#ለጥንቃቄ🚨
“ በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ " - ኮሚሽኑ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በተለምዶ ሰላም ሰፈር አካባቢ 4 ሜትር ከሚገመት ከፍተኛ ቦታ በተከሰተ የአለት ናዳ 3 ሰዎች መሞታቸውን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።
አደጋው የደረሰው ዛሬ ነው።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ባደረጉት ጥረት የ8 ሰዎች ሕይወት ማትረፍ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የአደጋው ምንስኤ ምንድን ነው ?
- ይህ አደጋ በከተማዋ ሲከሰት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ?
- ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ አቅርቧል፡፡
አቶ ንጋቱ ምን ምላሽ ሰጡ ?
“ እንዲህ አይነት አደጋዎች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጅ ኢንስቲትዩትም የመሬት መንሸራተት፣ ጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ይደረግ የሚል መረጃ ሲያስተላልፍ ነበር፡፡
ያልተጠበቀ ዝናብ ያጋጥማቸዋል የተባሉ ከተሞችን ሲጠቅስም አዲስ አበባም እዛ ውስጥ ተጠቅሳለች፡፡
በእርጥበት ምክንያት ናዳ፣ የአፈር መደርመስ ሊኖር ስለሚችል በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡
ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ላይ መፍትሄ ለመስጠት በሚደረገው ጥረትም የመፍትሄው አካል መሆን ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ሰዎችን ከቦታው ማንሳት ሊያስፈልግ ይችላል።
አዲስ አበባ ላይ የአለት ናዳ አደጋ አጋጥሞ አያውቅም፣ አላስታውስም፡፡ በእርግጥ ደረጃቸውን ያልጠበቁ፣ የአደጋ ደህንነት መስፈርት ሳይጠብቁ አፋፍ ላይ የተሰሩ ቤቶች ተንደው የሰው ሕይወት ጠፍቶ ያውቃል።
ጠሮ መስጂድ የሚባለው (አዲስ ከተማ ፍለ ከተማ ውስጥ) ሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈበት ሁኔታ ነበር ከኮንስትራክሽን ጥራት ጋር በተያያዘ፡፡
ይሄኛው (የአሁኑ የአለት አደጋ) እዛው መሬቱ ጋር ተያይዞ የበቀለው አለት ከዝናብ ብዛት በመሬት መሸርሸር የሚያጋጥም ነው፡፡
የአለት አደጋውን መስንስኤ ማጣራት የሚጠይቅ ነው ግን ከክረምቱ ወቅት ጋር የሚያያዝ ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን፡፡ አደጋ የደረሰባቸው መኖሪያ ቤቶቹ ከታች ነው ያሉት፤ አለቱ ደግሞ አፋፍ ላይ ነው ያለው፡፡ በግምት ወደ 4 ሜትር ከፍታ አለው፡፡
ብዙ ጊዜ አፋፍ ላይ ተንጠልጥለው ያሉ ቤቶች ላይ የመውደቅ እድልም አለው፡፡ የሰዎቹም የአኗኗር ሁኔታ፣ የቤቱ አቀማመጥና ደረጃ አስተዋጽኦ አድርጓል። ”
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ " - ኮሚሽኑ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በተለምዶ ሰላም ሰፈር አካባቢ 4 ሜትር ከሚገመት ከፍተኛ ቦታ በተከሰተ የአለት ናዳ 3 ሰዎች መሞታቸውን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።
አደጋው የደረሰው ዛሬ ነው።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ባደረጉት ጥረት የ8 ሰዎች ሕይወት ማትረፍ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የአደጋው ምንስኤ ምንድን ነው ?
- ይህ አደጋ በከተማዋ ሲከሰት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ?
- ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ አቅርቧል፡፡
አቶ ንጋቱ ምን ምላሽ ሰጡ ?
