#እንድታውቁት #አዲስአበባ
ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
የ1445ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል።
የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅም ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የሶላት ስነስርዓቱ የሚካሄደው በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ነው።
ይህ ተከትሎ ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የሶላት ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት ፦
- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ
- ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ
- ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ
- ከብሔራዊ ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ
- ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
- ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ
- ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ
- ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
- ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን መገንጠያ ላይ
- ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
- ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
የ1445ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል።
የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅም ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የሶላት ስነስርዓቱ የሚካሄደው በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ነው።
ይህ ተከትሎ ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የሶላት ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት ፦
- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ
- ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ
- ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ
- ከብሔራዊ ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ
- ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
- ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ
- ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ
- ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
- ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን መገንጠያ ላይ
- ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
- ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ
- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
❤1.02K😡163🕊69🙏60👏56😭33🥰29😢29😱28🤔21
" የሞባይል ስልክ እና ላፕቶፕ ጠፍቶብኛል የሚል ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ ይችላል " - ፖሊስ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣን ሞባይል ስልክን ከሌባ ላይ የገዛችን ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ንብረቱን ማስመለሱን አስታወቀ፡፡
ግለሰቧ ከወንጀለኞች በተለያየ ጊዜ የገዛቻቸው ልዩ ልዩ ሞባይል ስልኮችን ፣ ላፕቶፖችንና ታብሌት ይዞ ምርመራው መቀጠሉን አዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው ...
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው " አለምነሽ ፕላዛ " አካባቢ አንድ ግለሰብ ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣ አይነቱ አይፎን ፕሮ ማክስ ሞባይል ስልክ ይቀማሉ።
ይህን ተከትሎ አደይ አበባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታሉ።
የግለሰቡን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ፖሊስ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሌሎች መንግስታዊ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል የተሰረቀው ስልክ አራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ከሚገኝ አንድ የሞባይል መሸጫ ሱቅ መኖሩ ይረጋገጣል፡፡
ፖሊስ የህግ አግባብን በመከተል ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትእዛዝ በማውጣት ባደረገው ብርበራ ከግለሰቡ ላይ የተቀማውን ስልክ ጨምሮ በልዩ ልዩ ጊዜያት ከተለያዩ ቦታዎች የተሰረቁ ፦
➡️ 85 ስማርት ሞባይል ስልኮችን ፣
➡️ 4 ለፕቶፖችን ፣
➡️ 1 ታብሌትና የላፕቶፕ ቦርሳዎችን በኤግዚቢትነት ይዟል።
የቅሚያ ወንጀል የፈፀመውን ተጠርጣሪ ለመያዝ ክትትሉ መቀጠሉን ፖሊስ አመልክቷል።
የሞባይል ስልክ እና ላፕቶፕ ጠፍቶብኛል የሚል ማንኛውም ግለሰብ አደይ አበባ ስቴዲዮም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ሞባይል ስልኩን በመለየትና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ እንደሚችል አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabapolice
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣን ሞባይል ስልክን ከሌባ ላይ የገዛችን ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ንብረቱን ማስመለሱን አስታወቀ፡፡
ግለሰቧ ከወንጀለኞች በተለያየ ጊዜ የገዛቻቸው ልዩ ልዩ ሞባይል ስልኮችን ፣ ላፕቶፖችንና ታብሌት ይዞ ምርመራው መቀጠሉን አዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው ...
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው " አለምነሽ ፕላዛ " አካባቢ አንድ ግለሰብ ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣ አይነቱ አይፎን ፕሮ ማክስ ሞባይል ስልክ ይቀማሉ።
ይህን ተከትሎ አደይ አበባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታሉ።
የግለሰቡን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ፖሊስ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሌሎች መንግስታዊ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል የተሰረቀው ስልክ አራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ከሚገኝ አንድ የሞባይል መሸጫ ሱቅ መኖሩ ይረጋገጣል፡፡
ፖሊስ የህግ አግባብን በመከተል ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትእዛዝ በማውጣት ባደረገው ብርበራ ከግለሰቡ ላይ የተቀማውን ስልክ ጨምሮ በልዩ ልዩ ጊዜያት ከተለያዩ ቦታዎች የተሰረቁ ፦
➡️ 85 ስማርት ሞባይል ስልኮችን ፣
➡️ 4 ለፕቶፖችን ፣
➡️ 1 ታብሌትና የላፕቶፕ ቦርሳዎችን በኤግዚቢትነት ይዟል።
የቅሚያ ወንጀል የፈፀመውን ተጠርጣሪ ለመያዝ ክትትሉ መቀጠሉን ፖሊስ አመልክቷል።
የሞባይል ስልክ እና ላፕቶፕ ጠፍቶብኛል የሚል ማንኛውም ግለሰብ አደይ አበባ ስቴዲዮም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ሞባይል ስልኩን በመለየትና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ እንደሚችል አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabapolice
@tikvahethiopia
❤601👏366🙏63🤔33😢27🕊16😭14😡14😱11🥰7
" ' ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል ' የሚል ግለሰብ ማስረጃ በማቅረብ ስልኩን መውሰድ ይችላል " - ፖሊስ
በአዲስ አበባ በሞተር ሳይክል እየተንቀሳቀሱ ከግለሰቦች ሞባይል በመንጠቅ ሱቅ ውስጥ ሲያከመቹ የነበሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
አቶ ሱራፌል ቢያብል የተባሉ የግል ተበዳይ በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 ዋና ስራ አስፈፀሚ ሲሆኑ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረጉ ነበር።
በወቅት 2 ተጠርጣሪዎች በጥቁር ሞተር ሳይክል ኮድ 2 A19216 ደ.ሕ (ደቡብ ህዝብ) በሆነ 1ኛ ተጠርጣሪ እያሽከረከረ ፣ 2ኛ ተጠርጣሪ ሞተር ሳይክል ላይ ከኋላ በመሆን ከግለሰቡ ሞባይል ስልክ ነጥቀው በፍጥነት እያሽከረከሩ ከአካባቢው ይሰወራሉ።
የግል ተበዳይ ወንጀሉ እንደተፈፀመባቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለገርጂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ያመለክታሉ።
ፖሊስም የግል ተበዳዩን አቤቱታ በመቀበል ባደረገው ክትትል ከሁለቱ ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ ከሌቦቹ የሚረከቡ 2 ተጠርጣሪዎች በድምሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።
ህግን ተከትሎ ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹ ተከራይተው የሞባይል ጥገና የሚሰሩበት ሱቅ ውስጥ በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ግለሰቦች ተቀምተው የተከማቹ 32 ስማርት ሞባይል ስልኮችን በኤግዚቢት ተይዘዋል።
" ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል " የሚል ማንኛውም ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያያ በአካል በመቅረብና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መውሰድ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በሞተር ሳይክል እየተንቀሳቀሱ ከግለሰቦች ሞባይል በመንጠቅ ሱቅ ውስጥ ሲያከመቹ የነበሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
አቶ ሱራፌል ቢያብል የተባሉ የግል ተበዳይ በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 ዋና ስራ አስፈፀሚ ሲሆኑ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረጉ ነበር።
በወቅት 2 ተጠርጣሪዎች በጥቁር ሞተር ሳይክል ኮድ 2 A19216 ደ.ሕ (ደቡብ ህዝብ) በሆነ 1ኛ ተጠርጣሪ እያሽከረከረ ፣ 2ኛ ተጠርጣሪ ሞተር ሳይክል ላይ ከኋላ በመሆን ከግለሰቡ ሞባይል ስልክ ነጥቀው በፍጥነት እያሽከረከሩ ከአካባቢው ይሰወራሉ።
የግል ተበዳይ ወንጀሉ እንደተፈፀመባቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለገርጂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ያመለክታሉ።
ፖሊስም የግል ተበዳዩን አቤቱታ በመቀበል ባደረገው ክትትል ከሁለቱ ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ ከሌቦቹ የሚረከቡ 2 ተጠርጣሪዎች በድምሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።
ህግን ተከትሎ ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹ ተከራይተው የሞባይል ጥገና የሚሰሩበት ሱቅ ውስጥ በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ግለሰቦች ተቀምተው የተከማቹ 32 ስማርት ሞባይል ስልኮችን በኤግዚቢት ተይዘዋል።
" ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል " የሚል ማንኛውም ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያያ በአካል በመቅረብና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መውሰድ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏890❤164🙏51😡40😱31🕊26😭17😢15🤔13🥰6
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።
ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።
በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።
" በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።
ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።
በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።
" በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏550❤122😡60🤔47🙏26😭25😱24😢18🥰15🕊14
#እንድታውቁት #አዲስአበባ
ነገ ለስራ ይሁን ዘመድ ጥየቃ ወይም ደግሞ ለተለያየ ፕሮግራም ከቤት የምትወጡ ካላችሁ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።
መንገዶች የሚዘጉት 80ኛውን የመቻል ስፖርት ቡድን ምስረታን ምክንያት በማድረግ በሚካሄድ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው።
ሩጫው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።
በዚህም ፦
- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ አንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ነገ ለስራ ይሁን ዘመድ ጥየቃ ወይም ደግሞ ለተለያየ ፕሮግራም ከቤት የምትወጡ ካላችሁ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።
መንገዶች የሚዘጉት 80ኛውን የመቻል ስፖርት ቡድን ምስረታን ምክንያት በማድረግ በሚካሄድ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው።
ሩጫው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።
በዚህም ፦
- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ አንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
😡759❤158🙏156😭37👏34😢19🕊18🤔17😱17🥰13
#AddisAbaba
አዲስ አበባ ፖሊስ ከሰኔ 5 እስከ ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ለ15 ቀናት በሁሉም ክ/ከተሞች ኦፕሬሽን ማካሄዱን አሳውቋል።
በርካታ የወንጀል ተጠርጣሪዎችንና ኤግዚቢቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለም ገልጿል።
በተደረገው ኦፕሬሽን ፦
➡️ ከዚህ ቀደም የተሰረቁ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ማስመለሱን ፤
➡️ ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ሀሰተኛ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በተለጣፊ እስቲከር ሲያዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ሀሰተኛ ሰሌዳ ለማዘጋጀት ከሚጠቀሙበት ኮምፒውተር ፣ ላፕቶፕ ፣ ፍላሽ እና ካሜራ ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋለ፤
➡️ የመኪና መያቸውን
➡️ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀል የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ከ700 በላይ ሞባይል ስልኮች ማስመለሱን፤
➡️ የተሰረቀ እቃ ከሚገዙ ህገወጦች ላይ 108 ላፕቶፕ ߹6 ኮምፒዩተር ߹11 ካሜራዎች ߹ 2 ቴሌቪዥንና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ከሸሸጉበት ቦታ መያዙን
➡️ 2 ክላሽ ከመሰል 120 ጥይቶች ጋር፣ 67 ልዩ ልዩ ሽጉጦች ከ568 መሰል ጥይት ጋር እንዲሁም 2 ኋላ ቀር መሳሪያ ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በኦፕሬሽኑ መያዙን አመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪ ኮንትሮባንድ ፣ ሀሰተኛና ሰነዶችን እና መድኃኒቶች በኦፕሬሽኑ መገኘታቸውን ገልጿል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንደሚኒዬም ውስጥ መድሃኒት የማከፋፈልም ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የሌላቸውና በህገ-ወጥ መንገድ መድሃኒት እያዘጋጁ ሲያከፋፍሉ የተገኙ ግለሰቦች ተዘዋል፡፡
ግለሰቦቹ ያዘጋጇቸውና ለገበያ ሊያቀርቧቸው የነበሩ ፦
° 169 ብልቃጥ መድሃኒቶች ፣
° 40 ግሉኮስ ፣
° በርካታ የመድሃኒት ብልቃጦች እና ህገ-ወጥ ስራቸውን ለመስራት የሚገለገሉበት አንድ ማሽንን ጨምሮ ፕሪንተር እና ላፕቶፕ በኤግዚቢትነት መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
አዲስ አበባ ፖሊስ ከሰኔ 5 እስከ ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ለ15 ቀናት በሁሉም ክ/ከተሞች ኦፕሬሽን ማካሄዱን አሳውቋል።
በርካታ የወንጀል ተጠርጣሪዎችንና ኤግዚቢቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለም ገልጿል።
በተደረገው ኦፕሬሽን ፦
➡️ ከዚህ ቀደም የተሰረቁ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ማስመለሱን ፤
➡️ ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ሀሰተኛ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በተለጣፊ እስቲከር ሲያዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ሀሰተኛ ሰሌዳ ለማዘጋጀት ከሚጠቀሙበት ኮምፒውተር ፣ ላፕቶፕ ፣ ፍላሽ እና ካሜራ ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋለ፤
➡️ የመኪና መያቸውን
➡️ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀል የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ከ700 በላይ ሞባይል ስልኮች ማስመለሱን፤
➡️ የተሰረቀ እቃ ከሚገዙ ህገወጦች ላይ 108 ላፕቶፕ ߹6 ኮምፒዩተር ߹11 ካሜራዎች ߹ 2 ቴሌቪዥንና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ከሸሸጉበት ቦታ መያዙን
➡️ 2 ክላሽ ከመሰል 120 ጥይቶች ጋር፣ 67 ልዩ ልዩ ሽጉጦች ከ568 መሰል ጥይት ጋር እንዲሁም 2 ኋላ ቀር መሳሪያ ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በኦፕሬሽኑ መያዙን አመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪ ኮንትሮባንድ ፣ ሀሰተኛና ሰነዶችን እና መድኃኒቶች በኦፕሬሽኑ መገኘታቸውን ገልጿል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንደሚኒዬም ውስጥ መድሃኒት የማከፋፈልም ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የሌላቸውና በህገ-ወጥ መንገድ መድሃኒት እያዘጋጁ ሲያከፋፍሉ የተገኙ ግለሰቦች ተዘዋል፡፡
ግለሰቦቹ ያዘጋጇቸውና ለገበያ ሊያቀርቧቸው የነበሩ ፦
° 169 ብልቃጥ መድሃኒቶች ፣
° 40 ግሉኮስ ፣
° በርካታ የመድሃኒት ብልቃጦች እና ህገ-ወጥ ስራቸውን ለመስራት የሚገለገሉበት አንድ ማሽንን ጨምሮ ፕሪንተር እና ላፕቶፕ በኤግዚቢትነት መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
🙏377❤98👏80😢14🕊13😡13😱11😭10🥰5🤔5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህፃን ሶሊያን ዳንኤል ተገኝታለች። • " 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር መቻሏል ተጠርጣሪዋ ገልጻለች " - የአዲስ አበባ ፖሊስ ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባደረገው ጠንካራ ክትትል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።…
#AddisAbaba
የሁለት ዓመቷን ሶሊያና ዳንኤል የተባለችውን ህፃን በመጥለፍና በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥታለች።
የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባት ቤዛዊት በቀለ የተባለችው ግለሰብ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራበት ከነበረበት ቤት (ሳሪስ አዲስ ሰፈር) መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ህጻን ሶሊያናን ይዛ በመሰወር ሱሉልታ ከተማ " ኖኖ መና አቢቹ " ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃኗን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ይታወሳል።
ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ የአ/አ ፖሊስ ምርመራ የማስፋት ስራ በመስራት ከዚህ ቀደም በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችባቸው አምስት የተለያዩ ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን መስረቋን አረጋግጧል።
ከሰረቀቻቸው ንብረቶች መካከልም 2 ላፕቶፕ ፣ 1 ሞባይል ስልክ እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎች ፖሊስ ባደረገው ጥረት ከሸጠችበት በምሪት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡
በግለሰቧ ላይ ምርመራ ተጣርቶ በከባድ ስርቆት እና ህፃን ልጅ መጥለፍ በሚል ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ቤዛዊት በቀለ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የሁለት ዓመቷን ሶሊያና ዳንኤል የተባለችውን ህፃን በመጥለፍና በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥታለች።
የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባት ቤዛዊት በቀለ የተባለችው ግለሰብ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራበት ከነበረበት ቤት (ሳሪስ አዲስ ሰፈር) መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ህጻን ሶሊያናን ይዛ በመሰወር ሱሉልታ ከተማ " ኖኖ መና አቢቹ " ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃኗን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ይታወሳል።
ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ የአ/አ ፖሊስ ምርመራ የማስፋት ስራ በመስራት ከዚህ ቀደም በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችባቸው አምስት የተለያዩ ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን መስረቋን አረጋግጧል።
ከሰረቀቻቸው ንብረቶች መካከልም 2 ላፕቶፕ ፣ 1 ሞባይል ስልክ እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎች ፖሊስ ባደረገው ጥረት ከሸጠችበት በምሪት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡
በግለሰቧ ላይ ምርመራ ተጣርቶ በከባድ ስርቆት እና ህፃን ልጅ መጥለፍ በሚል ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ቤዛዊት በቀለ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏714❤123🙏46😢37😭26🕊14😱12🤔9😡7🥰4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አካል ጉዳተኛ በመምሰል ስትለምን የነበረች ተጠርጣሪ ከእነ ግብረአበሯ መያዟን አስታወቀ።
ግለሰቦቹ በቀን እስከ 500 ብር ድረስ እንደሚያገኙ ታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዋ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖራት ነው አካል ጉደተኛ በመምሰል ወገቧን በጎማ በማሰር ዊልቸር ላይ በመሆን ስትለምን ትላንት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው " #መገናኛ " አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ የተያዘችው።
ግለሰቧን ከቦታ ወደ ቦታ ሲያንቀሳቅሳት የነበረው ተጠርጣሪም ተይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ ዊልቸሩን በቀን 35 ብር ተከራይተው ለ8 ወር እንደተጠቀሙና በቀን እስከ 500 መቶ ብር እንደሚያገኙ ከሰጡት ቃል ማወቅ እንደተቻለ ፖሊስ አስረድቷል።
ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖርባቸው ጉዳተኛ በመስምሰል የሚያታልሉ እንዳሉ ህብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ሲል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አካል ጉዳተኛ በመምሰል ስትለምን የነበረች ተጠርጣሪ ከእነ ግብረአበሯ መያዟን አስታወቀ።
ግለሰቦቹ በቀን እስከ 500 ብር ድረስ እንደሚያገኙ ታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዋ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖራት ነው አካል ጉደተኛ በመምሰል ወገቧን በጎማ በማሰር ዊልቸር ላይ በመሆን ስትለምን ትላንት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው " #መገናኛ " አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ የተያዘችው።
ግለሰቧን ከቦታ ወደ ቦታ ሲያንቀሳቅሳት የነበረው ተጠርጣሪም ተይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ ዊልቸሩን በቀን 35 ብር ተከራይተው ለ8 ወር እንደተጠቀሙና በቀን እስከ 500 መቶ ብር እንደሚያገኙ ከሰጡት ቃል ማወቅ እንደተቻለ ፖሊስ አስረድቷል።
ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖርባቸው ጉዳተኛ በመስምሰል የሚያታልሉ እንዳሉ ህብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ሲል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏512😡172❤88🤔87😢69😱68🕊17🙏10🥰8😭6
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ፖሊስ " የከንቲባዋ ታናሽ ወንድም እና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ነኝ " በማለት ከ4 ግለሰቦች ላይ ከ970 ሺ ብር ያታለለን ተጠርጣሪ መያዙን አሳወቀ።
እንደ ፖሊስ መረጃ ተጠርጣሪው ግለሰብ ታደለ ጌታነህ ይባላል፡፡
በስሙ ግን " ታደለ አቤቤ " እንደሚባል ሐሰተኛ መታወቂያ አዘጋጅቷል።
ይኸው ግለሰብ የግል ተበዳይ አቶ ልዑል ኪሮስን የከንቲባዋ ወንድም እንደሆነ እና መንግስት ለቤት መስሪያ 140 ካሬ ሜትር ቦታ ስለሰጠው ለሊዝ የሚክፍለው 800 ሺ ብር እንዲያበድሩት ይጠይቃል።
የግል ተበዳይም የተባሉትን በማመን 600 ሺ ብሩን አስናቀ ጌታነህ ቀሪውን 200 ሺ ብር ደግሞ በላይ ጣሰው በተባሉት ግብራበሮቹ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ በነገራቸው መሰረት ብሩን ገቢ ያደርጋሉ፡፡
በተመሳሳይ የማታለያ ዘዴ አቶ ፈለቀ ሃይሉ የተባሉ ግለሰብን በመቅረብ ቤት ለመገንባት 4 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገውና 500ሺ ብር ብድር እንዲሰጡት ጠይቆ 105 ሺ ብር መቀበሉን በማስረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
በተመሳሳይ አዳማ ላይ የተዋወቀቃቸውን አቶ ለገሰ ሲሳይ የተባሉ ግለሰብን ደግሞ " የከንቲባዋ ወንድም ስለሆነኩ በቀላሉ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ መሬት አሰጥሃለሁኝ " ብሎ 10 ሺ ብር ወስዷል።
እንዲሁም ለቤተሰባቸው ' #ፓስፖርት ' ለማውጣት ኢሚግሬሽን ላይ ያገኛቸውን አቶ ፈለቀ ዝናቡ የተባሉ ግለሰብን " የከንቲባዋ ወንድም ነኝ በተጨማሪም እኔም ዳኛ ነኝ ምናልባት ያለ አግባብ የሚያጉላሉህ ካሉ አሳውቀኝ ሰብስቤ አሳስራቸዋለሁኝ " የሚል የማታለያ ቃል በመናገር ጉዳያቸው በፍጥነት እንዲያልቅል 80 ሺህ ብር እንዲሰጠው ጠይቆ 10 ሺህ ብር አታሎ ወስዷል።
ፖሊስ ግለሰቡ ከከንቲባ አዳነች ጋር ምንም አይነት ዝምድና የሌለውና በድለላ ስራ የተሰማራ መሆኑን ገልጿል።
ግለሰቡን ጨምሮ በዚህ ወንጀል ተሳትፎ ያላቸው ሦስት ተጠርጣዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን አዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ " የከንቲባዋ ታናሽ ወንድም እና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ነኝ " በማለት ከ4 ግለሰቦች ላይ ከ970 ሺ ብር ያታለለን ተጠርጣሪ መያዙን አሳወቀ።
እንደ ፖሊስ መረጃ ተጠርጣሪው ግለሰብ ታደለ ጌታነህ ይባላል፡፡
በስሙ ግን " ታደለ አቤቤ " እንደሚባል ሐሰተኛ መታወቂያ አዘጋጅቷል።
ይኸው ግለሰብ የግል ተበዳይ አቶ ልዑል ኪሮስን የከንቲባዋ ወንድም እንደሆነ እና መንግስት ለቤት መስሪያ 140 ካሬ ሜትር ቦታ ስለሰጠው ለሊዝ የሚክፍለው 800 ሺ ብር እንዲያበድሩት ይጠይቃል።
የግል ተበዳይም የተባሉትን በማመን 600 ሺ ብሩን አስናቀ ጌታነህ ቀሪውን 200 ሺ ብር ደግሞ በላይ ጣሰው በተባሉት ግብራበሮቹ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ በነገራቸው መሰረት ብሩን ገቢ ያደርጋሉ፡፡
በተመሳሳይ የማታለያ ዘዴ አቶ ፈለቀ ሃይሉ የተባሉ ግለሰብን በመቅረብ ቤት ለመገንባት 4 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገውና 500ሺ ብር ብድር እንዲሰጡት ጠይቆ 105 ሺ ብር መቀበሉን በማስረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
በተመሳሳይ አዳማ ላይ የተዋወቀቃቸውን አቶ ለገሰ ሲሳይ የተባሉ ግለሰብን ደግሞ " የከንቲባዋ ወንድም ስለሆነኩ በቀላሉ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ መሬት አሰጥሃለሁኝ " ብሎ 10 ሺ ብር ወስዷል።
እንዲሁም ለቤተሰባቸው ' #ፓስፖርት ' ለማውጣት ኢሚግሬሽን ላይ ያገኛቸውን አቶ ፈለቀ ዝናቡ የተባሉ ግለሰብን " የከንቲባዋ ወንድም ነኝ በተጨማሪም እኔም ዳኛ ነኝ ምናልባት ያለ አግባብ የሚያጉላሉህ ካሉ አሳውቀኝ ሰብስቤ አሳስራቸዋለሁኝ " የሚል የማታለያ ቃል በመናገር ጉዳያቸው በፍጥነት እንዲያልቅል 80 ሺህ ብር እንዲሰጠው ጠይቆ 10 ሺህ ብር አታሎ ወስዷል።
ፖሊስ ግለሰቡ ከከንቲባ አዳነች ጋር ምንም አይነት ዝምድና የሌለውና በድለላ ስራ የተሰማራ መሆኑን ገልጿል።
ግለሰቡን ጨምሮ በዚህ ወንጀል ተሳትፎ ያላቸው ሦስት ተጠርጣዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን አዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏1.41K🤔223❤211🥰70😭63😱53😡45🙏44😢29🕊22
TIKVAH-ETHIOPIA
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ 1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን…
#AddisAbaba
“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡
አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦
° ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?
° ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?
° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡
ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡
አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡
ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡
በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡
ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡
ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡
ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡
መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡
ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡
ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡
በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡
ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡
ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡
አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡
አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡
ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡
በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡
ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡
ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል። "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡
አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦
° ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?
° ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?
° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡
ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡
አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡
ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡
በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡
ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡
ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡
ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡
መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡
ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡
ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡
በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡
ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡
ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡
አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡
አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡
ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡
በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡
ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡
ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል። "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏344❤165😡71🕊44🙏39😱20🤔19😭18🥰15😢15
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
ከኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል።
የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 25/ 2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከበራል ፤ ይህን ተከትሎ የሚከተሉት መንገዶች ይዘጋሉ።
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ፤
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፤
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ፤
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)፤
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ፤
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፤
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ፤
- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ፤
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፤
- ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ፤
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ፤
ከመስከረም 24/ 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
ከኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል።
የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 25/ 2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከበራል ፤ ይህን ተከትሎ የሚከተሉት መንገዶች ይዘጋሉ።
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ፤
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፤
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ፤
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)፤
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ፤
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፤
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ፤
- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ፤
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፤
- ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ፤
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ፤
ከመስከረም 24/ 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
😡2.73K❤697🙏142👏127😭88🕊70🤔52🥰49😢39😱29
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ አሽከርክሩ " - ፖሊስ
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ የደረሱት የትራፊክ አደጋዎች የሰው ህይወት ቀጥፈዋል ፣ ከባድ እና ቀላል ጉዳት አድርሰዋል፣ ንብረትም ላይ ጉዳት ደርሷል።
በአንድ ክ/ከተማ፣ በአንድ ቀን፣ በተለያየ ቦታና ሰዓት በደረሰ የመንገድ ትራፊክ አደጋ አጠቃላይ የ7 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ9 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
አደጋዎቹ የደረሱት ቦሌ ክ/ከተማ ውስጥ መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ/ም ነው።
የጉዞ መስመሩን ከጎሮ ወደ ኮዬ ፈቼ ያደረገ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-69867 ኢት #ሲኖ_ትራክ ተሽከርካሪ ከከተማ አውቶቡስ ጋር ተጋጭቶ ትኬት ሊቆርጡ ወደ አውቶቡሱ ተጠግተው የነበሩ 3 ሴቶች እንዲሁም በአካባቢው ላይ ጧፍ ስትሸጥ በነበረች ሴት ላይ የሞት አደጋ ያስከተለ ሲሆን የከባድ መኪናው አሽከርካሪም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶበታል፡፡
ከተከሰተው ሞት በተጨማሪ በ7 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
በዛው እለት ቡልቡላ መስቀለኛ ተብሎ በሚጠራው አካባቢም አካባቢ በደረሰው አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
የጉዞ አቅጣጫውን ከመድኃኒያለም ወደ ማርያም ያደረገ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-8660 ኢት #ሲኖ_ትራክ ተሽከርካሪ ከማርያም ወደ ኮዬ ይሄድ ከነበረ ኮድ 3-46737 ኦሮ ዶልፊን ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭተው የደረሰ አደጋ ነው።
በአንድ ቀን በ7 ሰዎች ላይ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ መድረሱ በእጅጉ አስዛኝ እንደሆነ የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ በአብዛኛው ለሚከሰቱት የትራፊክ አደጋዎች ዋነኛ ምክንያት ተገቢውን ጥንቃቄ ባለማድረግ የሚደርሱ መሆናቸውን አስገንዝቧል።
አሽከርካሪዎች ከምንጊዜውም በላይ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ የአካባቢውን߹ የመንገዱን እና የእግረኛውን የመንገድ አጠቃቀም ሁኔታ በተገቢው በማስተዋል ማሽከርከር እንደሚጠበቅባቸው ፖሊስ አሳስቧል።
ከተፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር በኋላ ከሚመጣው መፀፀት እንደማያድን በመገንዘብ በጥንቃቄና በእርጋታ ማሽከርከር እንደሚገባ ፖሊስ ገልጿል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ የደረሱት የትራፊክ አደጋዎች የሰው ህይወት ቀጥፈዋል ፣ ከባድ እና ቀላል ጉዳት አድርሰዋል፣ ንብረትም ላይ ጉዳት ደርሷል።
በአንድ ክ/ከተማ፣ በአንድ ቀን፣ በተለያየ ቦታና ሰዓት በደረሰ የመንገድ ትራፊክ አደጋ አጠቃላይ የ7 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ9 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
አደጋዎቹ የደረሱት ቦሌ ክ/ከተማ ውስጥ መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ/ም ነው።
የጉዞ መስመሩን ከጎሮ ወደ ኮዬ ፈቼ ያደረገ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-69867 ኢት #ሲኖ_ትራክ ተሽከርካሪ ከከተማ አውቶቡስ ጋር ተጋጭቶ ትኬት ሊቆርጡ ወደ አውቶቡሱ ተጠግተው የነበሩ 3 ሴቶች እንዲሁም በአካባቢው ላይ ጧፍ ስትሸጥ በነበረች ሴት ላይ የሞት አደጋ ያስከተለ ሲሆን የከባድ መኪናው አሽከርካሪም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶበታል፡፡
ከተከሰተው ሞት በተጨማሪ በ7 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
በዛው እለት ቡልቡላ መስቀለኛ ተብሎ በሚጠራው አካባቢም አካባቢ በደረሰው አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
የጉዞ አቅጣጫውን ከመድኃኒያለም ወደ ማርያም ያደረገ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-8660 ኢት #ሲኖ_ትራክ ተሽከርካሪ ከማርያም ወደ ኮዬ ይሄድ ከነበረ ኮድ 3-46737 ኦሮ ዶልፊን ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭተው የደረሰ አደጋ ነው።
በአንድ ቀን በ7 ሰዎች ላይ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ መድረሱ በእጅጉ አስዛኝ እንደሆነ የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ በአብዛኛው ለሚከሰቱት የትራፊክ አደጋዎች ዋነኛ ምክንያት ተገቢውን ጥንቃቄ ባለማድረግ የሚደርሱ መሆናቸውን አስገንዝቧል።
አሽከርካሪዎች ከምንጊዜውም በላይ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ የአካባቢውን߹ የመንገዱን እና የእግረኛውን የመንገድ አጠቃቀም ሁኔታ በተገቢው በማስተዋል ማሽከርከር እንደሚጠበቅባቸው ፖሊስ አሳስቧል።
ከተፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር በኋላ ከሚመጣው መፀፀት እንደማያድን በመገንዘብ በጥንቃቄና በእርጋታ ማሽከርከር እንደሚገባ ፖሊስ ገልጿል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
😭374❤90😢40🕊31🙏13👏7😱7🥰6🤔6
" የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል ! "
የ17 አመት ታዳጊ በሆነችው አዶናይት ይሄይስ ላይ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ክልል ልዩ ቦታው 15 ሜዳ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።
የወንጀሉ ሰለባ የሆነችው የ17 አመት እድሜ ያላት አዶናይት ይሄይስ የተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የፍቅረኛው ልጅ ነበረች።
መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰአት ሲሆን ታዳጊ አዶናይት ይሄይስ መኖሪያ ቤቷ እያለች ተከሳሽ " ለምን አስገድዶ ደፈረኝ ብለሽ ለፖሊስ ክስ መሰረትሽ " በሚል ሰበብ በቢላዋ የተለያየ የሰውነት ክፍሏን 16 ቦታ በመውጋት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ መኖሪያ ቤቱ በመሄድ ልብሱን በመቀየር ሊሰወር ሲሞክር በአካባቢው ማህበረሰብ እና በወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሊያዝ ችሏል።
ፖሊስም በተያዘው ተከሳሽ ላይ ባደረገው ምርመራ ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ባልታወቀ ጊዜና ሰዓት ታዳጊዋን " ነይ ሱቅ ልላክሽ " እና ሌሎች ማታለያዎችን እየተጠቀመ በመኖሪያ ቤቱ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት የቆየ መሆኑንና በወቅቱ እድሜዋ በግምት 10 አመቷ እንደነበረ የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡
ግለሰቡ የእናቷ የፍቅር ጓደኛ የነበረ ሲሆን ይህንን አፀያፊ ድርጊት ለአንድ ሰው ብትናገሪ እናት እና አባትሽን እገላለሁ እያለ ሲያስፈራት የቆየ ስለመሆኑ የሚዘረዝረው የምርመራ መዝገቡ በተጨማሪም ሟችን " በሞባይል ካሜራ ቪዲዮ ቀርጬሻለሁ በሚዲያ እና በቴሌግራም እለቀዋለሁ " እያለ ለአመታት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱንና በዚህም ታዳጊዋ ከተከሳሽ በመፀነሷ ፅንሱን እንድታስወርድ ማድረጉን የተከሳሽ የምርመራ መዝገብ ያስረዳል።
ፖሊስ ባከናወነው ተጨማሪ የምርመራ ስራ ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን አምኖ ቦታው ድረስ በመሄድ መርቶ ያሳየ ሲሆን የምርመራ መዝገቡን በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለዓቃቤ ህግ በመላክ ክስ ተመስርቶበታል።
የወንጀል መዝገቡን ሲከታተል የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ #የሞት_ቅጣት እንዲቀጣ እና የዘወትር ህዝባዊ መብቶቹ እንዲሻሩ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የ17 አመት ታዳጊ በሆነችው አዶናይት ይሄይስ ላይ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ክልል ልዩ ቦታው 15 ሜዳ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።
የወንጀሉ ሰለባ የሆነችው የ17 አመት እድሜ ያላት አዶናይት ይሄይስ የተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የፍቅረኛው ልጅ ነበረች።
መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰአት ሲሆን ታዳጊ አዶናይት ይሄይስ መኖሪያ ቤቷ እያለች ተከሳሽ " ለምን አስገድዶ ደፈረኝ ብለሽ ለፖሊስ ክስ መሰረትሽ " በሚል ሰበብ በቢላዋ የተለያየ የሰውነት ክፍሏን 16 ቦታ በመውጋት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ መኖሪያ ቤቱ በመሄድ ልብሱን በመቀየር ሊሰወር ሲሞክር በአካባቢው ማህበረሰብ እና በወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሊያዝ ችሏል።
ፖሊስም በተያዘው ተከሳሽ ላይ ባደረገው ምርመራ ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ባልታወቀ ጊዜና ሰዓት ታዳጊዋን " ነይ ሱቅ ልላክሽ " እና ሌሎች ማታለያዎችን እየተጠቀመ በመኖሪያ ቤቱ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት የቆየ መሆኑንና በወቅቱ እድሜዋ በግምት 10 አመቷ እንደነበረ የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡
ግለሰቡ የእናቷ የፍቅር ጓደኛ የነበረ ሲሆን ይህንን አፀያፊ ድርጊት ለአንድ ሰው ብትናገሪ እናት እና አባትሽን እገላለሁ እያለ ሲያስፈራት የቆየ ስለመሆኑ የሚዘረዝረው የምርመራ መዝገቡ በተጨማሪም ሟችን " በሞባይል ካሜራ ቪዲዮ ቀርጬሻለሁ በሚዲያ እና በቴሌግራም እለቀዋለሁ " እያለ ለአመታት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱንና በዚህም ታዳጊዋ ከተከሳሽ በመፀነሷ ፅንሱን እንድታስወርድ ማድረጉን የተከሳሽ የምርመራ መዝገብ ያስረዳል።
ፖሊስ ባከናወነው ተጨማሪ የምርመራ ስራ ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን አምኖ ቦታው ድረስ በመሄድ መርቶ ያሳየ ሲሆን የምርመራ መዝገቡን በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለዓቃቤ ህግ በመላክ ክስ ተመስርቶበታል።
የወንጀል መዝገቡን ሲከታተል የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ #የሞት_ቅጣት እንዲቀጣ እና የዘወትር ህዝባዊ መብቶቹ እንዲሻሩ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏4.21K😭678❤248🙏139😡62🕊42😢39🤔16🥰9😱9
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba 🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል !! " እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ። ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም። ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ…
#AddisAbaba
በተደመሰሰ፣ በታጠፈ እና በማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር ሲገለገሉ የተገኙ ከ1,000 በላይ አሽከርከሪዎችን ቀጥቻለሁ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለጸ።
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል አሽከርካሪዎች የተቀባ፣ የታጠፈ ፣ የተፋፋቀ፣ የተቆራረጠ እና በአጠቃላይ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን በመጠቀም ደምብ ሲተላለፉ ቆይተዋል ሲል ፖሊስ አስታውሷል፡፡
አንዳንዶቹ እንደውም ወንጀል ሲፈፅሙ ተገኝተው ምርመራ እየተጣራባቸው ነው ብሏል፡፡
ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገ ቁጥጥር 1,587 ተሽከርካሪዎች ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን ለጥፈው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡
የተፋፋቀ፣ የደበዘዘ፣ የታጠፈ እና የማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር መጠቀም፣ ከሰሌዳ መብራት ውጪ ሌሎች ዓይነቶችን አብረቅራቂ መብራቶችን መጠቀም፣ ሰሌዳውን በማይታይ ቦታ መለጠፍ እና ሆን ብለው ሰሌዳን አጥፎ መንቀሳቀስ በቁጥጥሩ ወቅት የተገኙ ጥፋቶች ናቸው ሲል ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በጥፋት ውስጥ ከተገኙት ውስጥ ኮድ-1 ወይም ታክሲ 216፣ ኮድ-2 ወይም የቤት መኪና 320፣ ኮድ-3 የሆኑ 1,037 እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች 14 መሆናቸውን በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ ጠቅሷል፡፡
ቁጥጥር ከተደረገባቸው መካከል አብዛኛዎቹ የፊት ወይም የኋላ ሰሌዳ ሳይኖራቸው የተገኙ ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ 633ቱ ደግሞ የተቆረጠ ወይም ለዕይታ ግልጽ ያልሆነ ሰሌዳ ሲጠቀሙ የተገኙና ሰሌዳውን በማይታይ ቦታ ያሰሩ፣ የተሸፈኑና የተለያየ ቀለም የተቀቡ ሰሌዳዎች መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡
#AddisAbabaPolice #ShegerFM
@tikvahethiopia
በተደመሰሰ፣ በታጠፈ እና በማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር ሲገለገሉ የተገኙ ከ1,000 በላይ አሽከርከሪዎችን ቀጥቻለሁ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለጸ።
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል አሽከርካሪዎች የተቀባ፣ የታጠፈ ፣ የተፋፋቀ፣ የተቆራረጠ እና በአጠቃላይ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን በመጠቀም ደምብ ሲተላለፉ ቆይተዋል ሲል ፖሊስ አስታውሷል፡፡
አንዳንዶቹ እንደውም ወንጀል ሲፈፅሙ ተገኝተው ምርመራ እየተጣራባቸው ነው ብሏል፡፡
ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገ ቁጥጥር 1,587 ተሽከርካሪዎች ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን ለጥፈው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡
የተፋፋቀ፣ የደበዘዘ፣ የታጠፈ እና የማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር መጠቀም፣ ከሰሌዳ መብራት ውጪ ሌሎች ዓይነቶችን አብረቅራቂ መብራቶችን መጠቀም፣ ሰሌዳውን በማይታይ ቦታ መለጠፍ እና ሆን ብለው ሰሌዳን አጥፎ መንቀሳቀስ በቁጥጥሩ ወቅት የተገኙ ጥፋቶች ናቸው ሲል ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በጥፋት ውስጥ ከተገኙት ውስጥ ኮድ-1 ወይም ታክሲ 216፣ ኮድ-2 ወይም የቤት መኪና 320፣ ኮድ-3 የሆኑ 1,037 እና ሌሎች ተሽከርካሪዎች 14 መሆናቸውን በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ ጠቅሷል፡፡
ቁጥጥር ከተደረገባቸው መካከል አብዛኛዎቹ የፊት ወይም የኋላ ሰሌዳ ሳይኖራቸው የተገኙ ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ 633ቱ ደግሞ የተቆረጠ ወይም ለዕይታ ግልጽ ያልሆነ ሰሌዳ ሲጠቀሙ የተገኙና ሰሌዳውን በማይታይ ቦታ ያሰሩ፣ የተሸፈኑና የተለያየ ቀለም የተቀቡ ሰሌዳዎች መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡
#AddisAbabaPolice #ShegerFM
@tikvahethiopia
❤459😡242👏105😁48😭28🙏26🕊18🥰16🤔15😢9😱3
" በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈፀም ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል " - ፖሊስ
ከኢትዮጵያውያን ባህል፣ ኃይማኖትና ወግ ተቃራኒ የሆነ በርካታ ድርጊቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያስረጨ ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ፖሊስ ግለሰቡ ሚሊዮን ድሪባ የሚባል እንደሆነና በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስል በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታቸውን ያነሱበት ጉዳይ እንደሆነ ገልጿል።
ከሚነሳው ቅሬታ ባሻገር የኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈፀም ወንጀል መሆኑን ይደነግጋል ብሏል።
ግለሰቡ በጎዳናዎች ላይ የተለያዩ አፀያፊ በተለይም የሴቶችን ክብር የሚነካ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች በመፈፀም የቀረፃቸውን ምስሎች በመልቀቅ በፈፀመው ህገ ወጥ ተግባርና በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ አንዳንድ ምስሎች ተገቢነታቸውን የሳቱና ያፈነገጡ እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ ገልፆ ህገ ወጥ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በሚለቁ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ከኢትዮጵያውያን ባህል፣ ኃይማኖትና ወግ ተቃራኒ የሆነ በርካታ ድርጊቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያስረጨ ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ፖሊስ ግለሰቡ ሚሊዮን ድሪባ የሚባል እንደሆነና በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስል በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታቸውን ያነሱበት ጉዳይ እንደሆነ ገልጿል።
ከሚነሳው ቅሬታ ባሻገር የኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈፀም ወንጀል መሆኑን ይደነግጋል ብሏል።
ግለሰቡ በጎዳናዎች ላይ የተለያዩ አፀያፊ በተለይም የሴቶችን ክብር የሚነካ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች በመፈፀም የቀረፃቸውን ምስሎች በመልቀቅ በፈፀመው ህገ ወጥ ተግባርና በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ አንዳንድ ምስሎች ተገቢነታቸውን የሳቱና ያፈነገጡ እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ ገልፆ ህገ ወጥ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በሚለቁ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
14👏6.45K🙏399❤385😡124😭54🤔45😱44🥰34💔29🕊25😢23
#እንድታውቁት
ነገ በአዲስ አበባ መንገዶች ይዘጋሉ።
ነገ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም በ " ኢትዮጵያ ታምርት " የ10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር ምክንያት መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ) ፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።
በዚህም መሠረት ፡-
➡️ ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ)
➡️ ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደቤይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
➡️ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
➡️ ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
➡️ ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት
➡️ ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት
➡️ ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
➡️ ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ
➡️ ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት
➡️ ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር
➡️ ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ
➡️ ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ
➡️ ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በተጠቀሱት መስመሮች ከዛሬ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ/ም ምሽት 12፡00 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድም ፈጽሞ መከልከሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ነገ በአዲስ አበባ መንገዶች ይዘጋሉ።
ነገ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም በ " ኢትዮጵያ ታምርት " የ10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር ምክንያት መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ) ፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።
በዚህም መሠረት ፡-
➡️ ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ)
➡️ ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደቤይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
➡️ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
➡️ ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
➡️ ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት
➡️ ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
➡️ ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት
➡️ ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
➡️ ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ
➡️ ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት
➡️ ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር
➡️ ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ
➡️ ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ
➡️ ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በተጠቀሱት መስመሮች ከዛሬ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ/ም ምሽት 12፡00 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድም ፈጽሞ መከልከሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
😡797❤217😭68🤔62👏33🙏28🕊19🥰16😱15💔10😢6
#AddisAbaba
ከለሊት 10:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ መንገዶች ይዘጋሉ።
116ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ በዓል ነገ እሁድ ሚያዚያ 26/2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ በተለያዩ ወታደራዊ ትርኢቶች ይከበራል።
በዚህም ምክንያት መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
➡️ ከ22 አደባባይ ወደ ወደ ቅዱስ ዑራኤል -መስቀል አደባባይ (22 አደባባይ በተመሣሣይ ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ ላይ)
➡️ ከአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ (አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ)
➡️ ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
➡️ ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት
➡️ ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ ጋዜቦ አደባባይ (መስቀል ፍላዎር አደባባይ ላይ)
➡️ ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኤግዚብሽን ውስጥ ለውስጥ ወደ ፊላሚንጎ (ጋዜቦ አደባባይ ላይ)
➡️ ከቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ወደ ለገሃር መብራት ( ቅዱስ ቂርቆስ ወደ ጋዜቦ ላይ)
➡️ ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ
➡️ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር መብራት (ሜክሲኮ አደባባይ ላይ)
➡️ ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ (ፓርላማ መብራት ላይ)
➡️ ከጥይት ቤት ወደ ቅዱስ ገብርኤል (ጥይት ቤት መታጠፊያ ላይ )
➡️ ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ ላይ) ከለሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪም፦
- ከቅዱስ ዑራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
- ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም
- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ጀምሮ ዝግ ተደርጓል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ከለሊት 10:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ መንገዶች ይዘጋሉ።
116ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ በዓል ነገ እሁድ ሚያዚያ 26/2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ በተለያዩ ወታደራዊ ትርኢቶች ይከበራል።
በዚህም ምክንያት መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
➡️ ከ22 አደባባይ ወደ ወደ ቅዱስ ዑራኤል -መስቀል አደባባይ (22 አደባባይ በተመሣሣይ ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ ላይ)
➡️ ከአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ (አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ)
➡️ ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
➡️ ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት
➡️ ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ ጋዜቦ አደባባይ (መስቀል ፍላዎር አደባባይ ላይ)
➡️ ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኤግዚብሽን ውስጥ ለውስጥ ወደ ፊላሚንጎ (ጋዜቦ አደባባይ ላይ)
➡️ ከቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ወደ ለገሃር መብራት ( ቅዱስ ቂርቆስ ወደ ጋዜቦ ላይ)
➡️ ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ
➡️ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር መብራት (ሜክሲኮ አደባባይ ላይ)
➡️ ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ (ፓርላማ መብራት ላይ)
➡️ ከጥይት ቤት ወደ ቅዱስ ገብርኤል (ጥይት ቤት መታጠፊያ ላይ )
➡️ ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ ላይ) ከለሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪም፦
- ከቅዱስ ዑራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
- ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም
- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ጀምሮ ዝግ ተደርጓል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
1😡1.07K❤325👏88😭65🕊48🙏45🤔44😢27💔22🥰15😱13
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ፖሊስ ልዩ ቦታው " ሶማሌ ተራ " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ሰዒድ ጀማል እና ብርሀኑ ቢያድግልኝ የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።
ግለሰቦቹን የያዘው የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንደሚያዘጋጁ ከህብረተሠቡ በደረሠው ጥቆማ ነው።
የፍርድ ቤት የመያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹን ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር እንዳዋለቸው አመልክቷል።
ከተያዙት ሀሰተኛ ሰነዶች መካከል ፦
- የተለያዩ የነዋሪነት መታወቂያዎች፣
- ፓሰፖርቶች፣
- የትምህርት እና የህክምና ማስረጃዎች፣
- መንጃ ፈቃዶች ይገኙበታል።
ሰነዶቹን የሚያዘጋጁበት 1 ኮምፒውተር፣ 1ፕሪንተር እንዲሁም የተለያዩ የፕሪንተር ቀለማት መያዛቸውንም ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ እንደሆነ ገልጾ ሲጠናቀቅም በዐቃቤ ህግ በኩል ክስ እንደሚያስመሠርት አሳውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ልዩ ቦታው " ሶማሌ ተራ " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ሰዒድ ጀማል እና ብርሀኑ ቢያድግልኝ የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።
ግለሰቦቹን የያዘው የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንደሚያዘጋጁ ከህብረተሠቡ በደረሠው ጥቆማ ነው።
የፍርድ ቤት የመያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹን ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር እንዳዋለቸው አመልክቷል።
ከተያዙት ሀሰተኛ ሰነዶች መካከል ፦
- የተለያዩ የነዋሪነት መታወቂያዎች፣
- ፓሰፖርቶች፣
- የትምህርት እና የህክምና ማስረጃዎች፣
- መንጃ ፈቃዶች ይገኙበታል።
ሰነዶቹን የሚያዘጋጁበት 1 ኮምፒውተር፣ 1ፕሪንተር እንዲሁም የተለያዩ የፕሪንተር ቀለማት መያዛቸውንም ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ እንደሆነ ገልጾ ሲጠናቀቅም በዐቃቤ ህግ በኩል ክስ እንደሚያስመሠርት አሳውቋል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
👏279❤93😭33😱15😡13🥰12🕊10🤔7🙏5😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
ዒድ ሙባረክ ! 1446ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ አርብ (በጁምዓ እለት) ተከብሮ ይውላል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆን ከልብ ይመኛል። #TikvahEthiopiaFamily❤️ @tikvahethiopia
#AddisAbaba
ከለሊቱ 10:00 ሠዓት ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።
በነገው ዕለት የሚከበረው 1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሰረት፡-
- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
- ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ
- ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ ለገሃር መብራት የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛ ላይ
- ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል አካባቢ
- ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት ትራክ መብራቱ መስቀለኛ ላይ
- ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ከፍተኛ ፍ/ቤትአደባባይ አካባቢ
- ከኑር ህንፃ ወደ ባልቻ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ኑር ህንፃ መስቀለኛ ላይ
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ የሚወስደው መንገድ ጨፌ ሜዳ ትራፊክ መብራት አጠገብ
- ከበርበሬ በረንዳ ወደ አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ አካባቢ
- ከተ/ሃይማኖት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ
- ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንደሚኒየም ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሰንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ አካባቢ
- ከጌጃ ሰፈር በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ አካባቢ
- ከተ/ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ተ/ሃይማኖት አደባባይ አካባቢ
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ድሮ EBC የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መታጠፊያ
- ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን መስቀለኛ አካባቢ
- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ
- ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
- ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ ፓርላማ መብራት ላይ
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መታጠፊያ አካባቢ
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ ላይ ከለሊቱ 10:00 ሠዓት ጀምሮ ይዘጋል።
በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዓለም ባንክ መስቀለኛ አካባቢ ከሚከበረው በዓል ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይደረጋሉ፡፡
በዚህም መሰረት፡-
° ከዩኒሳ አደባባይ ወደ በላይ አብ መኪና መገጣጠሚያ የሚወስደው መንገድ
° ከቱሉዲምቱ - ወደ ጨፌ ይርጋ አደባባይ እስከ ዓለም ባንክ መስቀለኛ የሚወስደው መንገድ
° ከፌሮ ድልድይ እስከ ዩኒሳ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል፡፡
ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaPolice
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከለሊቱ 10:00 ሠዓት ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።
በነገው ዕለት የሚከበረው 1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሰረት፡-
- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
- ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ
- ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ ለገሃር መብራት የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛ ላይ
- ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል አካባቢ
- ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት ትራክ መብራቱ መስቀለኛ ላይ
- ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ከፍተኛ ፍ/ቤትአደባባይ አካባቢ
- ከኑር ህንፃ ወደ ባልቻ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ኑር ህንፃ መስቀለኛ ላይ
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ የሚወስደው መንገድ ጨፌ ሜዳ ትራፊክ መብራት አጠገብ
- ከበርበሬ በረንዳ ወደ አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ አካባቢ
- ከተ/ሃይማኖት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ
- ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንደሚኒየም ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሰንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ አካባቢ
- ከጌጃ ሰፈር በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ አካባቢ
- ከተ/ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ተ/ሃይማኖት አደባባይ አካባቢ
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ድሮ EBC የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መታጠፊያ
- ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን መስቀለኛ አካባቢ
- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ
- ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
- ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ ፓርላማ መብራት ላይ
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መታጠፊያ አካባቢ
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ ላይ ከለሊቱ 10:00 ሠዓት ጀምሮ ይዘጋል።
በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዓለም ባንክ መስቀለኛ አካባቢ ከሚከበረው በዓል ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይደረጋሉ፡፡
በዚህም መሰረት፡-
° ከዩኒሳ አደባባይ ወደ በላይ አብ መኪና መገጣጠሚያ የሚወስደው መንገድ
° ከቱሉዲምቱ - ወደ ጨፌ ይርጋ አደባባይ እስከ ዓለም ባንክ መስቀለኛ የሚወስደው መንገድ
° ከፌሮ ድልድይ እስከ ዩኒሳ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል፡፡
ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaPolice
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.97K😡190🕊53🥰49😭31🤔24💔23👏22🙏22😱14😢2
" የ3 ዓመት ህጻንን ጨምሮ 9 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል " - ፖሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በተለምዶ አባሳሙኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ረፋድ በግምት 3 ሰዓት ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ከሟቾቹ መካከል የ3 ዓመት ዕድሜ ያለው ሕጻን የሚገኝበት ሲሆን፤ በ8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ፖሊስ ገልጿል።
አደጋው ሊከሰት የቻለው ከሃይሌ ጋርመንት ወደ ዩኒሳ አደባባይ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-78979 ኢት የሆነ የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት አውቶቡስ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-04273 ኢት ከሆነ ሌላ ከባድ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ እና መንገድ ስቶ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ በመግባቱ ነው፡፡
አውቶቡሱ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ከገባ በኋላ ከዩኒሳ አደባባይ ወደ ሃይሌ ጋርመንት ሲጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-77970 ኦሮ ከሆነ ዶልፊን ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ በዶልፊኑ ውስጥ ከነበሩት ተሳፋሪዎች መካከል አሽከርካሪውን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስረድቷል።
ከሟቹቹ መካከል የ3 ዓመት ሕጻን ይገኝበታል።
በሌሎች 8 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
ከዚህ በተጨማሪ በአካባቢው ላይ የቆመ እና በጉዞ ላይ የነበረ ሌሎች ሁለት ተሽከርካሪዎች በአውቶቡሱ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በተለምዶ አባሳሙኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ረፋድ በግምት 3 ሰዓት ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ከሟቾቹ መካከል የ3 ዓመት ዕድሜ ያለው ሕጻን የሚገኝበት ሲሆን፤ በ8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ፖሊስ ገልጿል።
አደጋው ሊከሰት የቻለው ከሃይሌ ጋርመንት ወደ ዩኒሳ አደባባይ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-78979 ኢት የሆነ የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት አውቶቡስ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-04273 ኢት ከሆነ ሌላ ከባድ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ እና መንገድ ስቶ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ በመግባቱ ነው፡፡
አውቶቡሱ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ከገባ በኋላ ከዩኒሳ አደባባይ ወደ ሃይሌ ጋርመንት ሲጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-77970 ኦሮ ከሆነ ዶልፊን ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ በዶልፊኑ ውስጥ ከነበሩት ተሳፋሪዎች መካከል አሽከርካሪውን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስረድቷል።
ከሟቹቹ መካከል የ3 ዓመት ሕጻን ይገኝበታል።
በሌሎች 8 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
ከዚህ በተጨማሪ በአካባቢው ላይ የቆመ እና በጉዞ ላይ የነበረ ሌሎች ሁለት ተሽከርካሪዎች በአውቶቡሱ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
😭1.87K❤685💔107😢89🕊45🙏22😡12🤔7🥰3👏2😱1