TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.7K photos
1.56K videos
216 files
4.27K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ፣ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ከኢትዮጵያ መንግሥት የተበረከተላቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " አልቀበልም " ብለው መልሰው ከመድረክ መውረዳቸው ይታወሳል። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር " ገንዘቡ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ ይሆናል። ምክንያቱም ስጦታ በግድ ውሰዱ ስለማይባል " ሲል ለኤፍ ኤም 97.1 ተናግሯል። አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ፤ ለሙያውና…
#GemedoDedefo

ከፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ እጅ የተሰጣቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " የኛ የአሰልጣኞችን ልፋት አመጥንም " ብለው ሳይቀበሉ የቀሩትና በኃላም " እዛ ቦታ ላይ ያን ማድረግ አልነበረብኝ ፤ ተሳስቻለሁ " በማለት ህዝቡን እና ፕሬዜዳንቷን በይፋ ይቅርታ የጠየቁት አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ዛሬ " ታስረዋል " ከሰዓታት በኃላ ደግሞ  " ከእስር ተፈተው ወደ ቤት ገብተዋል " የሚሉ መረጃዎች ሲሰራጩባቸው ነበር።

እሳቸው ግን " እኔ አልታሰርኩም ፤ እስር ቤትም አልነበርኩም  " ሲሉ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ዙሪያ ታማኝ ነው የሚባለው ጋዜጠኛ ኤቢሳ ነገሰ አሰልጣኙን በስልክ እንዳገኛቸውና " ጉዳዩም እንደሚባለው እንዳልሆነ "  ገልጿል።

እሳቸው አሰልጣኝ ገመዶም እስር ቤት እንዳልነበሩ ቃላቸውን እንደሰጡት አመልክቷል።

" እኔ አልታሰርኩም " ማለታቸውን ጋዜጠኛው አሳውቋል።

በሌላ በኩል አሰልጣኙ በራሳቸው የፌስቡክ ገጽ መታሰራቸው " ውሸት ሀሰተኛ ዜና " እንደሆነ እና ቤታቸው እንደሚገኙ ገልጸው ወዲያው ደግሞ አጥፍተውታል።

ጉዳዩን ከሚያውቁ ሌሎች አካላት በተገኘው መረጃ ግን አሰልጣኙ ታስረው እንደነበር ፤ ምሽት ላይ ግን መፈታታቸው ተሰምቷል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አሰልጣኙ " አልወስድም " ያሉት  ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ እንደሚሆን ማሰወቁ ይታወሳል። " ስጦታ በግድ ውሰዱ አይባልም " ነው ያለው።

@tikvahethiopia