TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FDREDefenseForce

የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመሰረታዊ ውትድርና ያሰለጠናቸውን 2ኛ ዙር ምልምል ወታደሮች እያስመረቀ ይገኛል።

ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት ለውትድርና ሙያ ብቁ የሚያደርጋቸውን የመሰረታዊ ውትድርና ስልጠና ወስደው ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።

በምርቃት ስነስርቱ ላይ የተገኙት የምድር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ለተመራቂ ወታደሮቹ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

ጀኔራል መኮንኖች፣ የትምህርት ቤቱ አዛዥ ኮ/ል አዲሱ ተርፋሳ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል ፤ ከሀገር መከላከያ እና ለኢዜአ እንደተገኘው መረጃ።

NB : የሁርሶ የሰላም ማስከበር ማዕከል በምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኝ እና አንጋፋ ከሚባሉት ማሰልጠኛዎች መካከል ተጠቃሽ ነው።

@tikvahethiopia
👍1
#FDREDefenseForce

የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በህወሓት ተይዘው የነበሩ ቦታዎችን ማስለቀቁን አስታወቀ።

የመከላከያ ሰራዊት ከአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና የአማራ ሚሊሻ ጋር በመሆን በወሰደው እርምጃ፦ ጋሳይ፣ ክምር ድንጋይ፣ ጎብጎብ፣ ሳሊና ንፋስ መውጫ ነፃ ማውጣቱን ገልጿል።

የንፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪዎች ህወሓት በንፋስ መውጫ ከተማ ንፁሃንን መግደሉንና በርካታ ውድመት ማድረሱን የተናገሩ ሲሆን ሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደከተማቸው ሲገባ አቀባበል አድርገዋል።

በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አንደኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ፤ ከሰሞኑን ህወሓት ህዝቡን በጣም እንደጎዳው፤ የቀረ ነገር ሳይኖር ዘርፊያ እንደፈፀመ ገልፀው፥ "ህዝባችን እንዲህ ያለ ወራዳ ተግባር ማየቱ የሚያሳዝን ነው፤ ነገር ግን አሁን ላይ ቡድኑ ዋጋውን እያገኘ ነው" ብለዋል።

ብርጋዴር ጄነራል ብርሃኑ፥ "ህወሓት በወረራ የያዛቸውን ቦታዎች በሙሉ የማስለቀቅ እና የማፅዳት ስራ እየተሰራ ነው ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ከመኪና ወርዶ እየተበታተነ ነው እሱን የመልቀም ስራ እየተሰራ ነው፤ የሚሸሽበትም መንገድ ተዘግቷል፤ ትግራይ ውስጥ ያየውን ጉድ እዚህም ያየዋል፤ እዚህ ገብቶ መውጣት የሚባል ነገር እንደሌለ ያየዋል" ብለዋል።

አዛዡ ፥ ህወሃት ስርዓት መቀየር ነው ፍላጎቴ ይላል እንጂ ተግባሩ ሀገር ማፍረስ እና ሀገር ማውደም ነው ፣ ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው የማፍረስ ምልክቱም ህዝቡን ምን እያረገው እንዳለ ማየት በቂ ነው ፤ የከተማውን ህዝብ ጠይቁ ምን አድርጓቸው እንደሄደ፤ እነሱ የስርዓት አራማጅ አይደሉም ፤ ድሆች ናቸው ፤ ከድሆቹ አፍ ነጥቆ ሽሮ ሳይቀር እየጫነ እየወሰደ ያለው" ሲሉ አስረድተዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/ENDF-08-23

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ የጦር ፍርድ ቤት በሀገር እና በሀገሪቱ ሰራዊት ላይ ክህደት በመፈፀም ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ባላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ቅጣት አስተላልፎባቸዋል።

ተጠርጣሪዎቹ የተከሰሱበት ክስ ዋና ጭብጥ ምንድናቸው ?

- ከሀገር አፍራሽ አሸባሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት በመፍጠር የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል፣
- ክህደት በመፈፀም ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀውን የህወሓት ቡድን ለመቀላቀል በማሴር፣
- ሽብርተኛ ተብሎ ለተፈረጀው የ "ሸኔ" ቡድን መረጃ ማቀበል፣
- ከግዳጅ ቀጠና በመሸሽ የወገን ጦርን ለአደጋ ማጋለጥ፣
- ያለ በቂ ምክንያት ሲቪሎችን በመግደል፣
- የበላይን ትዕዛዝ ችላ በማለት ለንፁሐን ሞት ምክንያት መሆን
- የመንግሥትና የህዝብን ወታደራዊ ንብረትን ይዞ ለመሸሽ ሙከራ ማድረግ የሚሉ ክሶች ዋነኛ ጭብጥ ሆነው ቀርቧል፡፡

ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ሲመረምር ቆይቶ ተከሳሾች እራሳቸውን መከላከል ባለመቻላው የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

1. ሻለቃ ክፍሌ ካሳይ በ17 አመት ፅኑ እስራት
2. ኮሎኔል ክፍሌ ፍሰሃዬ በ14 ከ 2 ወር ፅኑ እስራት
3. ሀምሳ አለቃ መብራቱ ጥላዬ በ18 አመት ፅኑ እስራት
4. መሰረታዊ ወታደር መኮንን ክንፈ በ13 አመት ፅኑ እስራት
5. ሀምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ በ11 አመት እስራት
6. ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ በ11 አመት ፅኑ እስራት
7. ምክትል ክፍሌ ንጉስ በ9 አመት ፅኑ እስራት
8. ኮሎኔል ካሱ ሀብቱ በ11 አመት ከ2 ወር
9. ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ በ8 አመት ፅኑ እስራት
10. ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ በ10 አመት ከ2 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወታደራዊ ፍ/ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

@tikvahethiopia
👍1
#GERD #FDREDefenseForce

ሀገር መከላከያ ሰራዊት፥ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ግዙፉን የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረውን የህወሓት ቅጥረኛ ሃይል ደመሰስኩኝ አለ።

የግድቡን ግንባታ ለማደናቀፍ ተልዕኮ ውስደው የተንቀሳቀሱና ሰራዊቱ የማያዳግም እርምጃ የወሰደባቸው ኃይሎች (የተገደሉ) በቁጥር 50 ሲሆኑ ፤ ከ70 በላይ የሚሆኑት ቁስለኛ ሆነዋል።

መከላከያ ሰራዊት ፥ እርምጃ የወሰደበት ኃይል የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ መሞከሩን ነገር ግን መቋቋም ተስኖት መበታተኑን አሳውቋል።

ይኸው ጥፋት ሊፈፅም የነበረው ኃይል ይጠቀምባቸው የነበሩ ቀላል እና ከባድ የቡድን መሳሪያዎች፣ ፈንጂዎች ወድመዋል ፤ የተቀሩትን ሰራዊቱ ተቆጣጥሯቸዋል።

የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮ/ል ሰይፈ ኢንጊ ፣ "አሸባሪው ሕወሃት በግንባር ድል አልቀና ሲለው አብዛኝው ጦር ወደ ሰሜኑ ክፍል አቅንቷል በሚል ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅቶ የህዳሴ ግድባችንን ስራ ለማስተጓጎል ለማጥቃት ቢሞክርም አልተሳካለትም" ብለዋል።

በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሃይል፣ እግረኛና ሜካናይዝድ ክፍለጦሮች እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይሎች አስፈላጊውን ዝግጁነት በማረጋገጥ ግዳጃቸውን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የኢትዮጵያ ጦር ዛሬ በሰጠው መግለጫ በጄነራል ምግበይ ይመራል ያለውን " አርሚ 1 " የተባለ ኃይል ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን በይፋ አሳወቀ።

የዛሬውን መግለጫ የሰጡት የመከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊት ግንባታ ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ግዳጅ አፈጻጸምና ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት ህፃናትን አሰልፎ በአማራ ክልል ወረራ መፈፀሙን ያነሱት ሌ/ጄነራል ባጫ የቡድኑ ፍላጎት ኢትዮጵያ የምትባልን ሀገር መበታተን ነው ብለዋል።

ህወሓት ስልጠና ያልወሰዱ ህፃናትን ወደ ጦርነት በመማገድ ላይ ነው ሲሉም አክለዋል።

ሌ/ጄነራሉ በመግለጫቸው ፥ ህወሓት በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶችን አሰልፎ በ4 አርሚ ራሱን በማደራጀት በአማራ ክልል የሚያደርገውን ወረራ እንደቀጠለ ጠቁመዋል።

በ4 አርሚዎች ካደራጃቸው ኃይሎች መካከል አንደኛው በጀነራል ምግበይ የሚመራ ሲሆን ይህ ኃይል አርሚ 1 ተብሎ የሚጠራ እንደሆነ አስረድተዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ ይኸው ኃይል በሁመራ አካባቢ አደርቃይ እና ማይጠብሪ አካባቢ ደባርቅንና ዳባትን በመቁረጥ ጎንደርን በመያዝ ከዚያ በኋላ ሁመራን ነፃ ለማድረግ ቢንቀሳቀስም ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል ብለዋል።

በ3 ክፍለ ጦሮች የተደራጀው ይህ የአሸባሪ ኃይል በእያንዳንዱ ክፍለ ጦር ስር ሶስት ኮሮችን ያቀፈ ሲሆን ሰሞኑን በተደረገ ውጊያ ከ5 ሺ 600 በላይ ሙት ከ2 ሺ 300 በላይ ደግሞ ቁስለኛ ሲሆኑ ፣ 2 ሺ አባላቱ ተማርከው ቀሪዎቹም ተበታትነውበታል።

