#19_ዓመት ?
የ14 ዓመቷን ልጅ የደፈረው እና ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ በ19 ዓመት መቀጣቱ ተሰምቷል።
ተከሳሹ አላዩ ሞገስ ደሳለኝ ይባላል።
ጥር 29 ቀን 2015 ዓ / ም ከጠዋቱ በግምት 1፡30 ሲሆን በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 ሽሮ ሜዳ አዲስ ተስፋ ትምህርት ቤት አካባቢ የ14 ዓመት የሆነችውን የግል ተበዳይ የምትኖርበት መኖሪያ ቤት ይገባል።
ከዛም በጥፊ በመምታት ፣ እንዳትጮህ በአፏ ውስጥ ጨርቅ በመጠቅጠቅ እና አንገቷን በሁለት እጁ አንቆ በመያዝ በኃይል የግብረ-ስጋ ግንኙነት ይፈጽምባታል።
በአፏ ውስጥ #ጨርቅ_በመጠቅጠቁ እና አንገቷን በማነቁ ምክንያት ትንፋሽ አጥሯት ሕይወቷ ሊያልፍ ችሏል።
ጉዳዩም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 11ኛ ወንጀል ችሎት ሲታይ ቆይቷል።
የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሹ ክሱን እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ የመከላከያ ምስክሮችን ያሰማ ቢሆንም የቀረበበትን ክስ ግን ሊከላከል አልቻለም።
ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት " በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ " ሲል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከፍትህ ሚኒስቴር ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
የ14 ዓመቷን ልጅ የደፈረው እና ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ በ19 ዓመት መቀጣቱ ተሰምቷል።
ተከሳሹ አላዩ ሞገስ ደሳለኝ ይባላል።
ጥር 29 ቀን 2015 ዓ / ም ከጠዋቱ በግምት 1፡30 ሲሆን በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 ሽሮ ሜዳ አዲስ ተስፋ ትምህርት ቤት አካባቢ የ14 ዓመት የሆነችውን የግል ተበዳይ የምትኖርበት መኖሪያ ቤት ይገባል።
ከዛም በጥፊ በመምታት ፣ እንዳትጮህ በአፏ ውስጥ ጨርቅ በመጠቅጠቅ እና አንገቷን በሁለት እጁ አንቆ በመያዝ በኃይል የግብረ-ስጋ ግንኙነት ይፈጽምባታል።
በአፏ ውስጥ #ጨርቅ_በመጠቅጠቁ እና አንገቷን በማነቁ ምክንያት ትንፋሽ አጥሯት ሕይወቷ ሊያልፍ ችሏል።
ጉዳዩም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 11ኛ ወንጀል ችሎት ሲታይ ቆይቷል።
የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሹ ክሱን እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ የመከላከያ ምስክሮችን ያሰማ ቢሆንም የቀረበበትን ክስ ግን ሊከላከል አልቻለም።
ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት " በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ " ሲል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከፍትህ ሚኒስቴር ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia