#AfaanOromoo
ወደ አፋን ኦሮሞ እየተተረጎመ ባለው የቋንቋ ፖሊሲ ላይ ሰኞ ዕለት በኦሮሞ ባሕል ማዕከል ውይይት መካሄዱ ተገለጸ፡፡
ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ 5 የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የመንግስት የሥራ ቋንቋ ሆነው እንዲያገለግሉ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርቦ መጽደቁ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ የነበረው የኢትዮጵያ የቋንቋ ፖሊሲ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ሥራ ላይ ውሏል ነው የተባለው፡፡
በውይይቱ በሀገራችን ተጨማሪ 5 ቋንቋዎች የመንግስት የሥራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ መወሰኑን ተከትሎ የቋንቋ ፖሊሲውን ወደ አፋን ኦሮሞ መተርጎም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱ ተመላክቷል፡፡
የፖሊሲ ትርጉም ሥራውን ለማስጀመር የጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ከኦሮሚያ ባሕልና ቱሪዝም ጋር በመተባበር የቋንቋ ምሁራንን ያሳተፈ ውይይት በኦሮሞ ባሕል ማዕከል አድርገዋል፡፡
የቋንቋ ፖሊሲውን በጥንቃቄ ወደ አፋን ኦሮሞ ቋንቋ ለመተርጎም የቋንቋ ምሁራን ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንዳለው የኦሮሚያ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ቡጤ ገልጸዋል፡፡
የቋንቋ ምሁራኑ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ እንደሆኑ መጠቆሙን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ወደ አፋን ኦሮሞ እየተተረጎመ ባለው የቋንቋ ፖሊሲ ላይ ሰኞ ዕለት በኦሮሞ ባሕል ማዕከል ውይይት መካሄዱ ተገለጸ፡፡
ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ 5 የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የመንግስት የሥራ ቋንቋ ሆነው እንዲያገለግሉ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርቦ መጽደቁ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ የነበረው የኢትዮጵያ የቋንቋ ፖሊሲ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ሥራ ላይ ውሏል ነው የተባለው፡፡
በውይይቱ በሀገራችን ተጨማሪ 5 ቋንቋዎች የመንግስት የሥራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ መወሰኑን ተከትሎ የቋንቋ ፖሊሲውን ወደ አፋን ኦሮሞ መተርጎም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱ ተመላክቷል፡፡
የፖሊሲ ትርጉም ሥራውን ለማስጀመር የጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ከኦሮሚያ ባሕልና ቱሪዝም ጋር በመተባበር የቋንቋ ምሁራንን ያሳተፈ ውይይት በኦሮሞ ባሕል ማዕከል አድርገዋል፡፡
የቋንቋ ፖሊሲውን በጥንቃቄ ወደ አፋን ኦሮሞ ቋንቋ ለመተርጎም የቋንቋ ምሁራን ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንዳለው የኦሮሚያ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ቡጤ ገልጸዋል፡፡
የቋንቋ ምሁራኑ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ እንደሆኑ መጠቆሙን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia