TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
3ኛው ዙር የ8100A ገቢ ማሰባሰቢያ ይፋ ሆነ!

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ገቢ ማሰባሰቢያ 3ኛው ዙር የ8100A ሁለት አዳዲስ ንዑስ ፕሮጀክቶችን ይዞ መቅረቡን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

የጽሕፈት ቤቱ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሪሶርስና ፕሮጀክት ማኔጅመንት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተወካይ ሰለሞን ተካ እንደገለጹት ለ6 ወራት የሚቆይ በተንቀሳቃሽ ስልክ በኩል የሚደረግ ድጋፍና ለ3 ወራት የሚቆይ የሊቀናይል የጥያቄና መልስ ውድድር ሁለቱ ንዑስ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡

በመርሃ ግብሩ ዜጎች በዝቅተኛ ገንዘብ ተሳትፈውበት 20 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ቢሆንም ፕሮጀክቱ በዋናነት የህዳሴ ግድቡን አጀንዳ በማድረግ አገራዊ መግባባትና አንድነትን ማጠናከርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

#WaltaInfo
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#UNHCR

በመላው አፍሪካ በሙዚቃ ስራዎቿ ተወዳጅነትንና እውቅና እያተፈረች የምትገኘው ወጣቷ ኢትዮጵያዊቷ ድምፃዊ ብሩክታዊት ጌታሁን [ቤቲ-ጂ] የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት [UNHCR] የበጎ ፈቃድ አምባሳደር በመሆን መሰየሟ ተሰምቷል፡፡

#UNHCR #WALTAINFO
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia