TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Happening_Now የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ አሰራር የቃል ኪዳን ስነድ የፊርማ ስነ ስርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በስነ ስርዓቱ ላይም የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #አቢይ_አህመድን ጨምሮ የሁሉም ፓርቲ መሪዎች ተገኝተዋል። የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ አሰራር የቃል ኪዳን ስነዱን የሚፈራረሙት 107 የፓለቲካ ፓርቲ እና ከድርጅቶች መሆናቸውም ታውቋል።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Happening_now

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳና አጣዬ ከተማ አስተዳደር እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ነዋሪዎች መካከል ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት #በእርቅ_ለመፍታት ያለመ የሰላም ውይይት መካሄድ ጀምሯል።

የሰላም ውይይቱ እየተካሄደ የሚገኘው በአጣዬ ከተማ ነው።

የእርቀ ሰላም ውይይቱን ሌተናል ጀኔራል ደስታ አብቼ እየመሩት ይገኛሉ።

በተጨማሪ የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ አህመድ ያሲን ፣ የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጀማል ሀሰን እና የአጣዬ ከንቲባ አቶ አገኘሁ መክቴ ከአወያዩቹ መካከል ይገኛል።

የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ነዋሪዎችና አመራሮች ፣ የአጣዬ ከተማ ነዋሪዎችና አመራሮች እየተሳተፉበት እንደሚገኙ ከሰሜን ሸዋ ዞን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia