#EthiopiaElectricPower
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በትግራይ ክልል የ'ህግ ማስከበር ዘመቻ' ወቅት ጉዳት የደረሰባቸው ከተሞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት ለአሃዱ ሬድዮ ገለፀ።
መንግሥት በትግራይ ክልል ሲካሄድ የነበረውን የ "ህግ ማስከበር ዘመቻ" አጠናቅቅያለሁ ባለ ሰሞን በትግራይ ክልል ከተሞች የተቋረጠውን የቴሌኮምና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአጭር ጊዜ እንደሚመልስ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሁንም ድረስ በአክሱም ፣ በአድዋ፣ በሽረ እና በሌሎች ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት አስታውቋል፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለመመለስ በኤሌክትሪክ መስመሮቹ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ከፍተኛ ጥገና ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በመሆኑም ጥገናውን ለማድረግ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል እና ወጪ ከፍተኛ መሆኑ አገልግሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ተደራሽ ለማድረግ አስቸጋሪ እንዳደረገው ተናግሯል፡፡ ~ አሃዱ ሬድዮ ጣቢያ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በትግራይ ክልል የ'ህግ ማስከበር ዘመቻ' ወቅት ጉዳት የደረሰባቸው ከተሞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት ለአሃዱ ሬድዮ ገለፀ።
መንግሥት በትግራይ ክልል ሲካሄድ የነበረውን የ "ህግ ማስከበር ዘመቻ" አጠናቅቅያለሁ ባለ ሰሞን በትግራይ ክልል ከተሞች የተቋረጠውን የቴሌኮምና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአጭር ጊዜ እንደሚመልስ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሁንም ድረስ በአክሱም ፣ በአድዋ፣ በሽረ እና በሌሎች ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት አስታውቋል፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለመመለስ በኤሌክትሪክ መስመሮቹ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ከፍተኛ ጥገና ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በመሆኑም ጥገናውን ለማድረግ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል እና ወጪ ከፍተኛ መሆኑ አገልግሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ተደራሽ ለማድረግ አስቸጋሪ እንዳደረገው ተናግሯል፡፡ ~ አሃዱ ሬድዮ ጣቢያ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT