TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Turkey_Africa

የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በአፍሪካ ሀገራት 4 ቀናት ይፋዊ የስራ ገብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።

በመጀመሪያው ቀን ጉብኝታቸው በአንጎላ፣ ላውንዳ ተገኝተው ከሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ጃኦ ሎሬንኮ ጋር መክረዋል።

በመቀጠል በበቶጎ ሎሜ ከፕሬዚዳንት ፋውሬ ናሲንግቤ ጋር ተገናኝተው መክረዋል፤ በተጨማሪ ከቡርኪና ፋሶ ፕሬዜዳንት ሮች ማርክ ክርስትያን ካቦሬ እንዲሁም ከላይቤሪያ ፕሬዝዳት ጆርጅ ዊሃ ጋር ተገናኝተው መክረዋል (ሁሉም ምክክሮች ለሚዲያ ዝግ ነበሩ) ።

ዛሬ በመጨረሻው የስራ ጉብኝት መርሃግብራቸው ፕሬዜዳንት ሬስፕ ጣይብ ኤርዶጋን ወደናይጄሪያ አቅንተው በአቡጃ በፕሬዜዳንት ሙሀመድ ቡሃሪ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፤ መሪዎቹ ምክክርም አድርገዋል።

ቱርክ እና ናይጄሪያ ከኃይል እስከ መከላከያ ድረስ በርካታ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል፤ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከርም ስምምነት አድርገዋል።

ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን እ.ኤ.አ በ2003 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ቱርክ በአፍሪካ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ እና ከሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገች ነው።

@tikvahethiopia
👍1