፡" #mamush
@tsegabwolde @tikvagethiopia
@tsegabwolde @tikvagethiopia