በዚህም ህወሓት ወደሱዳን ለመውጣት ያቀደው ሙከራ ሳይሳካለት ቀርቷል ፥ ሙሉ በሙሉም ተዘግቶበታል ሲሉ ተናግረዋል።

More : telegra.ph/FDRE-Defense-Force-09-04

@tikvahethiopia
🤔1
#FDREDefenseForce

መከላከያ ሰራዊት ሲጠቀምባቸው የነበሩ የማዕረግ ምልክቶች ላይ ማሻሻያ አድርጓል።

በምልክቶቹ ውስጥ ጋሻና አንበሳን ጥቅም ላይ ማዋሉን ነው የተገለጸው።

ማሻሻያ ያስፈለገው የሠራዊቱ ማዕረግ አገራዊ ይሁን ወታደራዊ ታሪካዊ ይዘት ያለውና የሠራዊቱንም ባህሪ ሊገልፅ የሚችል ሆኖ እንዲዘጋጅ በማስፈለጉ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
👍662👎210😁12344🔥18🎉10🤩10😢1
#HappeningNow

በአሁኑ ሰዓት የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት የአውደ ውጊያ ውሎ የሜዳሊያ ሽልማት እና አዲሱ የመከለከያ ጠቅላይ መምሪያ ህንጻ ምረቃ እየተከናወነ ይገኛል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የሰልፍ እና የአየር ትርዒትም ቀርቧል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👎873👍54851🔥23🎉12🤩10😢7😁3
#Update

ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦

1. ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
2. ጀነራል አበባው ታደሰ
3. ጀነራል ባጫ ደበሌ
4. ሌ/ጀ አለምሸት ደግፌ

የአደዋ ድል ጀግና ከፍተኛ ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦

1. ጀነራል ጌታቸው ጉዲና
2. ሌ/ጀነራል በላይ ስዩም
3. ሌ/ጀነራል ዘውዱ በላይ
4. ሌ/ጀነራል መሰለ መሠረት
5. ሌ/ጀነራል ሹማ አብደታ
6. ሌ/ጀነራል አብዱራህማን እስማኤል
7. ሌ/ጀነራል ይልማ መርዳሳ
8. ሌ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ

የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት የመዘከሪያና የመከላከያ ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት የማስመረቅ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

#PMOEthiopia #FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👎920👍86548🎉36😁33🔥19🤩18
#FDREDefenseForce

የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን ሶስተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ ነው ስራውን ሰርቶ ያጠናቀቀው።

ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ የነበረ ሲሆን በተከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች #በአንድ_ቀን ለመድረስ ይችላሉ ተብሏል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia
👍8👎2
#ETHIOPIA #GERD

" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ

የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።

የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።

" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው  " ብለዋል።

ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።

የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።

ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👍1.3K👎91🕊5336🙏32😢29🤔26🥰17😱15
#FDREDefenseForce

የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ ምን አሉ ?

" ለኢትዮጵያ ዕድገት እንቅፋት ለመፍጠር የሚጥሩ በአካባቢያችን ያሉ #ታሪካዊ_ጠላቶቻችን እና #አዳዲስ_ኃይሎች እየተሰባሰቡ እንዳለ እያየን ነው።

እነኝህ ጠላቶች ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ በቅርበት እየተከታተልን እንገኛለን።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የማንንም ሃገር ብሔራዊ ጥቅም መንካት ተገቢ አለመሆኑን በማመን በዘመኗ የሌላ ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ነክታ አታውቅም አሁንም አትነካም ታሪኳም አይደለም።

የሌላን ሀገር ብሔራዊ ጥቅም እንደማንነካው ሁሉ እኛም የሃገራችንን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም።

ለሃገራችን ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም ዘብ እንቆማለን። "

ጄነራሉ ይህን የተናገሩት " አዋሽ አርባ " የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሜካናይዝድ ጦርን እና እየወሰደ ያለውን ስልጠና ከጎበኙ በኃላ ነው።

ሰልጣኞቹ በስነ-ልቦና ዝግጁነት ብቁ በመሆን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር መረጋገጥ ሲባል የሚወስዱትን ሙያዊ ስልጠና በፍጥነት ማጠናቀቅና ለሚሰጣቸው #ማንኛውም_ግዳጅ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው #አፅንኦት ሰጥተዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
😡1.3K859🕊158🙏110😭68😱31😢30🥰24
" እንደ ታላቁ የህዳሴ ግድባችን ሁሉ የቀይ ባህር ተልማችንንም ዕውን አድርገን ወሽመጣቸውን ዳግም እንቆርጠዋለን " - ሀገር መከላከያ ሰራዊት

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ባሰራጨው አንድ ፅሁፍ ፤ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለሀገር ስኬት ሁሌም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጿል።

ሰራዊቱ ባወጣው ፅሁፍ ፤ ስማቸውን በግልፅ ያልጠራቸው እና " #እነሱ " ሲል የጠራቸው አካላት " እንደ ጦስ ዶሮ ዙሪያችንን እየዞሩ የብሄራዊ ጥቅማችንን ማረጋገጫ መንገዶች ሁሉ ለመዝጋት ከመፍጨርጨር ቦዝነው ያወቁበት የታሪክ አጋጣሚ የለም " ብሏል።

" አንዳንዴ ከራሳቸው ስኬት በላይ የእኛ በጠና መቸገርና መጎሳቆል በእጅጉ የሚያረካቸው እስኪመስል ድረስ ሀገራዊ የተስፋ ብርሃናችንን ለማጨለም ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም " ሲል ገልጿል።

" አባይን ለሺህዎች ዘመናት ለብቻቸው እንዳሻቸው ሆነውበታል። ለምተው አድገው ሀገራቸውን በጠንካራ መሠረት ላይ አቁመውበታል " ያለው ሰራዊቱ " እኛ ይህ ለምን ሆነ የሚል በከንቱ ምቀኝነት ብቻ ተነሳስተን ያደረግነው አንዳችም ነገር የለም " ሲል አስረድቷል።

" ለኢትዮጵያም ሆነ ለእነሱ ወንዝ ብቻ ያልሆነው አባይ እነሱን ሲያስውብ እኛን ሲያገረጣ ለብዙ ጊዜያት ቆይቷል " ያለው ሰራዊቱ ፤ " እውነት ከእነሱ ቅጥ ያጣ ስጋትና ራስ ወዳድነት በሚመነጭ ሴራ እየተጎነጎነልን በዚህም ዋጋ ከፋዮች ሆነን መቆየታችን ስናስበው የሚተናነቀን መራር እውነት ነው " ብሏል።

ኢትዮጵያ ጥቅሟን በሌሎች መጉዳት ላይ መመስረት እንደማትፈልግም ገልጾ ሁሌም " ማንም ሳይጎዳ እኔም በድርሻዬ ልጠቀም " በሚል መርህ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ይህን ማረጋገጥ መቻሏን አስታውሷል። በዚህም እነዚህ አካላት ወሽመጣቸው መቆረጡን ገልጿል።

ይህን ተከትሎ ፤ " ከቀጠና እስከ አህጉር፣ ከአህጉር እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ብዙ ማስነው ሊያስቆሙት ያልቻሉት ታላቁ የህዳሴ ግድብ አሁን ' የተበላ እቁብ ሆኖባቸዋል ' " ብሏል

" እነዚሁ አካላት አሁን ደግሞ የሶማሊያ ' አዛኝ ቅቤ አንጓች ' ሆነው ብቅ ብለዋል " ያለው ሰራዊቱ " የህዳሴ ግድቡስ እሺ ከአባይ ጋር ተያያዘ እንበል። ከወዳጅ ጎረቤታችን ሶማሌላንድ በቀይባህር የባህር በር እና የባህር ሃይል ቤዝ እንዲኖረን በምትኩም ሶማሌላንድን ተጠቃሚ የሚያደርግ የምንሰጠው ኖሮን ተስማማን። ታዲያ እንዴት ቀይባህር ውስጥም አባይ ሊታያቸው ቻለ ? ... ይህ ታሪካዊ ጠላትነት ካልሆነ ምን ይባላል ? " ሲል ጠይቋል።

መከላከያ ባወጣው ፅሁፍ ፤ " የማይመጡበት የለም " ያላቸው እነዚህ አካላት " ከውስጥ በብሄር፣ በሃይማኖት በሌላም እንድንናቆር፣ ሁሌም በአዙሪት እንድንዳክር.. ይተጋሉ። መቼም አይተኙልንም " ብሏል።

" እኛም እንደ ታላቁ የህዳሴው ግድባችን ሁሉ የቀይ ባህር ተልማችንንም ዕውን አድርገን ወሽመጣቸውን ዳግም እንቆርጠዋለን። እኛ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለሀገራችን ስኬት ሁሌም ዝግጁ ነን " ሲል አሳውቋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
2.17K😡546👏136🕊114🙏67😭58😱39😢38🥰21🤔1
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስገነባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዛሬ ለባለ ዕድለኞች በእጣ ያስተላልፋል።

ፋውንዴሽኑ ከዚህ በፊት ተመዝግበውና ቆጥበው መመዘኛውን አሟልተው ለተገኙ የሠራዊት አባላትና ስቪል ሠራተኞች 1236  ቤቶችን በእጣ አስተለልፎ ነበር።

