TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MeskelSquare

መስቀል አደባባይን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያየ።

ሰሞኑን በመስቀል አደባባይ የተደረገውን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መንፈሳዊና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ የተነሱ የመብትና የይዞታ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሁም አንቲባ አዳነች አቤቤ አስተላለፉት የተባለውን መልዕክት ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 3 ረፋድ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጉባኤ አካሒዷል።

በጉባኤውም ላይ ከፍ ሲል የተገለጸውን ርዕስ መሰረት በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ ክብርት ከንቲባዋ አርብ ጥር 6 ጠዋት አራት ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሚካሔደው ጉባዔ ላይ እንዲገኙና ማብራሪያ እንዲሰጡ ቀጠሮ አንዲያዝ አና ጉዳዩ በተረጋጋ መንገድ ውሳኔ እንዲያገኝ መመሪያ ሰጥቷል።

#EOCT

@tikvahethiopia
👍129👎21