#MoretEnaJeruWoreda
ትላንት ምሽት በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ አንድ ሰው ሲሞት 7 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው።
አደጋው የደረሰው በሰሜን ሸዋ ዞን ሞረትና ጅሩ ወረዳ ጅሁር ኮሲያንባ ቀበሌ መሆኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
ቦንቡ የፈነዳው በቀበሌው "ሰርጠሶስ" በሚባል መጠጥ ቤት ውስጥ ሲሆን የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሰባት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡
አደጋው ትናንት ምሽት ሁለት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሰው።
የጅሁር ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ዘነበ ሰሙ ፥ ፍንዳታው በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ መከሰቱን ለኤፍ ቢ ሲ አረጋግጠዋል ፥ በአደጋው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 4 ሰዎች ደብረ ብርሀን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
"የቦንብ አደጋውን ያደረሰው ግለሰብ ማን እንደሆነ በማጣራት ላይ ነን" ሲሉም አክለዋል።
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ አንድ ሰው ሲሞት 7 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው።
አደጋው የደረሰው በሰሜን ሸዋ ዞን ሞረትና ጅሩ ወረዳ ጅሁር ኮሲያንባ ቀበሌ መሆኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
ቦንቡ የፈነዳው በቀበሌው "ሰርጠሶስ" በሚባል መጠጥ ቤት ውስጥ ሲሆን የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሰባት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡
አደጋው ትናንት ምሽት ሁለት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሰው።
የጅሁር ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ዘነበ ሰሙ ፥ ፍንዳታው በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ መከሰቱን ለኤፍ ቢ ሲ አረጋግጠዋል ፥ በአደጋው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 4 ሰዎች ደብረ ብርሀን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
"የቦንብ አደጋውን ያደረሰው ግለሰብ ማን እንደሆነ በማጣራት ላይ ነን" ሲሉም አክለዋል።
@tikvahethiopia