TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EthiopiaElectricPower

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በትግራይ ክልል የ'ህግ ማስከበር ዘመቻ' ወቅት ጉዳት የደረሰባቸው ከተሞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት ለአሃዱ ሬድዮ ገለፀ።

መንግሥት በትግራይ ክልል ሲካሄድ የነበረውን የ "ህግ ማስከበር ዘመቻ" አጠናቅቅያለሁ ባለ ሰሞን በትግራይ ክልል ከተሞች የተቋረጠውን የቴሌኮምና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአጭር ጊዜ እንደሚመልስ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡

ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሁንም ድረስ በአክሱም ፣ በአድዋ፣ በሽረ እና በሌሎች ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አዳጋች እንደሆነበት አስታውቋል፡፡

ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለመመለስ በኤሌክትሪክ መስመሮቹ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ከፍተኛ ጥገና ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

በመሆኑም ጥገናውን ለማድረግ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል እና ወጪ ከፍተኛ መሆኑ አገልግሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ተደራሽ ለማድረግ አስቸጋሪ እንዳደረገው ተናግሯል፡፡ ~ አሃዱ ሬድዮ ጣቢያ

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT