TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
30ኛው የትምህርት ጉባኤ አስተናጋጅ ጋምቤላ መሆኗ ታውቋል!

በጅግጅጋ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው #29ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ በዛሬው እለት ተጠናቋል። ጉባኤው በቆይታው የ2011 አም የእቅድ አፈፃፀም እና የ2012 እቅድ ላይ የመከረ ሲሆን፥ በሶስተኛው ቀን ውሎም አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ላይ መክሯል። በዚሁ ፍኖተ ካርታ ላይም በአመዛኙ አተገባበሩ ላይ ቢስተካከሉ እና እንደገና ቢታዩ ያሏቸውን ነጥቦች አንስተዋል ጉባኤተኛቹ።

በዚህም ፍኖተ ካርታውን ለመተግበር የሽግግር ጊዜና ከቀደመው ስርአት መውጫ ስትራቴጅ ያስፈልጋል፣ ለመምህራን የተሰጠው ስልጠና በቂ አይደለም፣ የመፅሀፍ እና ትምህርት ግብአት ዝግጅት በበቂ ሁኔታ አልተሟላም፣ ሁሉም ሳይስማማበት ወደ ትግበራ መግባቱ ችግር ይፈጥራል፣ ያልተወያዩ ክልሎችና የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ፣ የሚሉ ሃሳቦች ተነስተዋል።

https://telegra.ph/ETH-08-31-4

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia