TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Shebelle

ሸበሌ የምትሰኝ የኢትዮጵያ መርከብ ከ11 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ስኳርና ሩዝ ይዛ በርበራ ወደብ መድረሷን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።

መርከቧ ከህንድ ሀገር የጫነችውን ስኳርና ሩዝ ይዛ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ድርሻ ባላት የበርበራ ወደበ እያራገፈች ነው።

በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ የኢትዮጵያ መርከቦች ወደ በርበራ ወደብ ጉዞ ሲያደርጉ ከ20 ዓመታት በኋላ ሸበሌ መርከብ ሁለተኛ ናት።

ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ ከ20 ዓመታት በኋላ ጊቤ መርከብ በበርበራ ወደብ የመጀመሪያ ጉዞ አድርጋ ነበር፤ በዚህ ጉዞም 11 ሺ 200 ሜትሪክ ቶን የፍጆታ ዕቃ ለሶማሌላንድ ገበያ አጓጉዛ ነበር።

NB : በበርበራ ወደብ፤ ዲ ፒ ወርልድ 51 በመቶ፣ ሶማሌላንድ 30 በመቶ እና ኢትዮጵያ ደግሞ 19 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወሳል ።

#አልአይን_ኒውስ

@tikvahethiopia