TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ደራርቱ_ቱሉ #ቴዎድሮስ_ካሳሁን

ትናንት ምሽት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ልዩ የዕውቅና ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል፦

• ፍልቅልቋ ዝምተኛ ጀግና አትሌት ደራርቱ ቱሉ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት የኦሎምፒክ የወርቅ መዳልያ አሸናፊ በመሆኗ ከአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ልዩ ሽልማት አበርክቶላታል፡፡ እንዲሁም የዲሲ ከንቲባ ጽ/ቤት በክብር ሠርተፍኬት አበርክቶላታል፤

• ተወዳጁ አርቲስት ቴዲ አፍሮ ደግሞ በምሽቱ ሦስት ሽልማቶችን ተሽልሟል፡፡ በሙዚቃ ሥራው ለአፍሪካውያን ወጣቶች አርአያ በመሆኑ ከአፍሪካ ኅብረት ልዩ ዋንጫ ሲሸለም፤ የዲሲ ከተማ ከንቲባም የእውቅና ሠርተፍኬት አበርክቶለታል፡፡

የሜሪላንድ ኢትዮጵያውያንም ለቴዲ አፍሮ ልዩ ስጦታ ሰጥተውታል፤ ቴዲ አፍሮ (ድምጻዊ ቴድሮስ ካሳሁን) ባደረገው ንግግር፤ ሽልማቱን ላበረከቱለት ሁሉ አመስግኖ ሽልማቱን ለአፍሪካውያን ወጣቶች መታሰቢያ እንዲሆን አበርክቷል፤

Via #GETU_TEMSEGEN
@tsegabwolde @tikvahethiopia