TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddiAbaba

" ነዋሪዎች በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

በ54 የመኖሪያ ቤት የሕብረት ስራ ማሕብራት ከ4 ሺህ በላይ የጋራ የመኖሪያ ቤት ቆጣቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የቤት ግንባታ ዛሬ መጀመሩን የአ/አ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።

ስራው ያስጀመሩት የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ " የነዋሪው ቀዳሚ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ አማራጭ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" የጋራ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ቆጣቢ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጀውን ይህን አማራጭ ተጠቅመው በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን ይችላሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ ፤ የቤት ልማት አማራጮች ላይ ትኩረት በማድረግ የከተማውን የቤት ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።

ቢሮው ፍላጎት እና አቅሙ ያላቸውን የ20/80 እና የ40/60 ቤት ልማት ኘሮግራም ተመዝጋቢ የነበሩትን በ54 በጋራ ህንፃ ህብረት ስራ ማህበር በማደራጀት ወደስራ ለማስገባት ሲሰራ የቆየውን ስራ አጠናቆ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ እንደተጣለ ገልጿል።

@tikvahethiopia