ዛሬ ደግሞ 1336 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በእጣ ያስተላልፋል ተብሏል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👏425😡10483🤔30🕊12😱6🙏6🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስገነባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዛሬ ለባለ ዕድለኞች በእጣ ያስተላልፋል። ፋውንዴሽኑ ከዚህ በፊት ተመዝግበውና ቆጥበው መመዘኛውን አሟልተው ለተገኙ የሠራዊት አባላትና ስቪል ሠራተኞች 1236  ቤቶችን በእጣ አስተለልፎ ነበር። ዛሬ ደግሞ 1336 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በእጣ ያስተላልፋል ተብሏል። #FDREDefenseForce @tikvahethiopia
የመከላከያ_ሠራዊት_ፋውንዴሽን_የቤት_ባለዕድለኞች_ዝርዝር.pdf
11.1 MB
መከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያሥገነባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዛሬ ለባለ ዕድለኞች በዕጣ አስተላልፏል።

በዕጣ የተላለፉት አጠቃላይ 1,336  የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፦
- ባለ 4 መኝታ
- ባለ 3 መኝታ
- ባለ 2 መኝታ
- ባለ 1 መኝታ ናቸው።

የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ለሠራዊት አባላት እና ቋሚ ለሆኑ ስቪል ሰራተኞች ነው የተላለፉት።

(የቤት ባለዕድለኞች ስም ዝርዝር ከላይ በPDF ተያይዟል)

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👏195😡6551🙏18🕊14🤔11🥰7😢7😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የሀገር መከላከያው ስለ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንቅስቃሴ ምን አለ ?

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነትን መሰረት በማድረግ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሀገር መከላከያው ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እንዲያስተባብር አቅጣጫ ተሰጥቶ እየሰራ እንዳለ አመልክተዋል።

የፀለምት እና አካባቢው ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ኃላፊነት የተሰጠው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መሆኑን ተናግረው " ስራው እጅግ በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው " ብለዋል።

ዛሬን ረቡዕ ጨምሮ ባለፉት ቀናት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቄያቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ሌ/ጄነራሉ ፥ ተፈናቃዮች እየተመለሱ ያሉት አስፈላጊና መሟላት አለባቸው የተባሉ ቅድመ ሁኔታዎች ከጎን እየተሰሩ ነው ብለዋል።

ስራው በፍጥነት እየሄደ ያለው አብዛኛዎቹ አርሶ አደር የክረምቱ ወቅት ሳያልፍ እርሻውን እንዲሰራና ህይወቱን እንዲመራ በማሰብ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በፀለምት ካሉ 25 ቀበሌዎች አብዛኛው ተፈናቃይ ከ22 ቀበሌዎች ነው አሁን ባለው ሁኔታ በአስራዎቹ ቀበሌዎች ተፈናቃይ ተመልሷል ፤ እስከዚህ ሳምንት መጨረሻ ቀሪ 11 ቀበሌዎች  አብዛኛው እንዲገባ ይደረጋል ሲሉ አሳውቀዋል።

የቀረውም ስራ በቀጣይ ይሄዳል ብለዋል።

ስለ ታጣቂዎች መውጣት ምን አሉ ?

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የትግራይ ታጣቂዎች በኃይል ገብተዋል " ስለሚባለው ጉዳይ ሌ/ጄነራሉ ፥" ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ በፀለምትም ይሁን በወልቃይት በኃይል የገባባቸው ቦታዎች የሉም " ሲሉ መልሰዋል።

ፀለምት ካሉት ቀበሌዎች 3 ቀበሌዎች ላይ የትግራይ ታጣቂዎች እንዳሉ እነዚህም ጦርነት ሲቆም ባሉበት የቆሙ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።

ባለው መግባባት ከሁለቱም ክልል ጋር የሁለቱም ክልል ታጣቂ መውጣት ስላለበት ተፈናቃዮችን በመመለስ ታጣቂዎቹን የማስወጣት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ፀለምት ያለው የትግራይ ታጣቂ እንዲወጣ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ እንዳይመለስ ስለሚሰራ ስራ ምን አሉ ?

በአማራ በኩል " ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ ይገባል " የሚል ስጋት እንዳለ ያልሸሸጉት አዛዡ ፥ በትግራይ በኩልም " ታጣቂዎች (በአማራ በኩል ያሉ) እንደ አዲስ ተደራጅተዋል ስጋት ናቸው " የሚል ነገር እንዳለ ገልጸዋል።

" የሀገር መከላከያው ከሁለቱም በኩል ከተፈናቃዮች እና እዛው ከነበሩት ነዋሪዎች ( ካልተፈናቀሉት ) ሽማግሌዎች እንዲውጣጡ አድርጎ የተፈናቃዮችን ዝርዝር ለመከላከያ ተሰጥቶ ከዛም መከላከያው ከሽማግሌዎቹ ጋር አብሮ ሰዎቹ የዛ ቦታ ነዋሪ መሆናቸውን እየጠየቀና እያረጋገጠ ተፈናቃዮች ይመለሳሉ " ብለዋል።

