TIKVAH-ETHIOPIA
#Reminder 🔔 የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ምዝገባ ሊጠናቀቅ 11 ቀናት ቀርቶታል። አከራይ እና ተከራዮች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም አስፈላጊ ሰነዶችን በመያዝ ምዝገባውን እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀርቧል። ከሰኔ 30 በኃላ የሚደረግ ማንኛውም ምዝገባ ቅጣት እንደሚኖረው ተገልጿል። @tikvahethiopia
#ተራዘሟል
በአዲስ አበባ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ።
ምዝገባው ሰኔ 30 ያበቃል መባሉ ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ይፋ ባደረገው መረጃ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ 248,469 የኪራይ ውል ምዝገባ ተከናውኗል።
አሁንም ምዝገባው እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል።
ነገር ግን ፦
- በርካታ ተመዝጋቢ በመኖሩ
- ቀሪ ያልተመዘገበው የተከራይ አከራይ ውል እስከ ሰኔ 30/2016 መዝግቦ ለማጠናቀቅ አዳጋች ስለሚሆን
- ቀኑ እንዲራዘምም ከህብረተሰብ በቀረበ ጥያቄ የምዝገባ ጊዜው እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ/ም መራዘሙን ቢሮው ገልጿል።
ነዋሪዎች ጊዜው ተራዘመ ብለው ሳይዘናጉ ከመደበኛ የስራ ሰዓት ውጭ ፣ ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ ሳይጨናነቁ ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministration
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ።
ምዝገባው ሰኔ 30 ያበቃል መባሉ ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ይፋ ባደረገው መረጃ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ 248,469 የኪራይ ውል ምዝገባ ተከናውኗል።
አሁንም ምዝገባው እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል።
ነገር ግን ፦
- በርካታ ተመዝጋቢ በመኖሩ
- ቀሪ ያልተመዘገበው የተከራይ አከራይ ውል እስከ ሰኔ 30/2016 መዝግቦ ለማጠናቀቅ አዳጋች ስለሚሆን
- ቀኑ እንዲራዘምም ከህብረተሰብ በቀረበ ጥያቄ የምዝገባ ጊዜው እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ/ም መራዘሙን ቢሮው ገልጿል።
ነዋሪዎች ጊዜው ተራዘመ ብለው ሳይዘናጉ ከመደበኛ የስራ ሰዓት ውጭ ፣ ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ ሳይጨናነቁ ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥሪ ቀርቧል።
#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministration
@tikvahethiopia
❤300👏109😡87🙏35😭21🕊17🤔16😢16🥰14😱3