TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MoretEnaJeruWoreda

ትላንት ምሽት በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ አንድ ሰው ሲሞት 7 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው።

አደጋው የደረሰው በሰሜን ሸዋ ዞን ሞረትና ጅሩ ወረዳ ጅሁር ኮሲያንባ ቀበሌ መሆኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

ቦንቡ የፈነዳው በቀበሌው "ሰርጠሶስ" በሚባል መጠጥ ቤት ውስጥ ሲሆን የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሰባት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡

አደጋው ትናንት ምሽት ሁለት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሰው።

የጅሁር ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ዘነበ ሰሙ ፥ ፍንዳታው በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ መከሰቱን ለኤፍ ቢ ሲ አረጋግጠዋል ፥ በአደጋው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 4 ሰዎች ደብረ ብርሀን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

"የቦንብ አደጋውን ያደረሰው ግለሰብ ማን እንደሆነ በማጣራት ላይ ነን" ሲሉም አክለዋል።

@tikvahethiopia