“ እንዲህ አይነት አደጋዎች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጅ ኢንስቲትዩትም የመሬት መንሸራተት፣ ጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ይደረግ የሚል መረጃ ሲያስተላልፍ ነበር፡፡
ያልተጠበቀ ዝናብ ያጋጥማቸዋል የተባሉ ከተሞችን ሲጠቅስም አዲስ አበባም እዛ ውስጥ ተጠቅሳለች፡፡
በእርጥበት ምክንያት ናዳ፣ የአፈር መደርመስ ሊኖር ስለሚችል በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡
ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ላይ መፍትሄ ለመስጠት በሚደረገው ጥረትም የመፍትሄው አካል መሆን ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ሰዎችን ከቦታው ማንሳት ሊያስፈልግ ይችላል።
አዲስ አበባ ላይ የአለት ናዳ አደጋ አጋጥሞ አያውቅም፣ አላስታውስም፡፡ በእርግጥ ደረጃቸውን ያልጠበቁ፣ የአደጋ ደህንነት መስፈርት ሳይጠብቁ አፋፍ ላይ የተሰሩ ቤቶች ተንደው የሰው ሕይወት ጠፍቶ ያውቃል።
ጠሮ መስጂድ የሚባለው (አዲስ ከተማ ፍለ ከተማ ውስጥ) ሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈበት ሁኔታ ነበር ከኮንስትራክሽን ጥራት ጋር በተያያዘ፡፡
ይሄኛው (የአሁኑ የአለት አደጋ) እዛው መሬቱ ጋር ተያይዞ የበቀለው አለት ከዝናብ ብዛት በመሬት መሸርሸር የሚያጋጥም ነው፡፡
የአለት አደጋውን መስንስኤ ማጣራት የሚጠይቅ ነው ግን ከክረምቱ ወቅት ጋር የሚያያዝ ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን፡፡ አደጋ የደረሰባቸው መኖሪያ ቤቶቹ ከታች ነው ያሉት፤ አለቱ ደግሞ አፋፍ ላይ ነው ያለው፡፡ በግምት ወደ 4 ሜትር ከፍታ አለው፡፡
ብዙ ጊዜ አፋፍ ላይ ተንጠልጥለው ያሉ ቤቶች ላይ የመውደቅ እድልም አለው፡፡ የሰዎቹም የአኗኗር ሁኔታ፣ የቤቱ አቀማመጥና ደረጃ አስተዋጽኦ አድርጓል። ”
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😢431❤129😭90🙏26🕊22😱16🤔9🥰7👏7
" የሉካንዳ ያልሆኑ ግለሰቦች ይዘው ሲመጡ በልዩ ሁኔታ ከ11 ሰዓት (ከበዓሉ ጠዋት) ጀምሮ የእርድ አገልግሎት እንሰጣለን " - ቄራዎች ድርጅት
ማህበረሰቡ የትንሳዔ በዓልን በሚያከብርበት ወቅት በሕጋዊ ቄራዎች የታረዱ እንስሳት ስጋን በመጠቀም እንዲሆን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አሳሰበ።
ለበዓሉ የእርድ አገልግሎት ዝግጅትን ምን ይመስላል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቅናቸው የድርጅቱ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገ/ሚካኤል፣ " በበዓላት በርከት ያሉ እንስሳት በልዩ ሁኔታ እንደሚገቡ ይጠበቃል። ዘድሮም ወደ 6,500 እንሰሳት ይገባሉ። ትላልቅ እንስሳት ወደ 4,000፤ ትናንሽ የምንላቸው በግና ፍየል ደግሞ 2,500 ይገባሉ ብለን እንጠብቃለን " ብለዋል።
" ለነዚህ ዝግጅት ተደርጓል። አንዱ የሰው ኃይል ዝግጅት ነው። 1,000 የሰው ኃይል ሰራተኛም ለዚህ በዓል በተጨማሪ የቀጠርንበት፣ ባለፈው ፆም ወቅትም የአቅም ግባታ ስልጠናዎችን የሰጠንበት፣ የእርድ ቦታና እንስሳት የሚቆዩበት ቦታ ዝግጅት ያደረግንበት ሁኔታዎች አለ " ሲሉ ገልጸዋል።
" በስርጭት ክፍልም ችግር እንዳይጋጥም ከ40 በላይ መኪና ዝግጁ ተዘጋጅቷል። ሌሎች ተጨማሪ ድጋፍ ሰጪ ተሽከርካሪዎችም አሉ " ብለዋል።
የእርድ አገልግሎቱ መቼና ስንት ሰዓት ነው የሚከናወነው ? ለሚለው ጥያቄያችን " ሉኳንዳዎች ያውቁታል ሰዓቱን። የሉካንዳ ያልሆኑ ግለሰቦች ይዘው ሲመጡ በልዩ ሁኔታ ከ11 ሰዓት (ከበዓሉ ጠዋት) ጀምሮ የእርድ አገልግሎት እንሰጣለን " ብለዋል።
" ምርመራ አድርገን፣ እስከ ቤት አድርሰን የአገልግልት ክፍያ 1,500 ብር ነው የምናስከፍለው ለበሬ " ሲሉም ገልጸዋል።
አቶ አታክልቲ፣ " ሕገ ወጥ እርድ ዘርፈ ብዙ ችግር ስላለው ህብረተሰቡ በዓሉን ሲያከብር በሕጋዊ ቄራዎች የታረዱ እንስሳት ስጋን እንዲጠቀም ጥሪ አስተላልፋለሁ " የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።
" ድርጅቱ በመጀመሪያ የነበረ አቅሙ ከ300 በታች ነበር የሚያርደው አሁን በቀን ከ3,500 እሰሳት በላይ የማረድ አቅም አለው " ሲሉም ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለ66 ዓመታት ንጽህናው በሐኪም የተረጋገጠ የእንስሳት እርድ አገልግሎት አየሰጠ የመጣና የሚገኝ ተቋም መሆኑንም አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ማህበረሰቡ የትንሳዔ በዓልን በሚያከብርበት ወቅት በሕጋዊ ቄራዎች የታረዱ እንስሳት ስጋን በመጠቀም እንዲሆን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አሳሰበ።
ለበዓሉ የእርድ አገልግሎት ዝግጅትን ምን ይመስላል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቅናቸው የድርጅቱ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገ/ሚካኤል፣ " በበዓላት በርከት ያሉ እንስሳት በልዩ ሁኔታ እንደሚገቡ ይጠበቃል። ዘድሮም ወደ 6,500 እንሰሳት ይገባሉ። ትላልቅ እንስሳት ወደ 4,000፤ ትናንሽ የምንላቸው በግና ፍየል ደግሞ 2,500 ይገባሉ ብለን እንጠብቃለን " ብለዋል።
" ለነዚህ ዝግጅት ተደርጓል። አንዱ የሰው ኃይል ዝግጅት ነው። 1,000 የሰው ኃይል ሰራተኛም ለዚህ በዓል በተጨማሪ የቀጠርንበት፣ ባለፈው ፆም ወቅትም የአቅም ግባታ ስልጠናዎችን የሰጠንበት፣ የእርድ ቦታና እንስሳት የሚቆዩበት ቦታ ዝግጅት ያደረግንበት ሁኔታዎች አለ " ሲሉ ገልጸዋል።
" በስርጭት ክፍልም ችግር እንዳይጋጥም ከ40 በላይ መኪና ዝግጁ ተዘጋጅቷል። ሌሎች ተጨማሪ ድጋፍ ሰጪ ተሽከርካሪዎችም አሉ " ብለዋል።
የእርድ አገልግሎቱ መቼና ስንት ሰዓት ነው የሚከናወነው ? ለሚለው ጥያቄያችን " ሉኳንዳዎች ያውቁታል ሰዓቱን። የሉካንዳ ያልሆኑ ግለሰቦች ይዘው ሲመጡ በልዩ ሁኔታ ከ11 ሰዓት (ከበዓሉ ጠዋት) ጀምሮ የእርድ አገልግሎት እንሰጣለን " ብለዋል።
" ምርመራ አድርገን፣ እስከ ቤት አድርሰን የአገልግልት ክፍያ 1,500 ብር ነው የምናስከፍለው ለበሬ " ሲሉም ገልጸዋል።
አቶ አታክልቲ፣ " ሕገ ወጥ እርድ ዘርፈ ብዙ ችግር ስላለው ህብረተሰቡ በዓሉን ሲያከብር በሕጋዊ ቄራዎች የታረዱ እንስሳት ስጋን እንዲጠቀም ጥሪ አስተላልፋለሁ " የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።
" ድርጅቱ በመጀመሪያ የነበረ አቅሙ ከ300 በታች ነበር የሚያርደው አሁን በቀን ከ3,500 እሰሳት በላይ የማረድ አቅም አለው " ሲሉም ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለ66 ዓመታት ንጽህናው በሐኪም የተረጋገጠ የእንስሳት እርድ አገልግሎት አየሰጠ የመጣና የሚገኝ ተቋም መሆኑንም አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤277😡57🙏32🥰12🕊10😭9🤔6😱5😢4
TIKVAH-ETHIOPIA
#DV2026 የ2026 የአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ማመልከቻ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት ተደርጓል። ለ2026 DV ለማመልከት https://dvprogram.state.gov/ ይጠቀሙ። ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም። ማመልከቻው እስከ ህዳር 5 /2024 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል። ከፍተኛ የመሙላት ፍላጎቶች ድረገጹ ላይ መዘግየቶችን ሊያስከትል ስለሚችል ለመሙላት እስከ የምዝገባው ጊዜ የመጨረሻ…
#DV2026
የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2026 አሸናፊዎች ቅዳሜ ሚያዚያ 25/2017 ዓ/ም ይፋ ይደረጋሉ።
ለዲቪ (Diversity Visa) 2026 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።
NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል።
ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራትን ሁሉ የሚጠቃልል ሲሆን #ኢትዮጵያም አንዷ ናት።
የዲቪ ሎተሪ መውጫ መድረሱን ተከትሎ " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች ሊጠነቀቁ ይገባል።
አንድ አመልካች ዲቪ 2026 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ከላይ የተጠቀሰው ድረገጽ ብቻ ነው።
አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2026 አሸናፊዎች ቅዳሜ ሚያዚያ 25/2017 ዓ/ም ይፋ ይደረጋሉ።
ለዲቪ (Diversity Visa) 2026 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።
NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል።
ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራትን ሁሉ የሚጠቃልል ሲሆን #ኢትዮጵያም አንዷ ናት።
የዲቪ ሎተሪ መውጫ መድረሱን ተከትሎ " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች ሊጠነቀቁ ይገባል።
አንድ አመልካች ዲቪ 2026 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ከላይ የተጠቀሰው ድረገጽ ብቻ ነው።
አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤2.25K🙏1.24K🕊144👏115😭67🥰57🤔47💔46😱34😡31😢23
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ይህን ያሉት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአሜሪካ መንግስት የቪዛና አገልንሎትና ኢምግሬሽን ጉዳዮችን በሚመለከት አዳዲስ አሰራሮችንና አካሄዶችን ይፋ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
"በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል" ሲሉ ተናግረዋል።
"ወደፊትም ለትምህርትም ሆነ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የመጓዝ እድል ያላቸው ዜጎች እነኝህን የተቀመጡ የቪዛ ቆይታ ጊዜዎች ካላከበሩ ለተለያዩ ችግሮች ሊጋለጡ የሚችሉ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንደረግ ማሳሰብ እንፈልጋለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወደ አሜሪካ ለመጓዝ፣ ቪዛ ለማግኘት ለአሜሪካ ኤምባሲ ማመልከቻ የሚያስገቡ ከመንግስትም ሆነ ከግል ተቋማት የሚመነጩ ሰነዶች ትክክል ስለመሆናቸው እያረጋገጡ እንዲሆን አሳስበዋል።
በአጠቃላይ የአሜሪካ መንግስት የቪዛ አገልግሎትን የኢምግሬሽን ጉዳዮችን የሚያወጣቸውን አዳዲስ አሰራሮች በመከታተል ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አምባሳደሩ፣ "ከአሜሪካም ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን" ሲሉም ተናግረዋል።
አምባሳደር ነብያት፣ "ይህ አሰራር የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ያልያዙትን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ይጨምራል" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ይህን ያሉት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአሜሪካ መንግስት የቪዛና አገልንሎትና ኢምግሬሽን ጉዳዮችን በሚመለከት አዳዲስ አሰራሮችንና አካሄዶችን ይፋ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
"በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል" ሲሉ ተናግረዋል።
"ወደፊትም ለትምህርትም ሆነ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የመጓዝ እድል ያላቸው ዜጎች እነኝህን የተቀመጡ የቪዛ ቆይታ ጊዜዎች ካላከበሩ ለተለያዩ ችግሮች ሊጋለጡ የሚችሉ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንደረግ ማሳሰብ እንፈልጋለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወደ አሜሪካ ለመጓዝ፣ ቪዛ ለማግኘት ለአሜሪካ ኤምባሲ ማመልከቻ የሚያስገቡ ከመንግስትም ሆነ ከግል ተቋማት የሚመነጩ ሰነዶች ትክክል ስለመሆናቸው እያረጋገጡ እንዲሆን አሳስበዋል።
በአጠቃላይ የአሜሪካ መንግስት የቪዛ አገልግሎትን የኢምግሬሽን ጉዳዮችን የሚያወጣቸውን አዳዲስ አሰራሮች በመከታተል ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አምባሳደሩ፣ "ከአሜሪካም ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን" ሲሉም ተናግረዋል።
አምባሳደር ነብያት፣ "ይህ አሰራር የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ያልያዙትን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ይጨምራል" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.36K😡195🤔63👏59😭33🕊28💔19🥰17😢17🙏11😱5