' ይሄ ታጣቂ ነው ፣ ይሄ ሚሊሻ ነው ' የሚል ክርክር በሽማግሌ ደረጃ ከተነሳ ወደ ህዝብ ተወስዶ ህዝቡ እራሱ ይፈርዳል ሲሉ ተናግረዋል።

" እንግዳ ሰው ሲገባ ይታወቃል ይህ ጉዳይ አሳሳቢ አይደለም " ያሉት አዛዡ ፥ ገጠር ይሁን ከተማ መሬት ከሌላቸው / ሊገቡበት የሚችሉበት ቤት ከሌላቸው ተለይቶ ይታወቃል ብለዋል።

#Ethiopia
#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👏333😡213114🕊41🥰13🤔10😱9😢9🙏6😭6
" በይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል " - ሀገር መከላከያ ሰራዊት

ሀገር መከላከያ ሠራዊት " 178 የትግራይ ተወላጅ የሠራዊት አባላት ከዛሬ ጳጉሜን 5/2016 ጀምሮ ከእስር በይቅርታ እንዲለቀቁ ተወስኗል " ሲል አሳወቀ።

መከላከያ በአዲስ ዓመት ይቅርታ የተደረገላቸው የህወሓት ታጣቂ ሃይሎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ/ም የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መከፈታቸውን ተከትሎ የተሰጣቸውን ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ ወደ ጎን በመተው በሰራዊቱ እና በህዝብ ጥቅሞች ላይ ወንጀል የፈጸሙ ናቸው ብሏል።

" ጉዳያቸው በወታደራዊ ፍትህ ስርዓቱ አማካኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በተከሰሱበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ምክንያት በወታደራዊ ፍርድ ቤቶች እስከ ሞት ቅጣት ተወስኖባቸው በማረሚያ ቤት ይገኙ ነበር " ሲል አስረድቷል።

ሀገር መከላከያ " እኚሁ የሠራዊት አባላት በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው የይቅርታ ጥያቄአቸውን ለመንግስት እና ለመከላከያ ሚኒስቴር አሥገብተዋል " ሲልም አክሏል።

በዚህም በአዲሱ ዓመት በይቅርታ 178ቱ የትግራይ ተወላጅ የሠራዊት አባላት ከዛሬ ጀምሮ ከእስር እንዲለቀቁ መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
737😡389🕊115🙏82😭70🤔68👏33😱19😢16🥰11
TIKVAH-ETHIOPIA
" መልሼ አጤነዋለሁ " - ሶማሊያ የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ መካተታቸውን በተመለከተ " መልሶ ለማጤን " ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል። አንድ የሶማሊያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ " የሶማሊያ መንግሥት ለልዑኩ ኅይል ከሚያዋጡት ሀገራት ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ወታደሮችን አግኝቶ ደልድሏል " ሲሉ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ…
#Ethiopia #Somalia

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የ #AUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳወቀ።

በመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጉ ተነግሯል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሰራጨው መረጃ ፥ የልዑካን ቡድኑ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ማህሙድ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።

ከኢፌዴሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ  (ዶ/ር) ለፕሬዚዳንቱ የተላከ መልዕክትን አድርሰዋል።

" በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሶማሊያ እና በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋትን ለማረጋገጥ በጋራ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል " ያለው ሚኒስቴሩ " ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የAUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል " ሲል ገልጿል።

በቅርቡ የሶማሊያ ከፍተኛ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ ውይይት ለማካሄድ መስማማታቸውም ተመላክቷል።

የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አብድርቋድር ኑር ጃማ ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሶማሊያን ሰላም ለማረጋገጥ ለከፈለው መስዋትነት እና ላበረከተው አስተዋጽዖ ያላቸው አክብሮት እና ምስጋና ማቅረባቸው ተነግሯል።

#MinistryofForeignAffairsofEthiopia
#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
224🤔60🕊37😡18👏15🙏14🥰6😢5😱3😭3
#ADWA129

129ኛዉ የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል " በሚል መሪ ኃሳብ እንደሚከበር የሀገር መከላከያ ሰራዊት አስታውቋል።

የመከላከያ ስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜ/ጀነራል እንዳልካቸው ወ/ኪዳን ፥ " በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ኮሚቴ ተቋቁሞ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።

ከበዓሉ ቀደም ብሎም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ሚሲዮኖች ጭምር እንደሚከበር ጠቁመዋል።

" ዓድዋ የጋራ ድል፣ የአንድነት፣ የአላማ ፅናት እንዲሁም የአሸናፊነት ምሳሌ በመሆኑ የአባቶችን አርበኝነት በመያዝ ዘመኑ የሚጠብቅብንን ኃላፊነት መወጣት አለብን " ብለዋል።

#FDREDefenseForce #FMC

@tikvahethiopia
451😡202👏34🕊23🙏20😭7🥰6😱5😢5
TIKVAH-ETHIOPIA
" የቤተክርስቲያን ማሳ እያረሱ በነበሩ ሰዎች ላይ ጥቃት ተፈፅሞ የአንድ አርሶ አደር ሕይወት ጠፍቷል " - የኮሬ ዞን ጎርካ ነዋሪዎች እና የሃይማኖት አባቶች ባሳለፍነዉ ቅዳሜ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ " ጃሎ " ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በታጠቁ ሃይሎች በተፈፀመ ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ይታወቃል። ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት ገደማ በወረዳዉ " ዳኖ ቡልቶ " ተብሎ በሚጠራው አከባቢ…
" ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ይደረጋል፤ መንገዱ ክፍት የሚደረገው ግን የፀጥታ መዋቅር በሚያስቀምጠው የሰዓት ገደብ ነው " - አቶ ወገኔ ብዙነህ

በደቡብ ኢትዮጵያ እና ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አዋሳኝ አካባቢዎች የሚታየውን የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለ የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ መካሄዱ ተሰምቷል።

በምክክር መድረኩ ህዝብ መካከል ያሉ የተደራጁ ንብረት ዘራፊዎች እና ነፍስ አጥፊዎች ላይ የህግ የበላይነት ማስከበር እንዲሁም ሀገር መከላከያ ሠራዊት ኦፕሬሽን አድርጎ አካባቢውን ለማፅዳት የሚሰራውን ስራ ማገዝ ከዛ ባለፈ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እዲጠናከርና ሰላም እንዲፀና መስራት ይገባል ተብሏል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች እነማን ነበሩ ?

- የሀገር መከላከያ ሰራዊት
- የኮሬ ዞን
- የቡርጂ ዞን
- የምዕራብ ጉጂ ዞን
- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ

ምን ተባለ ?

የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ፤ መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለመጀመር ወሳኝ እና ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።

በኮሬ ዞን በኩል እየተሰራ ባለ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ የፀጥታው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቁመዋል።

የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኣቶ ዳኜ ሂዶ ፤ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ሁሉ። መዋቅሮች ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ ፤ መድረኩ አላማው የተሳሳቱ አመለካከቶችን ማስተካከል ጥርጣሬ በማስወገድ ግልፀኝነት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል።

በቀጣይ የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጠናከር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽን ማድረግ፣ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከር ላይ ይሰራል ብለዋል።

ሶስቱም ዞኖች በጋራ ሆነው የቆመው የፍስሃ ገነት - ኬሌ - ነዳሌ የአስፋልት መንገድ እንዲጀመር መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት 37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ ፤ ቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝ ከቀበሌ አንስቶ የህዝብ አመለካከት ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ህዝቡ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ ማድረግ ፣ ፀረሰላም ኃይሎች የሚንቀሳሰቁባቸውን ቀበሌያት ወሰን አካባቢ ህዝባዊ ሰራዊት እና ሚሊሻ ማደራጀት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በሰላም ግንባታ ላይ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሚናቸውን እንዲጫወቱ ጠይቀዋል።

መከላከያ ለሚሰራው ኦፕሬሽን አዋሳኝ ቀበሌያት ያለው ህዝብ እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ፥ " የተጀመረውን የአመራር ለአመራር እርስ በእርስ ግንኙነት ለማደናቀፍ የሚሰራ ፀረ ሰላም አለ " ብለዋል።

በመሆኑን የፀጥታ መዋቅሩ በተጠንቀቅ መቆም አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሁለቱም መዋቅር አመራርና ፀጥታ አካላት እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት በጋራ ተስማምተው በሚያስቀምጡት የሰዓት ገደብ መሰረት ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።

" ከዛሬ ጀምሮ በቀጠናው የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ንብረት የሚዘርፉ በኮሬ፣ ቡርኪና ጉጂ ስም የሚነግዱ ህገወጦች ወደ ቤት ግቡ " ሲሉ አሳስበዋል።

#KooreZone #BurjiZone #WestGujii #FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
149🙏23😡23🕊18👏15🤔10🥰3😢3💔3😱1😭1
TIKVAH-ETHIOPIA
ነዋሪዎች እየተካሄደ ነው ስላሉት አፈሳ ምን አሉ ? በተለያዩ ከተሞች ወጣቶች በግዳጅ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየተያዙ እየተወሰዱ መሆኑን ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው በባህር ዳር፣ አዴትና ሞጣ እንዲሁም ጋይንት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች " በ20ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ያሉ ወጣቶችን የመከላከያና የአድማ ብተና መለዮ የለበሱ የመንግስት የፀጥታ አካላት ወጣቶችን እያፈሱ እስር…
የመከላከያ እና የኢሰመኮ ምላሽ ምንድነው ?

