TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MayDay

በዓለም ለ133ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ የሚከበረውን የላብ አደሮች ቀን በአዲስ አበባ ስታዲየም በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል።

የሠራተኞች መብት አለመጠበቅ፣ የኑሮ ውድነትና ሰራተኞች የሚያገኙት ደሞዝ አለመጣጣም፣ ከጊዜ ወደጊዜ ግጭቶች መከሰት ፣ ዲሞክራሲ በፈተና ውስጥ መግባትና ሌሎች ችግሮች እንዲፈቱ ተጠይቋል።

በዕለቱ ከተላለፉት መልዕክቶች ፦

🪧 " ሠራተኛው መልካም አስተዳደርን ይሻል "

🪧 " ግጭት እና ጦርነት ቆሞ የአገራችን ሠላም ይረጋገጥ "

🪧 " ሀገር አቀፍ መነሻ ደመወዝ ወለል እንዲወሰንልን እንጠይቃለን "

🪧 " የቤት ሰራተኞች መብት ይከበር "

🪧 " ለኑሮ መሻሻል መንግስት የንግድ ስርዓቱን ያሻሽል "

🪧 " የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት የመንግስት ኃላፊነት ነው "

🪧 " መንግስት ለኑሮ ውድነት መፍትሄ ይስጥ "

በየዓመቱ እ.ኤ.አ ግንቦት 1 ቀን የሚከበረው የላብ አደሮች ቀን (ሜይ ዴይ) የሰራተኞችን መብት ማስከበር ዋነኛ አላማው ነው።

ፎቶ፦ ኢብኮ

@tikvahethiopia