TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MekdalaTreasures

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ በጀኔራል ናፒዬር ወታደሮች የተዘረፉ 13 የኢትዮጵያ ጥንታዊ የታሪክ አሻራ ማሳያ የሆኑ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቅርሶች በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል።

በኢትዮጵያ ቅርሶች አስመላሽ ኮሚቴ፣ በእንግሊዝ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሼሄራ ዛድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባባር ባደረጉት ጥረት ባለፈው ዓመት ጳጉሜን 3 /2013 ዓ.ም በለንደን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ መመለሳቸው ይታወሳል።

ከተመለሱት ቅርሶች መካከል ፦
- በነሀስ የተለበጠ ጋሻ፣
- በቆዳ የተደጎሰ በእጅ የተፃፈ ጥንታዊ የብራና የፀሎት መፅሀፍ እስከነመያዣቸው፣
- በመጠን ተለቅ ያለ የብር መስቀል፣
- አነስተኛ መጠን ያለው የብር መስቀል፣
- ፅዋ ይወሰድበት የነበረ ዋንጫ እና ማንኪያ፣
- የጳጳሳት እና የካህናት አክሊል፣
- ሦስት ከቀንድ የተሰሩና በብር የተለበጡ የቀንድ ዋንጫዎች፣
- የአንገት ጌጥ (ሃብል)፣
- ክታብ እና የገበታ ስዕል ይገኙበታል፡፡

ምንጭ፦ ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
👍2