TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Fagta

በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በሰብል ላይ ከባድ ጉዳት አደረሰ።

በአዊ ብ/አስተዳደር በፋግታ ለኮማ ወረዳ በጋፈራ እና በዘበላ ግራይታ ቀበሌ በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በመከር ሰብልና በመስኖ ሰብል ከባድ ጉዳት ማድረሱን ተጎጂ አርሶ አደሮች ተናግረዋል።

ጉዳት ከደረሰባቸው የመኸር ሰብሎች መካከል ጤፍ ፣ ስንዴ፣ አተር እና ገብስ እንዲሁም በመስኖ ድንች፣ የጓሮ አትክል ይገኙበታል።

የፋግታ ኮሙዩኒኬሽን ፥ የጉዳት መጠኑን በተመለከተ ተጣርቶ በቀጣይ እንደሚገልፅ አሳውቋል።

@tikvahethiopia