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮረኔል ጌትነት አዳነ ከቀናት በፊት በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳይ ላይ ለመከላከያ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ላይ የሰራዊት ምልመላን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

" የመከላከያ ሰራዊት ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ ነገር የሚወጣን ሰው ለመተካት እንዲሁም ሚዛን የጠበቀ የኃይል አሰላለፍ ታሳቢ ያደረገ የሰራዊት ዝግጅት ያስፈልጋል " ሲሉ የምልመላ አስፈላጊነትን ጠቅሰዋል።

ኮ/ል ጌትነት፥ " ተቋሙ በሚያወጣው መደበኛ የምልመላ መስፈርት ወጣቶችን ወደ ሰራዊቱ መቀላቀል በየትም ዓለም አቀፋዊ አሰራር ያለ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ የምልመላ መስፈርቶች ብለው ካቀረቧቸው በዋናነት ፦
- ህገ-መንግስቱን የተቀበሉ፤
- ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ፤
- ሀገራቸውን ለማገልገል ሙሉ ፈቃደኛ የሆኑ፤
- ከማንኛውም ፖለቲካ ድርጅቶች ወገኝተኝነት ነጻ የሆኑ፤
- ስልጠናውን ከወሰዱ በኋላ 7 ዓመት ለማገልገል ውል የሚገቡ፤
- ከወንጀል ነጻ የሆኑ፤
- የሚወጡትን አካላዊ መስፈርቶች የሚያሟሉ የሚሉት በጥቂቱ የሚጠቀሱት ናቸው።

የምልመላ አሰራሩን በተመለከተ ዳይሬክተሩ ምን አሉ ?

የምልመላ ሂደቱ በወረዳ እና በቀበሌ ያሉ የፀጥታ እና የመስተዳድር አካላት በኮሚቴ ሆነው የሚያከናውኑት ነው ሲሉ አፈጻጸሙን በተመለከተም ለመከላከያ ሪፖርት የሚቀርብበት መሆኑን አንስተዋል።

ምልመላው የብሔር ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ መሆን ስላለበትም ከብሔራዊ ስታስቲክስ ቢሮ በተወሰደ ቁጥራዊ የክልሎች መረጃ መሰረት መከላከያ ለክልሎች ኮታ እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።

አፈጻጸምን በተመለከተ ኮ/ል ጌትነት " እንደ አቅሙ ነው " በሚል የገለጹ ሲሆን ከወረዳ እና ቀበሌ የተደረገው ምዝገባ እንዲሁ የሚወሰድ ሳይሆን በዞን ደረጃ እንዲሁም ማሰልጠኛ ሲደርሱ የማጣራት ሥራ እንደሚሰራም አንስተዋል።

በዚህም የክልሎች ተወካዮች ባሉበት ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተሰይሞ በፈቃዱ መምጣቱን ብቻ ሳይሆን ከተቀነሰም የተቀነስኩበት አግባብ ትክክል አይደለም ብሎ ቅሬታ ማቅረብ እንደሚቻል ነው ያነሱት።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ ምን አለ ?

በየአካባቢው የሚስተዋሉ የወጣቶች አፈሳ ስለመኖሩ ቅሬታ ደርሷቸው እንደሆነ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ክትትሉ አልቆ የወጣ የተጠናቀቀ ዶክመንት የለንም። ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ ይሄን ይዘ [ከቀናት በፊት] ከሀገር ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሞያዎች ጋር ተወያይተናል።

በእነሱ በኩል የምልመላ መስፈርቱ ላይ፤ የምልመላ አካሄዱ ላይ ምንም ችግር የለም ችግር ያለው ምንአልባት ታች አከባቢ የአስተዳደር አካላት ምልመላውን ሲያካሄዱ የሚፈጸሙ ትክክል ያልሆኑ አካሄዶች ካሉ በጋራ ለመስራት ተስማምተን ነው የተለያየነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኢሰመኮ ይህ ድርጊት ስለመፈጸሙ መረጃው ኖሮት ነው ውይይቱን ያደረገው ?

ዋና ኮሚሽነሩ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት ቃል ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን በመከተል አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እየተካሄደ መሆን አለመሆኑን እያጣራ እንደሚገኝ እና ሥራው ሲጠናቀቅ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በዚህም ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ ስታንደርዱን ጠብቆ የቀረበ ዶክመንት ወይም Standard of Proof ጨርሶ መደምደሚያ ላይ አለመድረሱን ጠቁመው ይህ ሲጠናቀቅ በየአራት ወሩ በሚወጣው ሪፖርት አካተው እንደሚያወጡ ተናግረዋል።

ውይይቱን በተመለከተ ግን ኮሚሽነሩ " ሚዲያ ላይ የምንሰማው ነገር ስላለ እሱን ይዘን ነው ከመከላከያ ሚኒስቴር ባለሞያዎች ጋር የተወያየነው " ሲሉ ውይይቱ በግል ተነሳሽነት ጭምር የተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

#FDREDefenseForce #EHRC

@tikvahethiopia
😡57880😭70🙏21💔17👏9🕊9🤔8🥰4😢4😱1