#AddiAbaba
" ነዋሪዎች በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በ54 የመኖሪያ ቤት የሕብረት ስራ ማሕብራት ከ4 ሺህ በላይ የጋራ የመኖሪያ ቤት ቆጣቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የቤት ግንባታ ዛሬ መጀመሩን የአ/አ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ስራው ያስጀመሩት የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ " የነዋሪው ቀዳሚ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ አማራጭ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንገኛለን " ብለዋል።
" የጋራ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ቆጣቢ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጀውን ይህን አማራጭ ተጠቅመው በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " ሲሉ ገልጸዋል።
የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ ፤ የቤት ልማት አማራጮች ላይ ትኩረት በማድረግ የከተማውን የቤት ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
ቢሮው ፍላጎት እና አቅሙ ያላቸውን የ20/80 እና የ40/60 ቤት ልማት ኘሮግራም ተመዝጋቢ የነበሩትን በ54 በጋራ ህንፃ ህብረት ስራ ማህበር በማደራጀት ወደስራ ለማስገባት ሲሰራ የቆየውን ስራ አጠናቆ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ እንደተጣለ ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ነዋሪዎች በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በ54 የመኖሪያ ቤት የሕብረት ስራ ማሕብራት ከ4 ሺህ በላይ የጋራ የመኖሪያ ቤት ቆጣቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የቤት ግንባታ ዛሬ መጀመሩን የአ/አ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ስራው ያስጀመሩት የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ " የነዋሪው ቀዳሚ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ አማራጭ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንገኛለን " ብለዋል።
" የጋራ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ቆጣቢ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጀውን ይህን አማራጭ ተጠቅመው በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " ሲሉ ገልጸዋል።
የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ ፤ የቤት ልማት አማራጮች ላይ ትኩረት በማድረግ የከተማውን የቤት ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
ቢሮው ፍላጎት እና አቅሙ ያላቸውን የ20/80 እና የ40/60 ቤት ልማት ኘሮግራም ተመዝጋቢ የነበሩትን በ54 በጋራ ህንፃ ህብረት ስራ ማህበር በማደራጀት ወደስራ ለማስገባት ሲሰራ የቆየውን ስራ አጠናቆ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ እንደተጣለ ገልጿል።
@tikvahethiopia