#LteAdvanced
ኢትዮ ቴሌኮም የLte advance 4G አገልግሎት በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል። የ4G ኔትወርክ አገልግሎት ማብሰሪያ ፕሮግራም በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ እንዳሉት በጣም ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ልታገኙ ስለሆነ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።
የዚህ ኔትወርክ ማስፋፊያ ግንባታ የቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን ይህ ግንባታ 170 ሚሊዮን ብር እንደፈጀ ተገልጿል። ወይዘሪት ፍሬህይወት እንደገለጹት የደንበኞች እየጨመረ ያለ ፍላጎት ለዚህ እንዳበቃቸው ገልጸው በቀጣይ ከፍተኛ የኢንተርኔት ፍላጎት ያላቸውን የኢትዮጵያ ከተሞች በጥናት እየለየን Lte Advance 4G ተግባራዊ እናደርጋለን ብለዋል።
ይሄ የኔትወርክ ማስፋፊያ ያለምንም ዕዳ በመንግስት ወጪ የተገነባ ሲሆን አገልግሎቱ ከዛሬ በመላ አዲስ አበባ አገልግሎት ይጀምራል። ይህ የ4G Lte አገልግሎት በ 50 የተመረጡ የመዲናዋ ቦታዎች ላይ የሙከራ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ከዚህ በኋላ አገልግሎት የሚሰጠውም የኢንተርኔት ፍላጎት ከፍተኛ በሆኑባቸው አካባቢዎች ብቻ ነው ተብሏል። አዲሱ አገልግሎት በአንዳንድ አፕሊኬሽኖች ላይ፣ advanced Lte ከ4G አራት ዕጥፍ ከ 3G ደግሞ 14 ዕጥፍ እንደሚፈጥን ወይዘሪት ፍሬህይወት ተናግረዋል።
[ETHIO FM 107.8]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኢትዮ ቴሌኮም የLte advance 4G አገልግሎት በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል። የ4G ኔትወርክ አገልግሎት ማብሰሪያ ፕሮግራም በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ እንዳሉት በጣም ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ልታገኙ ስለሆነ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።
የዚህ ኔትወርክ ማስፋፊያ ግንባታ የቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን ይህ ግንባታ 170 ሚሊዮን ብር እንደፈጀ ተገልጿል። ወይዘሪት ፍሬህይወት እንደገለጹት የደንበኞች እየጨመረ ያለ ፍላጎት ለዚህ እንዳበቃቸው ገልጸው በቀጣይ ከፍተኛ የኢንተርኔት ፍላጎት ያላቸውን የኢትዮጵያ ከተሞች በጥናት እየለየን Lte Advance 4G ተግባራዊ እናደርጋለን ብለዋል።
ይሄ የኔትወርክ ማስፋፊያ ያለምንም ዕዳ በመንግስት ወጪ የተገነባ ሲሆን አገልግሎቱ ከዛሬ በመላ አዲስ አበባ አገልግሎት ይጀምራል። ይህ የ4G Lte አገልግሎት በ 50 የተመረጡ የመዲናዋ ቦታዎች ላይ የሙከራ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ከዚህ በኋላ አገልግሎት የሚሰጠውም የኢንተርኔት ፍላጎት ከፍተኛ በሆኑባቸው አካባቢዎች ብቻ ነው ተብሏል። አዲሱ አገልግሎት በአንዳንድ አፕሊኬሽኖች ላይ፣ advanced Lte ከ4G አራት ዕጥፍ ከ 3G ደግሞ 14 ዕጥፍ እንደሚፈጥን ወይዘሪት ፍሬህይወት ተናግረዋል።
[ETHIO FM 107.8]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot